እስራኤል ምንም አይነት የሰብአዊ እርዳታዎች ወደ ጋዛ ሰርጥ እንዳይገቡ ማስቆሟ ተነገረ
።።።።።።።።።።።።።።።።።።
በእስራኤልና በሀማስ መካከል ሲተገበር የቆየዉ የተኩስ አቁም ስምምነት የመጀመሪያ ምዕራፍ ወደ ሁለተኛ ምዕራፍ ለመቀጠል ስምምነት ላይ ሳይደረስ መጠናቀቁ ይታወቃል። ይንንም ተከትሎ ነዉ እስራኤል የሰብአዊ እርዳታዎችን ያስቆመችዉ።
ቀደም ሲል እስራኤል የተኩስ አቁም ስምምነቱ በጋዛ የረመዳን እና የፋሲካ ወቅቶች እስኪያልቁ እንዲራዘም በአሜሪካ የቀረበዉን ሃሳብ እንደምትቀበል አስታውቃ ነበር።
ሃማስ በጋዛ ቋሚ የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ ለመድረስ እስራኤል የተፈራረመችውን ስምምነት ምዕራፍ ሁለት ተግባራዊ ለማድረግ ያለዉን ፍላጎት አሳይቷል ተብሏል።
በሌላ በኩል በጋዛ የሚገኙ ፍልስጤማውያን በግዛቲቱ የተከሰተዉን ውድመት ተከትሎ ወደ ጦርነት ሊመልሰን ይችላል የሚል ፍራቻ እንዳላቸው በእስልምና እምነት ተከታዮች ዘንድ የተቀደሰዉ የረመዳን ወር የፆም የመጀመሪያ ቀናቸውን በያዙበት ቀን ገልፀዋል።
የጋዛ ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር በጦርነቱ እስካሁን 48,388 ፍልስጤማውያን መሞታቸውን ሲያረጋግጥ 111,803 ሰዎች ቆስለዋል ብሏል። እ.ኤ.አ. በጥቅምት 7 ቀን 2023 በተጀመረዉ የእስራኤል ሀማስ ጦርነት ቢያንስ 1,139 እስራኤላዉያን ህይወታቸዉ ያለፈ ሲሆን ከ200 በላይ በምርኮ ተወስደዋል። ዘገባዉ የአልጀዚራ ነዉ
በ- ሊያ ክብሮም
@Ethionews433 @Ethionews433
።።።።።።።።።።።።።።።።።።
በእስራኤልና በሀማስ መካከል ሲተገበር የቆየዉ የተኩስ አቁም ስምምነት የመጀመሪያ ምዕራፍ ወደ ሁለተኛ ምዕራፍ ለመቀጠል ስምምነት ላይ ሳይደረስ መጠናቀቁ ይታወቃል። ይንንም ተከትሎ ነዉ እስራኤል የሰብአዊ እርዳታዎችን ያስቆመችዉ።
ቀደም ሲል እስራኤል የተኩስ አቁም ስምምነቱ በጋዛ የረመዳን እና የፋሲካ ወቅቶች እስኪያልቁ እንዲራዘም በአሜሪካ የቀረበዉን ሃሳብ እንደምትቀበል አስታውቃ ነበር።
ሃማስ በጋዛ ቋሚ የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ ለመድረስ እስራኤል የተፈራረመችውን ስምምነት ምዕራፍ ሁለት ተግባራዊ ለማድረግ ያለዉን ፍላጎት አሳይቷል ተብሏል።
በሌላ በኩል በጋዛ የሚገኙ ፍልስጤማውያን በግዛቲቱ የተከሰተዉን ውድመት ተከትሎ ወደ ጦርነት ሊመልሰን ይችላል የሚል ፍራቻ እንዳላቸው በእስልምና እምነት ተከታዮች ዘንድ የተቀደሰዉ የረመዳን ወር የፆም የመጀመሪያ ቀናቸውን በያዙበት ቀን ገልፀዋል።
የጋዛ ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር በጦርነቱ እስካሁን 48,388 ፍልስጤማውያን መሞታቸውን ሲያረጋግጥ 111,803 ሰዎች ቆስለዋል ብሏል። እ.ኤ.አ. በጥቅምት 7 ቀን 2023 በተጀመረዉ የእስራኤል ሀማስ ጦርነት ቢያንስ 1,139 እስራኤላዉያን ህይወታቸዉ ያለፈ ሲሆን ከ200 በላይ በምርኮ ተወስደዋል። ዘገባዉ የአልጀዚራ ነዉ
በ- ሊያ ክብሮም
@Ethionews433 @Ethionews433