ኢትዮጲያዊቷ የእግር ኳስ ተጫዋች ወንድ ነሽ ቢሉኝም እኔ ግን ሴት ነኝ መገለሉ ይቁም ስትል ተናገረች
(ከአራት ዓመት በፊት የተሰራ ዘገባ)
ለሀዋሳ ከተማ የምትጫወተዉ መሳይ ተመስገን በተያዘዉ የዉድድር ዓመት የሴቶች ፕርሚየር ሊግ በኮከብ ግብ አግቢነት እየመራች ትገኛለች፡፡
ጾታዋን በተመለከተ በርካቶች ጥያቄን ያነሳሉ አንዳንዶችም ከፍተኛ የመገለል በደል እንደሚያደርሱባት ከጋዜጠኛ ምህረት ተስፋዬ ጋር በነበራት ቆይታ ተናግራለች፡፡
ተጫዋቿ በ2006 ዓመት ባህር ዳር ላይ ተዘጋጅቶ በነበረ የክልሎች ሻምፒዮና ጨዋታ ላይ በአንድ ጨዋታ አራት ግቦችን ታስቆጥራለች፡፡ይህ ግን መደነቅ አልነበረም ያተረፈላት ይልቁኑ ይህ ተጫዋች ወንድ ነዉ፤አብሮን ሊጫወት አይገባም የሚሉ ዘለፋና የደጋፊዎች ስድብ ከምቆጣጠረዉ በላይ ስሜቴን የጎዳ ክስተት ነበር ስትል መሳይ ተመስገን ተናግራለች፡፡
በእንዲህ ዓይነት ጫና እና ወከባ የተነሳ ከሶስት ዓመታት በላይ ከዉድድር ራሷ እንድታገል አስገድዷታል፡፡በድጋሚ ወደምትመደዉ ስፖርት እንድትመለስ አሰልጣኝ ዮሴፍ ገ/ወልድ ትልቁን ድጋፍ እንዳደረገላትም ታነሳለች፡፡
እግር ኳስ ፌደሬሽኑ በጠየቀዉ መሰረት ምርመራዉን አከናዉና በምርመራዉ ሴት መሆኗ ተረጋግጦላታል፡፡ምም እንኳን መሳይ በምርመራዉ ሴት መሆኗ ቢረጋገጥም በሜዳና ከሜዳ ዉጪ ስሜቷን የሚጎዱ ዘለፋና መገለል ደርሶባታል፡፡
የሰዉነቴ አቋም እኔ ፈልጌ ያመጣሁት አይደለም፡፡ፈጣሪ የሰዉ ልጆችን ሲፈጥር በምክንያት ነዉ፡፡ ስለ እኔ ብዙ የሚሉ ሰዎች ግጭታቸዉ ከእኔ ጋር ሳይሆን ከፈጣሪ ጋር ነው፡፡
መሳይ የማንችስተር ዩናይትድ ደጋፊ መሆኗን የምትናገር ሲሆን ከወጪ የክርስቲያኖ ሮናልዶ አድናቂ ከሀገር ዉስጥ ደግሞ የሽታዬ ሲሳይ አድናቂ መሆኗን የብስራት ሬዲዮ የቀድሞ ዘጋቢ ምህረት ተስፋዬ ተናግራለች፡፡
@Ethionews433 @Ethionews433
(ከአራት ዓመት በፊት የተሰራ ዘገባ)
ለሀዋሳ ከተማ የምትጫወተዉ መሳይ ተመስገን በተያዘዉ የዉድድር ዓመት የሴቶች ፕርሚየር ሊግ በኮከብ ግብ አግቢነት እየመራች ትገኛለች፡፡
ጾታዋን በተመለከተ በርካቶች ጥያቄን ያነሳሉ አንዳንዶችም ከፍተኛ የመገለል በደል እንደሚያደርሱባት ከጋዜጠኛ ምህረት ተስፋዬ ጋር በነበራት ቆይታ ተናግራለች፡፡
ተጫዋቿ በ2006 ዓመት ባህር ዳር ላይ ተዘጋጅቶ በነበረ የክልሎች ሻምፒዮና ጨዋታ ላይ በአንድ ጨዋታ አራት ግቦችን ታስቆጥራለች፡፡ይህ ግን መደነቅ አልነበረም ያተረፈላት ይልቁኑ ይህ ተጫዋች ወንድ ነዉ፤አብሮን ሊጫወት አይገባም የሚሉ ዘለፋና የደጋፊዎች ስድብ ከምቆጣጠረዉ በላይ ስሜቴን የጎዳ ክስተት ነበር ስትል መሳይ ተመስገን ተናግራለች፡፡
በእንዲህ ዓይነት ጫና እና ወከባ የተነሳ ከሶስት ዓመታት በላይ ከዉድድር ራሷ እንድታገል አስገድዷታል፡፡በድጋሚ ወደምትመደዉ ስፖርት እንድትመለስ አሰልጣኝ ዮሴፍ ገ/ወልድ ትልቁን ድጋፍ እንዳደረገላትም ታነሳለች፡፡
እግር ኳስ ፌደሬሽኑ በጠየቀዉ መሰረት ምርመራዉን አከናዉና በምርመራዉ ሴት መሆኗ ተረጋግጦላታል፡፡ምም እንኳን መሳይ በምርመራዉ ሴት መሆኗ ቢረጋገጥም በሜዳና ከሜዳ ዉጪ ስሜቷን የሚጎዱ ዘለፋና መገለል ደርሶባታል፡፡
የሰዉነቴ አቋም እኔ ፈልጌ ያመጣሁት አይደለም፡፡ፈጣሪ የሰዉ ልጆችን ሲፈጥር በምክንያት ነዉ፡፡ ስለ እኔ ብዙ የሚሉ ሰዎች ግጭታቸዉ ከእኔ ጋር ሳይሆን ከፈጣሪ ጋር ነው፡፡
መሳይ የማንችስተር ዩናይትድ ደጋፊ መሆኗን የምትናገር ሲሆን ከወጪ የክርስቲያኖ ሮናልዶ አድናቂ ከሀገር ዉስጥ ደግሞ የሽታዬ ሲሳይ አድናቂ መሆኗን የብስራት ሬዲዮ የቀድሞ ዘጋቢ ምህረት ተስፋዬ ተናግራለች፡፡
@Ethionews433 @Ethionews433