ጌታዬ ሆይ ልቤን አስፋልኝ


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Религия


رَّبِّ اغْفِرْ لِي وَلِوَالِدَيَّ وَلِمَن دَخَلَ بَيْتِيَ مُؤْمِنًا وَلِلْمُؤْمِنِينَ وَالْمُؤْمِنَاتِ وَلَا تَزِدِ الظَّالِمِينَ إِلَّا تَبَارًا
(ኑሕ - 28)
«ጌታዬ ሆይ! ለእኔም ለወላጆቼም ምእመን ኾኖ በቤቴ ለገባም ሰው ሁሉ ለምእመናንና ለምእምናትም ምሕረት አድርግ፡፡ ከሓዲዎችንም ከጥፋት በቀር አትጨምርላቸው

Связанные каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Религия
Статистика
Фильтр публикаций


እዝነት ከፍቅር የበለጠ ይጠነክራል
እዝነት ፍቅርን, ርህራሄን, ይቅር ማለትንና
ውዴታን አቅፋ የያዘች ናት
ሁላችንም ማፍቀር ስንችል
ግን ጥቂቶቻችን ናቸው 
ልባቸው ውስጥ እዝነት ያላቸው ።

እዝነት እና ፍቅር ካለህ ደሞ እድለኛው ሰው አንተ ነህ!

الروم 30:21

وَمِنْ آيَاتِهِ أَنْ خَلَقَ لَكُم مِّنْ أَنفُسِكُمْ أَزْوَاجًا لِّتَسْكُنُوا إِلَيْهَا وَجَعَلَ بَيْنَكُم مَّوَدَّةً وَرَحْمَةً ۚ إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَآيَاتٍ لِّقَوْمٍ يَتَفَكَّرُونَ

ለእናንተም ከነፍሶቻችሁ (ከጎሶቻችሁ) ሚስቶችን ወደእነርሱ ትረኩ ዘንድ መፍጠሩ፣ በመካከላችሁም #ፍቅርንና_እዝነትን ማድረጉ ከአስደናቂ ምልክቶቹ ነው፡፡ በዚህ ውስጥ ለሚያስተውሉ ሕዝቦች ተዓምራቶች አልሉ፡፡

https://t.me/My_Lord_is_with_me
href='' rel='nofollow'>


📚ጣፋጭ ቲላዋ የማታ ግብዣችን 🎀
يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا اتَّقُوا اللَّهَ وَلْتَنظُرْ نَفْسٌ مَّا قَدَّمَتْ لِغَدٍ ۖ وَاتَّقُوا اللَّهَ ۚ إِنَّ اللَّهَ خَبِيرٌ بِمَا تَعْمَلُونَ

እናንተ ያመናችሁ ሆይ! አላህን ፍሩ፡፡ ማንኛይቱም ነፍስ ለነገ ያስቀደመችውን ትመልከት፡፡ አላህንም ፍሩ፡፡ አላህ በምትሠሩት ሁሉ ውስጠ ዐዋቂ ነው፡፡
وَلَا تَكُونُوا كَالَّذِينَ نَسُوا اللَّهَ فَأَنسَاهُمْ أَنفُسَهُمْ ۚ أُولَٰئِكَ هُمُ الْفَاسِقُونَ
እንደነዚያም አላህን እንደረሱትና ነፍሶቻቸውን እንዳስረሳቸው (ሰዎች) አትኹኑ፡፡ እነዚያ እነርሱ አመጸኞቹ ናቸው፡፡
لَا يَسْتَوِي أَصْحَابُ النَّارِ وَأَصْحَابُ الْجَنَّةِ ۚ أَصْحَابُ الْجَنَّةِ هُمُ الْفَائِزُونَ
የእሳት ጓዶችና የገነት ጓዶች አይተካከሉም፡፡ የገነት ጓዶች እነርሱ ምኞታቸውን አግኚዎች ናቸው፡፡
لَوْ أَنزَلْنَا هَٰذَا الْقُرْآنَ عَلَىٰ جَبَلٍ لَّرَأَيْتَهُ خَاشِعًا مُّتَصَدِّعًا مِّنْ خَشْيَةِ اللَّهِ ۚ وَتِلْكَ الْأَمْثَالُ نَضْرِبُهَا لِلنَّاسِ لَعَلَّهُمْ يَتَفَكَّرُونَ
ይህንን ቁርኣን በተራራ ላይ ባወረድነው ኖሮ ከአላህ ፍራቻ (የተነሳ) ተዋራጅ ተሰንጣቂ ኾኖ ባየኸው ነበር፡፡ ይህችንም ምሳሌ ይገመግሙ ዘንድ ለሰዎች እንገልፃለን፡፡
📚📚🥀🥀🌿🌿🌹🌹🌹🎀🎀


htt rel='nofollow'>ps://t.me/My_Lord_is_with_me


ያ አሏህ ፣ ከባሪያዎችህ ሁሉ መርጠህ ረመዷንን የመፆም እድል ወፈቅከን። አልሀምዱሊላህ ያጎደልነውን አንተው  ሞልተህ ፆማችንን፣ ሰላታችንን፣ ዱአችንን እና ሌሎች ስራዎቻችንን ተቀበለን። ላጠፋነው ማርታህን ለግሰን። የደስታ ቀን በሆነችው ኢዳችን ደግሞ አንተን እያውሱና ከወንጀል ርቀው ከሚውሉ ባሪያዎችህ  ጋር አድርገን። አሚን ያ ረብ፣

🌙⭐ عيد مبارك

کل عام وأنتم بخير🌙⭐


https://t.me/ishaqdawa

https://t.me/My_Lord_is_with_me


۞ وَقَالَ الَّذِينَ لَا يَرْجُونَ لِقَاءَنَا لَوْلَا أُنزِلَ عَلَيْنَا الْمَلَائِكَةُ أَوْ نَرَىٰ رَبَّنَا ۗ لَقَدِ اسْتَكْبَرُوا فِي أَنفُسِهِمْ وَعَتَوْا عُتُوًّا كَبِيرًا
እነዚያም መገናኘታችንን የማይፈሩት በእኛ ላይ ለምን መላእክት አልወረደም፡፡ ወይም ጌታችንን ለምን አናይም አሉ፡ በነፍሶቻቸው ውስጥ በእርግጥ ኮሩ፡፡ ታላቅንም አመጽ አመፁ፡፡
يَوْمَ يَرَوْنَ الْمَلَائِكَةَ لَا بُشْرَىٰ يَوْمَئِذٍ لِّلْمُجْرِمِينَ وَيَقُولُونَ حِجْرًا مَّحْجُورًا
መላእክትን በሚያዩበት ቀን በዚያ ጊዜ ለአመጸኞች ምስራች የላቸውም፡፡ «የተከለከለ ክልክልም አድርገን» ይላሉ፡፡
وَقَدِمْنَا إِلَىٰ مَا عَمِلُوا مِنْ عَمَلٍ فَجَعَلْنَاهُ هَبَاءً مَّنثُورًا
ከሥራም ወደ ሠሩት እናስባለን፡፡ የተበተነ ትቢያም እናደርገዋለን፡፡
أَصْحَابُ الْجَنَّةِ يَوْمَئِذٍ خَيْرٌ مُّسْتَقَرًّا وَأَحْسَنُ مَقِيلًا
የገነት ሰዎች በዚያ ቀን በመርጊያ የተሻሉ በማረፊያም በጣም ያማሩ ናቸው፡፡
وَيَوْمَ تَشَقَّقُ السَّمَاءُ بِالْغَمَامِ وَنُزِّلَ الْمَلَائِكَةُ تَنزِيلًا

ሰማይም በደመና የምትቀደድበትንና መላእክትም መወረድን የሚወርድበትን ቀን (አስታውስ)፡፡
الْمُلْكُ يَوْمَئِذٍ الْحَقُّ لِلرَّحْمَٰنِ ۚ وَكَانَ يَوْمًا عَلَى الْكَافِرِينَ عَسِيرًا
እውነተኛው ንግሥና በዚያ ቀን ለአልራሕማን ብቻ ነው፡፡ በከሓዲዎችም ላይ አስቸጋሪ ቀን ነው፡፡وَيَوْمَ يَعَضُّ الظَّالِمُ عَلَىٰ يَدَيْهِ يَقُولُ يَا لَيْتَنِي اتَّخَذْتُ مَعَ الرَّسُولِ سَبِيلًا

በዳይም «ከመልክተኛው ጋር ቀጥተኛን መንገድ ይዤ በኾነ ዋ ምኞቴ!» እያለ (በጸጸት) ሁለት እጆቹን የሚነክስበትን ቀን (አስታውስ)፡፡
يَا وَيْلَتَىٰ لَيْتَنِي لَمْ أَتَّخِذْ فُلَانًا خَلِيلًا
«ዋ ጥፋቴ! እገሌን ወዳጅ ባልያዝኩ ኖሮ እመኛለሁ፡፡
لَّقَدْ أَضَلَّنِي عَنِ الذِّكْرِ بَعْدَ إِذْ جَاءَنِي ۗ وَكَانَ الشَّيْطَانُ لِلْإِنسَانِ خَذُولًا
(የእምነት ቃልን) ከመጣልኝ በኋላ ከማስታወስ በእርግጥ አሳሳተኝ» (ይላል)፡፡ ሰይጣንም ለሰው አጋላጭ ነው፡፡
وَقَالَ الرَّسُولُ يَا رَبِّ إِنَّ قَوْمِي اتَّخَذُوا هَٰذَا الْقُرْآنَ مَهْجُورًا
መልክተኛውም «ጌታዬ ሆይ! ሕዝቦቼ ይህንን ቁርኣን የተተወ ነገር አድርገው ያዙት» አለ፡፡
وَكَذَٰلِكَ جَعَلْنَا لِكُلِّ نَبِيٍّ عَدُوًّا مِّنَ الْمُجْرِمِينَ ۗ وَكَفَىٰ بِرَبِّكَ هَادِيًا وَنَصِيرًا
እንደዚሁም ለነቢዩ ሁሉ ከአመጸኞች የኾነ ጠላትን አድርገናል፡፡ መሪና ረዳትም በጌታህ በቃ፡፡
وَقَالَ الَّذِينَ كَفَرُوا لَوْلَا نُزِّلَ عَلَيْهِ الْقُرْآنُ جُمْلَةً وَاحِدَةً ۚ كَذَٰلِكَ لِنُثَبِّتَ بِهِ فُؤَادَكَ ۖ وَرَتَّلْنَاهُ تَرْتِيلًا

እነዚያ የካዱትም «ቁርኣን በእርሱ ላይ ለምን በጠቅላላ አንድ ጊዜ አልተወረደም» አሉ፡፡ እንደዚሁ በእርሱ ልብህን ልናረጋ (ከፋፍለን አወረድነው)፡፡ ቀስ በቀስ መለያየትንም ለየነው፡፡

وَلَا يَأْتُونَكَ بِمَثَلٍ إِلَّا جِئْنَاكَ بِالْحَقِّ وَأَحْسَنَ تَفْسِيرًا
በጥያቄም አይመጡብህም እውነተኛውን (መልስ) መልካምን ፍችም የምናመጣልህ ብንኾን እንጅ፡፡


https://t.me/My_Lord_is_with_me


ከውሸት_እንራቅ

ረሱል (ﷺ) እንዲህ ይላሉ ፦
ውሸትን አደራችሁን ራቁ ፤ ውሸት ወደ ጥመት ይመራልና ጥመት ደግሞ ወደ እሳት ይመራል  አንድ ሰው ከመዋሸት እና ውሸትን ከመጠባበቅ ላይ አይወገድም አላህ ዘንድ ውሸታም ተብሎ እስኪመዘገብ ድረስ
ቡኻሪ ፥ 6094 ሙስሊም ፥ 2607
https://t.me/My_Lord_is_with_me
href='' rel='nofollow'>


በቁርአን የተገለፁ የአላህን እዝነት(ራህመቱን) ለማግኘት የሚረዱን ተግባራቶች በጥቂቱ…።

አላህንና መልእክተኛውን ﷺመታዘዝ
(وَأَطِيعُوا اللَّهَ وَالرَّسُولَ لَعَلَّكُمْ تُرْحَمُونَ)
[سورة آل عمران 132]
{ይታዘንላችሁም ዘንድ አላህንና መልክተኛውን ታዘዙ፡፡}[ሱራ ኢምራን 132]

ቁርአን ሲቀራ #ማድመጥና ዝም ማለት للقرآن
(وَإِذَا قُرِئَ الْقُرْآنُ فَاسْتَمِعُوا لَهُ وَأَنْصِتُوا لَعَلَّكُمْ تُرْحَمُونَ)
[سورة اﻷعراف 204]
{ቁርኣንም በተነበበ ጊዜ እርሱን አዳምጡ፡፡ ጸጥም በሉ፡፡ ይታዘንላችኋልና፡፡}[አዕራፍ 204]

የቁርአንን መመሪያ መከተልና በቁርአን መተግበር
اتباع
(وَهَٰذَا كِتَابٌ أَنْزَلْنَاهُ مُبَارَكٌ فَاتَّبِعُوهُ وَاتَّقُوا لَعَلَّكُمْ تُرْحَمُونَ)
[سورة اﻷنعام 155]
{ይህም ያወረድነው የኾነ የተባረከ መጽሐፍ ነው፡፡ ተከተሉትም፡፡ ይታዘንላችሁም ዘንድ (ከክህደት) ተጠንቀቁ፡፡}[አንዓም 155]


አላህን ምህረት መለመን الاستغفار
(لَوْلَا تَسْتَغْفِرُونَ اللَّهَ لَعَلَّكُمْ تُرْحَمُونَ)
[سورة النمل 46]
{ይታዘንላችሁ ዘንድ #አላህን ምሕረትን አትለምኑምን»}[ነምል46]

አላህን መፍራትና በመካከላችን ማሳመር تقوى الله واصلاح

(إِنَّمَا الْمُؤْمِنُونَ إِخْوَةٌ فَأَصْلِحُوا بَيْنَ أَخَوَيْكُمْ ۚ وَاتَّقُوا اللَّهَ لَعَلَّكُمْ تُرْحَمُونَ)
[سورة الحجرات 10]
{ምእመናኖች ወንድማመቾች ናቸው፡፡ በሁለት ወንድሞቻችሁም መካከል አስታርቁ፡፡ ይታዘንላችሁም ዘንድ አላህን ፍሩ፡፡}[ሑጅራት 10]
📚😍

https://t.me/My_Lord_is_with_me


#ነቢዩ ((‌‏(ﷺ) እንዲህ ይላሉ፦

“የአደም ልጅ ሲሞት #ሶስት ነገሮች ሲቀሩ ስራው ይቋረጣል። ቀጣይነት ያለው #ሰደቃ፤ ጠቃሚ የሆነ #እውቀትና ለሱ ዱአ የሚያደርግለት መልካም #ልጅ።”

[ሙስሊም ዘግበውታል]




📚የጥወት #ግብዣ #ምንኛ የማረ ቲላዋ🌹🎀📚
ولَقَدْ نَعْلَمُ أَنَّهُمْ يَقُولُونَ إِنَّمَا يُعَلِّمُهُ بَشَرٌ ۗ لِّسَانُ الَّذِي يُلْحِدُونَ إِلَيْهِ أَعْجَمِيٌّ وَهَٰذَا لِسَانٌ عَرَبِيٌّ مُّبِينٌ
እነርሱም «እርሱን (ቁርኣንን) የሚያስተምረው ሰው ብቻ ነው» ማለታቸውን በእርግጥ እናውቃለን፡፡ የዚያ ወደርሱ የሚያስጠጉበት ሰው ቋንቋ ዐጀም ነው፡፡ ይህ (ቁርአን) ግን ግልጽ ዐረብኛ ቋንቋ ነው፡፡
إِنَّ الَّذِينَ لَا يُؤْمِنُونَ بِآيَاتِ اللَّهِ لَا يَهْدِيهِمُ اللَّهُ وَلَهُمْ عَذَابٌ أَلِيمٌ
እነዚያን በአላህ አንቀጾች የማያምኑትን አላህ አይመራቸውም፤ ለነሱም አሳማሚ ቅጣት አላቸው፡፡
إِنَّمَا يَفْتَرِي الْكَذِبَ الَّذِينَ لَا يُؤْمِنُونَ بِآيَاتِ اللَّهِ ۖ وَأُولَٰئِكَ هُمُ الْكَاذِبُونَ
ውሸትን የሚቀጣጥፉት እነዚያ በአላህ አንቀጾች የማያምኑት ብቻ ናቸው፡፡ እነዚያም ውሸታሞቹ እነሱ ብቻ ናቸው፡፡
مَن كَفَرَ بِاللَّهِ مِن بَعْدِ إِيمَانِهِ إِلَّا مَنْ أُكْرِهَ وَقَلْبُهُ مُطْمَئِنٌّ بِالْإِيمَانِ وَلَٰكِن مَّن شَرَحَ بِالْكُفْرِ صَدْرًا فَعَلَيْهِمْ غَضَبٌ مِّنَ اللَّهِ وَلَهُمْ عَذَابٌ عَظِيمٌ
🎀🎀📚🥀🥀👍🌿📚📚📚📚


htt rel='nofollow'>ps://t.me/My_Lord_is_with_me


ረመዳን ሙባረክ ያ ዑመተ ሙሀመድ ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም: ፆሙን በስርዓቱ ሰርተዉበት ከሚጠቀሙት ሰዎች ያድርገን


የረመዷን ስጦታ

ረመዷን ሙባረክ ያ ሙሥሊሙን ወሙሥሊማት!

በ 13 አርስት የተሰደረ መጣጥፍ በረመዷን ወር እንካችሁ ብለናል። ሊንኩን በማስፈንጠር ያግኙት!

1. ሶውም
https://t.me/Wahidcom/3136

2. የጦም ትሩፋት
https://t.me/Wahidcom/3470

3. ረመዷን
https://t.me/Wahidcom/2727

4.. የረመዷን ወር
https://t.me/Wahidcom/3107

5. የክርስትና ጦም
https://t.me/Wahidcom/3176

6. የጨረቃ አቆጣጠር
https://t.me/Wahidcom/2717

7. ጨረቃ እና ኮከብ
https://t.me/Wahidcom/2360

8. የሚታሰሩ ሰይጣናት
https://t.me/Wahidcom/2724

9. ሡሑር
https://t.me/Wahidcom/2726

10. ተራዊህ
https://t.me/Wahidcom/833

11. ኢዕቲካፍ
https://t.me/Wahidcom/2286

12. ለይለቱል ቀድር
https://t.me/Wahidcom/2289

13. መሓላ እና ማካካሻው
https://t.me/Wahidcom/2336

ሁሉም ቦታ ለሁሉም ሰው እንዲዳረስ አሰራጩ!

ወጀዛኩሙሏህ ኸይራ!




የማርቆስ ወንጌል

የማርቆስ ወንጌል እና ስህተቶቹ

ስህተት አንድ፦►“እነሆ፥ መንገድህን የሚጠርግ መልክተኛዬን በፊትህ እልካለሁ የጌታን መንገድ አዘጋጁ ጥርጊያውንም አቅኑ እያለ በምድረ በዳ የሚጮኽ ሰው ድምፅ ተብሎ በነቢዩ በኢሳይያስ እንደ ተጻፈ፥”
  📖[ማርቆስ 1፥2-3]

►ቅሉ ግን ትንቢቱ ያለው ሚልኪያስ ላይ ነው፦“እነሆ፥ መልእክተኛዬን እልካለሁ፥ መንገድንም በፊቴ ያስተካክላል፤ እናንተም የምትፈልጉት ጌታ በድንገት ወደ መቅደሱ ይመጣል፤ የምትወዱትም የቃል ኪዳን መልእክተኛ፥ እነሆ፥ ይመጣል፥ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር።”
  📖[ሚልክያስ 3፥1]

ማርቆስ ኬት አምጥቶ ነው ኢሳይያስ የሚለን ?መንፈስ ቅዱስ ነው ወይስ ማርቆስ የተሳሳው ?

ስህተት ሁለት፦►“እርሱም፦ ዳዊት ባስፈለገውና በተራበ ጊዜ፥ እርሱ አብረውት ከነበሩት ጋር ያደረገውን፥ አብያተር ሊቀ ካህናት በነበረ ጊዜ ወደ እግዚአብሔር ቤት እንደ ገባ፥”“ከካህናት በቀር መብላት ያልተፈቀደውን የመሥዋዕትን እንጀራ እንደ በላ፥ ከእርሱም ጋር ለነበሩት እንደ ሰጣቸው ከቶ አላነበባችሁምን? አላቸው።
  📖[ማርቆስ 2፥25/26]

ዳዊት ያልተፈቀደውን የመሥዋዕት እንጀራ በበላ ጊዜ ሊቀ ካህን የነበረ አብያታር ሳይሆን አቢሜሌክ ነበር፦
📖[1ኛ ሳሙኤል 21፥1/6]
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ ዳዊትም ወደ ካህኑ ወደ አቢሜሌክ ወደ ኖብ መጣ፤ አቢሜሌክም እየተንቀጠቀጠ ዳዊትን ሊገናኘው መጣና፦ ስለ ምን አንተ ብቻህን ነህ? ከአንተስ ጋር ስለ ምን ማንም የለም? አለው።
² ዳዊትም ካህኑን አቢሜሌክን፦ የተላክህበትን ነገርና የሰጠሁህን ትእዛዝ ማንም አይወቅ ብሎ ንጉሡ አንድ ነገር አዝዞኛል፤ ስለዚህም ብላቴኖቹን እንዲህ ባለ ስፍራ ተውኋቸው።
³ አሁንስ በእጅህ ምን አለ? አምስት እንጀራ ወይም የተገኘውን በእጄ ስጠኝ አለው።
⁴ ካህኑም ለዳዊት መልሶ፦ ሁሉ የሚበላው እንጀራ የለኝም፥ ነገር ግን የተቀደስ እንጀራ አለ፤ ብላቴኖቹ ከሴቶቹ ንጹሐን እንደ ሆኑ መብላት ይቻላል አለው።
⁵ ዳዊትም ለካህኑ መልሶ፦ በእውነት ከወጣን ጀምረን እኛ ሰውነታችንን ከሴቶች ሦስት ቀን ጠብቀናል፤ የብላቴኖችም ዕቃ የተቀደሰች ናት፤ ስለዚህ ዛሬ ዕቃቸው የተቀደሰች በመሆንዋ እንጀራው እንደሚበላ እንጀራ ይሆናል አለው።
⁶ ካህኑም በእርሱ ፋንታ ትኩስ እንጀራ ይደረግ ዘንድ ከእግዚአብሔር ፊት ከተነሣው ከገጹ ኅብስት በቀር ሌላ እንጀራ አልነበረምና የተቀደሰውን እንጀራ ሰጠው።

አብያታር የአቢሊክ ልጅ ነው፦“ከአኪጦብም ልጅ ከአቢሜሌክ ልጆች ስሙ አብያታር የሚባል አንዱ ልጅ አምልጦ ወደ ዳዊት ሸሸ።”
►📖[1ኛ ሳሙኤል 22፥20]

ታዲያ ዳዊት ያልተፈቀደውን የመሥዋዕት እንጀራ በበላ ጊዜ ሊቀ ካህን የነበረ አብያታር ሳይሆን አቢሜሌክ ነበር ማርቆስ አብያታር የሚለው ከየት አምጥቶ ነው የተሳሳተው የማርቆስ ጸሐፊ ወይስ የጠቀሰው ኢየሱስ ወይስ መንፈስ ቅዱስ ?

ስህተት ሦስት ፦►“ሙሴ፦ አባትህንና እናትህን አክብር፤ ደግሞ፦ አባቱን ወይም እናቱን የሰደበ ፈጽሞ ይሙት ብሎአልና።”
  📖[ማርቆስ 7፥10]

ሙሴ ሳይሆን እግዚአብሔር ነው ያለው ፦

“አባቱን ወይም እናቱን የሚሰድብ ፈጽሞ ይገደል።”
  📖[ዘጸአት 21፥17]

ይህንን ስህተት ማቴዎስ አስተካክሎታል፦

“እግዚአብሔር፦ አባትህንና እናትህን አክብር፤ ደግሞ፦ አባቱን ወይም እናቱን የሰደበ ፈጽሞ ይሙት ብሎአልና፤”
  📖[ማቴዎስ 15፥4]

ማርቆስ ለምን እግዚአብሔር ያዘዘውን ሙሴ የሚለን?

ማቴዎስ አስታክሎታል

⛳️ተርቡ አሊ


የማቴዎስ ወንጌል

የማቴዎስ ወንጌል እና ስህተቶቹ

ስህተት አንድ፦በዘካርያስ የተነገረውን ትንቢት ኤርሚያስ ነው ማለቱ፦

“በዚያን ጊዜ በነቢዩ በኤርምያስ የተባለው፦ ከእስራኤል ልጆችም አንዳንዶቹ የገመቱትን፥ የተገመተውን ዋጋ ሠላሳ ብር ያዙ፥”
  📖[ማቴዎስ 27፥9]

ቅሉ ግን ይህንን ትንቢት የምናገኘው ዘካርያስ ላይ ነው፦
“እኔም፦ ደስ ብሎአችሁ እንደ ሆነ ዋጋዬን ስጡኝ፤ ያለዚያ ግን ተዉት አልሁ። እነርሱም ለዋጋዬ ሠላሳ ብር መዘኑ።”እግዚአብሔርም፦ የተስማሙበትን የከበረውን ዋጋዬን በግምጃ ቤቱ ውስጥ አኑረው አለኝ። እኔም ሠላሳውን ብር ወስጄ በእግዚአብሔር ቤት ባለው በግምጃ ቤቱ ውስጥ አኖርሁት።”
  📖[ዘካርያስ 11፥12/13]

ማቴዎስ ከየት አምጥቶ ነው ኤርሚያስ ነው የሚለን?

ስህተት ሁለት፦ የዮዳሄ ልጅ ዘካርያስ ሞት የበራክዩ ልጅ ዘካርያስ ነው ማለቱ፦

“ከጻድቁ ከአቤል ደም ጀምሮ በቤተ መቅደስና በመሠዊያው መካከል እስከ ገደላችሁት እስከ በራክዩ ልጅ እስከ ዘካርያስ ደም ድረስ በምድር ላይ የፈሰሰው የጻድቅ ደም ሁሉ ይደርስባችሁ ዘንድ።”
  📖[ማቴዎስ 23፥35]

ኢየሱስ የተናገረው ክስተት በ2 ዜና 24፥20/21ተጠቅሷል ፦

“የእግዚአብሔርም መንፈስ በካህኑ በዮዳሄ ልጅ በዘካርያስ ላይ መጣ፤ እርሱም በሕዝቡ ፊት ቆመና፦ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ የእግዚአብሔርን ትእዛዝ ለምን ትተላለፋላችሁ? መልካምም አይሆንላችሁም፤ እግዚአብሔርን ስለ ተዋችሁ እርሱ ትቶአችኋል አላቸው።”“ተማማሉበትም በንጉሡም ትእዛዝ በእግዚአብሔር ቤት አደባባይ ውስጥ በድንጋይ ወገሩት።”
  📖[2 ዜና 24፥20/21]
በመሰዊያው መካከል ተወግሮ የተገደለው የዮዳሄ ልጅ ዘካርያስ እንጂ የበራክዩ ልጅ ዘካርያስ አደለም በራክዩ ከየዮዳሄ ልጅ ዘካርያስ ሞት ከብዙ ከአስርት ዓመታት በኃላ የኖረ የነቢዩ ዘካርያስ አባት ነው፦

“በዳርዮስ በሁለተኛው ዓመት በስምንተኛው ወር የእግዚአብሔር ቃል ወደ አዶ ልጅ ወደ በራክዩ ልጅ ወደ ነቢዩ ወደ ዘካርያስ እንዲህ ሲል መጣ፦”
 📖[ዘካርያስ 1፥1]

ታዲያ ማቴዎስ ከየት አምጥቶ ነው የበራክዩ ልጅ ዘካርያስ የሚለን?

ስህተት ሦስት ፦ የሌለ ትንቢት እንዳለ አድርጎ መናገሩ፦

“በነቢያት፦ ናዝራዊ ይባላል የተባለው ይፈጸም ዘንድ፥ ናዝሬት ወደምትባል ከተማ መጥቶ ኖረ።”
  📖[ማቴዎስ 2፥23]
ይህ ትንቢት በየትኛውም የነቢያት መጽሐፍ ላይ የለም።
ማቴዎስ ከየት አምጥቶ ነው?

⛳️ተርቡ አሊ


አስታርቁልን ²
ትላትን ግጭት አንድና ሁለት አንስተን ነበር ዛሬ ደሞ ሦስትና አራትን እንመለከታለን፦
ግጭት ሦስት³ ከብሉይ ኪዳን ፦

ምድር መቼ ደረቀች?

በመጀመሪያው ወር ከወሩም በመጀመሪያው ቀን
“በኖኅ ዕድሜ በስድስት መቶ አንድ ዓመት በመጀመሪያው ወር ከወሩም በመጀመሪያው ቀን ውኃው ከምድር ላይ ደረቀ፤ ኖኅም የመርከቢቱን ክዳን አነሣ፥ እነሆም፥ ውኃው ከምድር ፊት እንደ ደረቀ አየ።”
  📖[ዘፍጥረት 8፥13]

ሁለተኛውም ወር ከወሩም በሀያ ሰባተኛው ቀን

“በሁለተኛውም ወር ከወሩም በሀያ ሰባተኛው ቀን ምድር ደረቀች።”
  📖[ዘፍጥረት 8፥14]

ምድር የደረቀቸው መቼ ነው?በመጀመሪያው ወር ከወሩም በመጀመሪያው ቀን ወይስ ሁለተኛውም ወር ከወሩም በሀያ ሰባተኛው ቀን?

ግጭት አራት ⁴ ከአዲስ ኪዳን፦

መስቀሉን የተሸከመው ማነው?

ኢየሱስ ነው

“ኢየሱስንም ይዘው ወሰዱት፤ መስቀሉንም ተሸክሞ በዕብራይስጥ ጎልጎታ ወደ ተባለው የራስ ቅል ስፍራ ወደሚሉት ወጣ።”
  📖[ዮሐንስ 19፥17]

ስምዖን ነው፦
“አንድ መንገድ አላፊም የአሌክስንድሮስና የሩፎስ አባት ስምዖን የተባለ የቀሬና ሰው ከገጠር ሲመጣ መስቀሉን ይሸከም ዘንድ አስገደዱት።”
  📖[ማርቆስ 15፥21]

መስቀሉን የተሸከመው ኢየሱስ ወይም ስምዖን ?

⛳️ተርቡ ዓሊ


አስታርቁልን ¹

ግጭት አንድ¹ ከብሉይ ኪዳን፦
እግዚአብሔር ይጸጸታል ወይስ አይጸጸትምም?

እግዚአብሔር አይጸጸትምም፦

“የእስራኤል ኃይል እንደ ሰው የሚጸጸት አይደለምና አይዋሽም አይጸጸትምም አለው።”
  📖[1ኛ ሳሙኤል 15፥29]

“እግዚአብሔር ለዳዊት በእውነት ማለ አይጸጸትምም።
📖[መዝሙር 132፥11]

“ሐሰትን ይናገር ዘንድ እግዚአብሔር ሰው አይደለም፥ ይጸጸትም ዘንድ የሰው ልጅ አይደለም። እርሱ ያለውን አያደርገውምን? የተናገረውንስ አይፈጽመውምን?”
📖 [ዘኍልቁ 23፥19]

እግዚአብሔር ይጸጸታል፦

“እግዚአብሔርም ሰውን በምድር ላይ በመፍጠሩ ተጸጸተ፥ በልቡም አዘነ።”
  📖[ዘፍጥረት 6፥6]

“ እግዚአብሔርም በእስራኤል ላይ ሳኦልን ስላነገሠ ተጸጸተ።”
  📖[1ኛ ሳሙኤል 15፥35]

“እግዚአብሔርም ስለዚህ ነገር ተጸጸተ።
  📖[አሞጽ 7፥3]

“እግዚአብሔርም ስለዚህ ነገር ተጸጸተ።
  📖[አሞጽ 7፥6]

ጥያቄያችን እግዚአብሔር ይጸጸታል ወይስ አይጸጸትምም?

ግጭት ሁለት ² ከአዲስ ኪዳን፦
ኢየሱስ በቅፍርናሆም በነበረበት ወቅት ቀርቦ ያነጋገረው ማን ነው?

የመቶ አለቃው ራሱ ኢየሱስን ቀርቦ እንዳነጋገረው ይገልጻል፦

“ወደ ቅፍርናሆምም በገባ ጊዜ የመቶ አለቃ ወደ እርሱ ቀርቦ፦ ጌታ ሆይ።
  “ብላቴናዬ ሽባ ሆኖ እጅግ እየተሣቀየ በቤት ተኝቶአል ብሎ ለመነው።”
📖[ማቴዎስ 8፥5/6]
 በሌላ ቦታ የመቶ አለቃው የአይሁድ ሽማግሌዎችን ልኮ ልመናውን እንዳቀረበ ይናገራል፦

“ስለ ኢየሱስም በሰማ ጊዜ የአይሁድን ሽማግሎች ወደ እርሱ ላከና መጥቶ ባሪያውን እንዲያድን ለመነው።”
  📖[ሉቃስ 7፥3]

ጥያቄያችን ኢየሱስ በቅፍርናሆም በነበረበት ወቅት ቀርቦ ያነጋገረው ማን ነው?የመቶ አለቃው ራሱ ወይስ የመቶ አለቃው የአይሁድ ሽማግሌዎችን ልኮ?

⛳️ከተርቡ አሊ


Репост из: ⛳️Ali dawah
ኮራጁ ደምሳሽ

📕[Encyclopaedia Britannica]

ancient Roman #god #of #love in all its varieties, the counterpart of the Greek god Eros and the equivalent of Amor in Latin poetry.

የጥንት የሮማውያን #የፍቅር #አምላክ በሁሉም ዓይነት ዝርያዎች, የግሪክ አምላክ ኤሮስ ተጓዳኝ እና በላቲን ግጥም ውስጥ ከአሞር ጋር ተመሳሳይ ነው።

📉[ቅዱስ ፍቅር መጽሐፍ 08] ገብረአኤልም ከመጣ በዋላም በሚገርም ፍጥነት #የፍቅር #አምላክ  በአይኔ አይቼ የማላውቀውን ሁሉ መንፈስና ድምጽ መስማ ት ጀመርኩኝ በዚህም በህያወቴ ምንም ያክል ሰው ቢያሰምረኝ ሊገብእኝ የማይችለውን መንፈሳዊ ብቃት አላበሰኝ።

ፍቅር ሲዝም ከጣዖታዊያን የተኮረጀ ሐይማኖት ነው ።

📕[Encyclopaedia Britannica]

Eros, in Greek religion, god of love.

ኤሮስ ፣ በግሪክ ሐይማኖት  ፣ የፍቅር አምላክ።
⛳️Ali Da'wah


Репост из: ⛳️Ali dawah
ፍቅር ሲዝም ወይስ ውሸት ሲዝም²?

ትላንት እስከ ቅዱስ ፍቅር መጽሐፍ 03 አይተን ነበር እናም ዛሬ ከ04እንቀጥል፦

04
ከዛም አምላክ አለምን አሳየኝ አለም ላይ ያለው ሰው በሙሉ ሞቶ እኔን ጨምሮ አሳየኝ እኔን አምላክ ራሱ አነሳኝ ከዛም ሌላውን ህዝብ ደግሞ እኔ ሳነሳ አሳየኝ
05
እምነትንም በመንፈስ አማካኘነት ሰጠኝ
06
ይህን ህልም ካሳየኝ በዋላ አምላክ በመቀጠል  ለኔ ያለኝን ነብይነትን በተላያዩ መልኩ ማስተማር ጀመረ ነብዩ መሐመድ በተደጋጋሚ  በህልሜ መተው አስተምረውኛል፡፡

04ላይ ያለውን በደንብ እንመልከት ነጥብ አንድ፦ በመጀመሪያ መጽሐፉ የአምላክ ቃል ነው በመንፈስ ቅዱስ ምሪት ነው የተፃፈው ብሎናል 04ላይ እንዲህ ይላል አምላክ አለምን አሳየኝ ይለናል  አሳየኝ እያለ የሚተርክልን ደምሳሽ ነው ስለዚ የደምሳሽ ንግግር እንጂ የአምላክ አደለም።

ነጥብ ሁለት ፦ አለም በሙሉ ሞቶ ነበር እኔንም ጨምሮ አለ እንግዲህ አንተው ሞተሀል እንጂ አለምንኳን አልሞተም ቀጥሎ አነሳኝ ሌላውንም ህዝብ ሳነሳ አሳየኝ አለ እስኪ አንተን ሳያነሳህ መሞትህን እንዴት አወክ ደምሳሽ?ወይስ ፊልም አይተህ ተኝተህ ደግመህ በህልም ያየኸው ያው ሱሰኛ ነኝ ስላልክ ቪዲዮ ላይም አጨስ እቅም እጠጣ ነበር ብለሀል አይፈረድብህም ያው ሱስ ነው እንደዚ የሚያደርግህ ።

ቁጥር 05ላይ እንቀጥል፦
እምነትንም በመንፈስ አማካኝነት ሰጠኝ ይላል
ነጥብ አንድሰጠኝ ብሎ የሚተርክልን ደምሳሽ ራሱ ነው ስለዚ ቅዱስ ፍቅር መጽሐፍ የፈጣሪ ቃል ሳይሆን የሬጌው ደምሳሽ ነው።

ቁጥር 06 >ነጥብ አንድ ፦ አሁንም እንደ ቅድሙ ይህንንም ህልም ካሳየኝ ቡሀላ የሚለን ጠጪው ደምሳሽ ነው ስለዚ የፈጣሪ ቃል አደለም።

ነጥብ ሁለት፦ለኔ ያለኝን ነብይነት ማስተማር ጀመረ ይለናል ለማነው ያስተማረው? ለደምሳሽ ከተባለ ማስተማር ጀመረ እንጂ ያስተምረኝ ጀመር አይልም ስለዚ የፍቅር አምላክ ያስተማረው ማንን ነው?

ነጥብ ሦስት ፦ ቀጥሎም ነብዩ ሙሐመድ በተደጋጋሚ በህልሜ መተው አስተምረውኛል እያለ በነብያችን ﷺ ላይ ይጥፋል አንደኛ በየትኛውም ዘመን ነብይ ነብይን በህልም መጥቶ አላስተማረም ሲቀጥል ከነብያችን ﷺ
ቡሀላ ነቢይም መልእክተኛም አይመጣም

مَّا كَانَ مُحَمَّدٌ أَبَا أَحَدٍ مِّن رِّجَالِكُمْ وَلَـٰكِن رَّسُولَ اللَّهِ وَخَاتَمَ النَّبِيِّينَ ۗ وَكَانَ اللَّهُ بِكُلِّ شَيْءٍ عَلِيمًا

📗[33፤40 ]
ሙሐመድ ከወንዶቻችሁ የአንድም ሰው አባት አይደለም፡፡ ግን የአላህ መልክተኛና የነቢዮች መደምደሚያ ነው፡፡ አላህም በነገሩ ሁሉ ዐዋቂ ነው፡፡

ነብያችን ﷺ የነቢያት መደምደሚያ ናቸው
እሳቸውም በሐዲስ ላይ እንዲህ ብለዋል፦

📕[Sahih al-Bukhari, Vol. 5, Book 59, Hadith 700]

أَنَّ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم خَرَجَ إِلَى تَبُوكَ، وَاسْتَخْلَفَ عَلِيًّا فَقَالَ أَتُخَلِّفُنِي فِي الصِّبْيَانِ وَالنِّسَاءِ قَالَ ‏"‏ أَلاَ تَرْضَى أَنْ تَكُونَ مِنِّي بِمَنْزِلَةِ هَارُونَ مِنْ مُوسَى إِلاَّ أَنَّهُ لَيْسَ نَبِيٌّ بَعْدِي ‏"‌‏.‏ وَقَالَ أَبُو دَاوُدَ
 
Narrated Sad:
Allah's Messenger (ﷺ)  set out for Tabuk. appointing Ali as his deputy (in Medina). `Ali said, "Do you want to leave me with the children and women?" The Prophet (ﷺ) said, "Will you not be pleased that you will be to me like Aaron to Moses? But there will be no prophet after me."

የአላህ መልእክተኛ”ﷺ” ከተቡክ ወጥተው ዐሊይን በመዲናህ እንዲከተል ሾሙት፤ ዐሊይ፦ “ከህጻናትና ከሴት ጋር ልተወኝ ትፈልጋለህን? አላቸው፤ ነብዩም ልክ አሮን ለሙሴ እንደሆነው አንተ ለእኔ ብትሆን አትደሰትምን? ነገር ግን ከእኔ በኃላ ነብይ የለም*።

ሐዲሱን እንዳነበብነው ከእኔ ቡኃላ ነብይ የለም ብለዋል ደምሳሽ ግን በነብያችን ﷺ ላይ ይቀጥፋል(ይዋሻል) አላህ እንዲህ ይላል፦

وَيْلٌ لِّكُلِّ أَفَّاكٍ أَثِيمٍ

📗[45፤7


Репост из: ⛳️Ali dawah
ሲመረመር part²


Репост из: ⛳️Ali dawah
ፍቅር ሲዝም ወይስ ውሸት ሲዝም¹?

እውን ከነብያችን ﷺ ቡሀላ ነቢይ እና መልእክተኛ  ይመጣልን?
ለሚለው መልሱን 

እኔ ልዳስስ የፈለኩት ፍቅር ሲዝም እውን ትክክለኛ ሐይማኖት  ነውን?የሚለውን ነው።

ቅዱስ ፍቅር የሚል መጽሐፍ አዘጋጅቷል እናም ይህ መጽሐፍ ከፈጣሪ ዘንድ ነው የተሰኝ ይላል እስኪ መጽሐፉ እውን ከፈጣሪ ዘንድ ነው የተሰጠውን የሚለውን እንይ፦

መጽሐፉን ገና ሲከፈት ቅዱስ ፍቅር መጽሐፍ ይላል እናም በመቀጠል አዘጋጅ እና አቅራቢ ነብይ ደምሳሽ ይላል ስሙ ፈገግ ያደርጋል ደምሳሽ ።
በመቀጠልም፦ይህ ቅዱስ መጽሐፍ የፍቅር አምላክ ራሱ እግዚአብሔር መልእክተኞች በዋነኝነት ገብርሄልንና ነብዩ ሙሀመድን ልኮልኝ በመንፈስ ቅዱስ ተፃፈ ።ይላል ቃል በቃል ነው ያስቀመጥኩት መጽሐፉ ላይ ያለውን ስህተት አንድ ገብርኤል ሲፃፍ
ገብርሄል ሳይሆን ገብርኤል ነው እሱ ግን መጽሐፉ ላይ ሲጠቀም ገብርሄል ብሎ ነው ስህተት ሁለት ነብዩ መሀመድ ብሎ በነብያች  ﷺ ላይ ይቀጥፋል በመጀመሪያ ደረጃ ነብያችን ሰው እንጂ መልአክ አደሉም ወሕይ የሚያመጡ የመጀመሪያው ውሸት ገብርኤል እና ነብዩ ሙሀመድ መጽሐፍ ሊያመጡት አይችሉም ገብርኤል መልአክ ነው ነብዩ ﷺ ደግሞ ሰው ናቸው ስለዚ እሳቸው ሞተዋል
ቀጥሎ እንዲህ ይላል፦

የፍቅርት ሀይማኖት መመርያ
መጽሀፍ
ፍቅር ሀይማኖት ማለት ሰዎች በፍቅር እርስ በእርስ ተዋደው እና ተከባብረው የሚኖሩ በት  ህግ ነው።

ይህ ህግ  እና ትህዛዝ የመጣው በመንፈስ ቅዱስ አማካኝነት ከፍቅር አምላክ ከእግዜብሄር ነው በአምላክ  መልክተኛ ነብይ ደምሳሽ በሀይሉ፡፡

በመጀመሪያ የአምላክ ቃል ነው ብሎ ካለ ይህ ሁሉ የሱ ቃል ምን ይሰራል?ቀጥሎ እንዲህ ይላል፦

01
2000 አ።ም ተጀመረ የአምላክ መንፈስ ተባርኮ ለሰው ልጆች ወደ ምድር  በመንፈስ አማካኝነት  ወረደ
በመጀመርያ ተኝቼ ነበር ከዛም በፊት ምንም ህልም አይቼም አምኜም አላውቅም  እናም አንድ ቀን በህየወቴ አይቼውና ሰምቼው የማላውቀውን ህልም አይው፡፡
02
ህልሙም ከሰማይ የመጣ ትልቅና አስፈሪ ደምጽ  የእግዜአብሄር ተህዛዝ ነበር
03
እሱም   ደምሳሸ ነብይ አድርጌ መርጬሀለው ነበር ያለኝ
እኔም አልፈልግም አልኩት መሆን የምፈልገው መንግስት ነው አልኩት በዛ ላይ በጣም ሱሰኛ ነኝ በዚህም ምክንያት  ነብይ መሆን አልችልም ድግሞስ ከዚህ ሁሉ ሰው ነብይ ጠፍቶ ነው ወይ አልኩት የፍቅር አምላክም ከለከለኝ
ዛሬ በእነዚህ አንቀጽ ላይ ብቻ እናውራ፦

ቅዱስ ፍቅር 01ላይ እደንህ ይላል 2000አ።ም ይላል ዓመተ ምህረት ለማለት ፈለጎ ነው ግን ዓመተ ምህረት ለመፃፍ ዓ.ም እንጂ አ።ም አደለም  መንፈስ ቅዱስ ነው ወይስ ደምሳሽ የተሳሳተው?
እቀጥል እዛው 01ላይ በ2000  እንደተጀመረ ይናገራል 2000በፊት የፍቅር አምላክ የለም ማለት ነው ምክንያቱም ተጀመረ እንጂ የነበረ ወይም ጠፍቶ አሁን የተነሳ አይደለም የተጀመረው በ2000ድህረ-ልደት ነው ስለዚ አምላክ ከ2000 በፊት የነበረ እንጂ በ2000የጀመረ ህልውና የለውም አምላክ አለም ሳይፈጠር ነበር አሁንም አለ እንቀጥል በመቀጠል እዛው01ላይ በመጀመርያ ተኝቼ ነበር ከዛም በፊት ምንም ህልም አይቼም አምኜም አላውቅም  እናም አንድ ቀን በህየወቴ አይቼውና ሰምቼው የማላውቀውን ህልም አይው፡፡

ነጥብ አንድ ፦ተኝቼ የሚለው ማነው?ደምሳሽ ከሆነ ቃሉ የደምሳሽ እንጂ የፈጣሪ አደለም።

ነጥብ ሁለት ፦አይቼም አምኜም አላውቅም
አምኜ አላውቅም ካለ ይህንን ለምን አመነ?
ምክንያቱም አምኖ አያውቅምና ።

ነጥብ ሦስት፦የፊደል ስህተት ይህ የኮፒውተር ችግር ነው እንዳይባል በገፍ ነው ያለው ስለዚ ከዚህ ስህተት ውስጥ አንዱ" በህይወቴ" እንጂ "በህየወቴ" አይባልም አየሁ እንጂ አይው አይደለም ።
ቅዱስ ፍቅር 02እንይ፦ህልሙም ከሰማይ የመጣ ትልቅና አስፈሪ ደምጽ  የእግዜአብሄር ተህዛዝ ነበር

ህልሙ እነደዚ ነበር ብሎ የሚተርክልን ደምሳሽ ነው ስለዚ ይህ የሱ ህልም እንጂ የፈጣሪ ቃል አደለም።
ቀጥሎ 03ላይ እንዲህ ይላል፦እሱም   ደምሳሸ ነብይ አድርጌ መርጬሀለው ነበር ያለኝ
እኔም አልፈልግም አልኩት መሆን የምፈልገው መንግስት ነው አልኩት በዛ ላይ በጣም ሱሰኛ ነኝ በዚህም ምክንያት  ነብይ መሆን አልችልም ድግሞስ ከዚህ ሁሉ ሰው ነብይ ጠፍቶ ነው ወይ አልኩት የፍቅር አምላክም ከለከለኝ

ነጥብ አንድ ፦ያለኝ እያለ የሚነግረን ደምሳሽ ነው አልፈልግም አልኩት የሚለን ደምሳሽ ነው
መንግስት መሆን ነው የምፈልገው አለኩ እያለ የሚነግረን ደምሳሽ ነው ስለዚህ ይህ ገብርኤል ወይም በሱ ቋንቋ ገብርሄል አደለም ያወረደለት እራሱ በንቅልፉ ያየውን ቅዠት ነው የሚነግረን።

ነጥብ ሁለት፦አንድን ሰው ነቢይ ኹን ቢባል እንቢ የሚል ሰው አለ?ያውም ቃሚ እና አጫሽ የሰፈር ዱሩዬ እንኳን ነቢይ ኹን ተብሎ ይኸው ሳይሆን ሆንኩ ብሎ እየዋሸ አይደል ሲቀጥል መንግስት መሆን ነው ፍላጎቱ ለዛም ነው ብልጽግናን የሚደግፈው ቀጥሎም ሱሰኛ ነኝ ይላል ሱስ ደሞ ብዙ ነገር ውስጥ ይከታል ለዚህም ነው ያልሆነ ነገር ውስጥ የገባው
ቀጥሎ ከሰው ሁሉ ነቢይ ጠፍቶ ነው እኔን ነቢይ ያደረከኝ ወይ ብሎ ይጠቀዋል ስለዚ እራሱ እንደመሰከረው ነቢይ ለመሆን ብቁ አደለም ማለት ነው።

ነጥብ ሦስት ፦ቀጥሎም ከለከለኝ ይላል ምን አድርጎ ነው የሚከለክለው አልፈልግም ስላለ?አው ከሆነ የፍቅር አምላክ ያስገድዳል ማለት ነው የፍቅር አምላክ አደለም ማለት ነው ምክንያቱም እሱን አስገድዶ ነቢይ ካረገ እኛንም አስገድዶ ምን እንደሚደገን አናቅም ።

مَّا كَانَ مُحَمَّدٌ أَبَا أَحَدٍ مِّن رِّجَالِكُمْ وَلَـٰكِن رَّسُولَ اللَّهِ وَخَاتَمَ النَّبِيِّينَ ۗ وَكَانَ اللَّهُ بِكُلِّ شَيْءٍ عَلِيمًا

📗[33፤40 ]
ሙሐመድ ከወንዶቻችሁ የአንድም ሰው አባት አይደለም፡፡ ግን የአላህ መልክተኛና የነቢዮች መደምደሚያ ነው፡፡ አላህም በነገሩ ሁሉ ዐዋቂ ነው፡፡

ለዛሬ እዚው ላብቃ ።

ይቀጥላል .........................
⛳️ከ
ተርቡ

Показано 20 последних публикаций.

443

подписчиков
Статистика канала