Репост из: "ቤተ ማርያም መንፈሳዊ ሚዲያ💒
🌹ወር በገባ በ 25/ታስባ የምትውለው ቅድስት ቴክላ ሐዋርያዊት ☑የሕሙማን እናት የተባለችው ሐምሌ 25 ያረፈችው በብዙ ሊቃውንት የተወደሰችው የቅድስት ቴክላ ድንቅ ታሪክ +
❖ በመጀመሪያው መቶ ክፍለ ዘመን የነበረችው ብዙዎች አበው በድርሳናቸው የመሰከሩላትን በድንግልናዋ ጸንታ የኖረችውን ቅድስት ቴክላ ናት፤ ይኽቺ ቅድስት ሴት፤ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስን ከተከተሉት ቅዱሳን ሴቶች አንዷ ስትኾን እጅግ ውብ፣ ሀብታምና የተማረች ነበረች ፤ በዚኽም ከልዑላኑ ታሚሪስ የሚባል ወጣት ሰው አጭቷት ነበር፤ ቅዱስ ጳውሎስ በ45 ዓ.ም. ከአንጾኪያ ከተማ ወደ ኒቆምድያ ከተማ ኼዶ ወንጌልን ሲሰብክ በተመስጦ ኾና ትምህርቱን ትከታተል እንደነበር ከሊቃውንት ቅዱስ አምብሮስና ቅዱስ አውግስጢኖስ ጽፈዋል።
❖ በሐዋርያውም ትምህርት ልቧ በመነካቱ የድንግልና ሕይወትን በመምረጥ ለእናቷ የታሚሪስ እጮኝነቷን ማፍረሷንና ክርስቲያን እንደምትኾን ነገረች፤ ወላጆቿ ግን ርሱን እንዳትሰማ ቢያግባቧትም ርሷ ግን እነርሱን አልሰማቻቸውም፤ በዚኽ ምክንያት አባቷ ዲማኖስና ርምጋኖስ ከሚባሉ ዳኞች ኺዶ ከሰሳት፤ እነርሱም ሊያስገድዷ ቢሞክሩም አልቻሉም፤ ከዚያም የቀደመ ልብሷንና ጌጦቿን ኹሉ ትታ ከቅዱስ ጳውሎስ ጉባኤ ተቀመጠች፡፡
❖ በዚኽ ተበሳጭተው በመኰንኑ ዘንድ እንደገና ከሰዋት፤ ርሱም ሌሎቹ ፈርተው ወደ ቅዱስ ጳውሎስ እንዳይኼዱ በእሳት እንዲያቃጥሏት አዘዘ፤ ርሷ ግን በሚያቃጥሏት ጊዜ ልቧን አጽንታ ቅዱስ ጳውሎስን ተመለከተችው፤ ያን ጊዜ ሐዋርያው በመስቀል ምልክት ባማተበ ጊዜ ወደ እሳቱ ምድጃ ተወረወረች፡፡
✍️ “ፈነወ እግዚአብሔር ዝናመ ብዙኀ ወበረደ ወመብረቀ ወኮነ ዕቶነ እሳት ከመ ጠል ቈሪር ወሮጸት ቴክላ ወበጽሐት ኀበ ቅዱስ ጳውሎስ ኀበ ኀሎ መካነ ኅቡአ” ይላል፤
❖ ያን ጊዜ እግዚአብሔር ብዙ ዝናብን፣ በረድን፣ መብረቅን ላከ፤ የእሳቱም ምድጃ እንደ ቀዝቃዛ ጠል ኾነ፤ ቴክላም ሩጣ ቅዱስ ጳውሎስ ተሰዉሮ ወደ አለበት ቦታ በመድረስ፤ ወንጌልን ለመማር በኼደበት ኹሉ ትከተለው ዘንድ ለመነችው፡፡
❖ ከዚያም ከርሱ ጋር አንጾኪያ ከተማ በመኼድ ለዐዲስ አማኞች የእግዚአብሔርን ቃል ትነግራቸው ነበር፤ ከመልኳ ውበትም የተነሣ ከመኳንንቶቹ አንዱ ሊአገባት ፈለገ፤ ርሷ ግን ዘለፈችው፤ ከዚያም ለአንበሶች እንድትጣል ቢደረግም ልክ እንደ ነቢዩ ዳንኤል አንበሶቹ ሳይነኳት በነርሱ መኻከል ኹለት ቀናት ቆየች፤ ከዚኽም በኋላ በኹለት በሬዎች መኻከል አስረው በከተማው ውስጥ አስጐተቷት፤ ነገር ግን ምንም ክፉ ነገር አልደረሰባትም፤ ከዚያም በኋላ ለቀቁዋት፡፡
❖ ርሷም ወደ ቅዱስ ጳውሎስ ኼደች ርሱም አጽንቶና አረጋግቶ የሰማችውን እንድትመሰክር አዘዛት፡፡ ርሷም ወደ ወላጆቿ ሀገር በመኼድ ስለ ክርስቶስ መሰከረች፤ አባትና እናቷም አምነው ክርስቲያን ኾኑ፤ ሀብተ ፈውስም ተሰጥቷት ብዙዎችን ትፈውሳቸው ነበር በዚኽም “የሕሙማን እናት” በመባል ትታወቃለች፤ በመጨረሻም ተጋድሎዋን ፈጽማ ሐምሌ 25 ዐረፈች፤ መስከረም 27 ትታሰባለች፤ ሥጋዋም በግብጽ ደቡብ ሰንጋር በሚባል ቦታ ተቀመጠ፤ በዚያም ከሥጋዋ የተነሣ ብዙ ድንቅ ተአምር ተገልጧል፡፡
❖ በርካቶች ቅዱሳን አበው በየድርሳናቸው የቅድስት ቴክላን ቅድስናና ተጋድሎ ጽፈውላታል፤ በተለይ ቅዱስ ሜቶዲየስ ቅድስት ቴክላ ከቅዱስ ጳውሎስ በተማረችው ትምህርት ምን ያኽል ጠንካራ እንደነበረች፤ በጊዜው ከነበሩት የደናግል ኅብረት ከፍ ከፍ ያለች፤ ድንግልናቸውን ጠብቀው እንዲኖሩ በዝማሬም ትመራቸው እንደነበር ይገልጣል ፡፡
❖ ሊቁ ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅም ስለ ርሷ ክብር ሲጽፍላት የተባረከች ድንግል ቴክላ ንጽሕናዋን ሰማዕትነቷን ለልዑል እግዚአብሔር በማቅረብ በአንድ እጇ በሥጋው በደማዊ ፈቃድ ላይ የድል ዘውድን ስትይዝ፤ በሌላኛው እጇ በአደገኛ ሥቃይና መከራ ላይ የክብር አክሊሏን እንደያዘች ዐውቃለኊ ብሏል፡፡
❖ ቅዱስ ጀሮምም በደብዳቤው ላይ “የጌታ እናት ቅድስት ድንግል ማርያም የደናግልን ማኅበር አስከትላ እናንተን ለመገናኘት የምትመጣባት የዚያቺ ቀን ክብር እንደምን ያለ ነው!... ያን ጊዜ ቴክላ እናንተን ለማቀፍ በደስታ ትበርራለች ብሏል፡፡
❖ ቅዱስ ሳዊሮስ ዘአንጾኪያም የድንግልና ሕይወቷን አብነት እንዲያደርጉ ሲያስተምር
✍️“የንጽሕና አምሳል ከምትኾን ወደር ከሌላት ከአምላክ እናት በመቀጠል ከሴቶች አስቀድማ ሰማዕት የኾነች ቴክላን ምሳሌ አድርጌ አነሣለኊ፤ እናንተም የርሷን መንፈሳዊ ውበት ተላብሳችኊ ሰማያዊ ጸጋን ለማግኘት ነፍሳኹን በተለያዩ መንፈሳዊ መልካሞች ሥራዎች ታስጌጧት ዘንድ ይገባል” በማለት አስተምሯል፡፡
❖ ኢትዮጵያዊዉ ሊቅ አርከ ሥሉስም ተጋድሎዋን በማዘከር
✍️“ሰላም እብል ለሐዋርያዊት ቴክላ እግዚአብሔር ዘአኀየላ ኢያቊስልዋ አናብስት ወእሳተ ዕቶን ኢያሕልላ እስመ አምነት ትምህርተ ጽድቅ ከመ ጳውሎስ ይቤላ እስከኀደገት አበዊሃ ወገደፈት ብዕላ”
👉አንበሶች እንዳያቈስሏት የእሳት ምድጃም እንዳያቃጥላት እግዚአብሔር ያበረታት ሐዋርያዊት ለኾነች ለቴክላ ሰላምታ ይገባል፤ አባቶቿን እስክትተውና ሀብቷን እስክትጥል ድረስ ደርሳ ጳውሎስ እንዳላት የእውነት ትምህርትን አምናለችና እያለ የተቀደሰ ሕይወቷን በአድናቆት ጽፎላታል፡፡
❖ ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫም በተአምኆ ቅዱሳን መጽሐፉ ላይ
✍️“ሰላም ለጤቅላ (ቴክላ) ዘሞአቶ ለተኲላ በገድል ንጽሕት ድንግል”
👉ንጽሕት ድንግል በገድል ተኲላውን ያሸነፈችው ለኾነች ለጤቅላ ሰላምታ ይገባል)እያለ ያወድሳታል።
የቅድስት ቴክላ በረከት ረድኤት ይደርብን
https://t.me/zikirekdusn
ምንጭ ገብረ ክርስቶስ መርዓዊ አቡየ
❖ በመጀመሪያው መቶ ክፍለ ዘመን የነበረችው ብዙዎች አበው በድርሳናቸው የመሰከሩላትን በድንግልናዋ ጸንታ የኖረችውን ቅድስት ቴክላ ናት፤ ይኽቺ ቅድስት ሴት፤ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስን ከተከተሉት ቅዱሳን ሴቶች አንዷ ስትኾን እጅግ ውብ፣ ሀብታምና የተማረች ነበረች ፤ በዚኽም ከልዑላኑ ታሚሪስ የሚባል ወጣት ሰው አጭቷት ነበር፤ ቅዱስ ጳውሎስ በ45 ዓ.ም. ከአንጾኪያ ከተማ ወደ ኒቆምድያ ከተማ ኼዶ ወንጌልን ሲሰብክ በተመስጦ ኾና ትምህርቱን ትከታተል እንደነበር ከሊቃውንት ቅዱስ አምብሮስና ቅዱስ አውግስጢኖስ ጽፈዋል።
❖ በሐዋርያውም ትምህርት ልቧ በመነካቱ የድንግልና ሕይወትን በመምረጥ ለእናቷ የታሚሪስ እጮኝነቷን ማፍረሷንና ክርስቲያን እንደምትኾን ነገረች፤ ወላጆቿ ግን ርሱን እንዳትሰማ ቢያግባቧትም ርሷ ግን እነርሱን አልሰማቻቸውም፤ በዚኽ ምክንያት አባቷ ዲማኖስና ርምጋኖስ ከሚባሉ ዳኞች ኺዶ ከሰሳት፤ እነርሱም ሊያስገድዷ ቢሞክሩም አልቻሉም፤ ከዚያም የቀደመ ልብሷንና ጌጦቿን ኹሉ ትታ ከቅዱስ ጳውሎስ ጉባኤ ተቀመጠች፡፡
❖ በዚኽ ተበሳጭተው በመኰንኑ ዘንድ እንደገና ከሰዋት፤ ርሱም ሌሎቹ ፈርተው ወደ ቅዱስ ጳውሎስ እንዳይኼዱ በእሳት እንዲያቃጥሏት አዘዘ፤ ርሷ ግን በሚያቃጥሏት ጊዜ ልቧን አጽንታ ቅዱስ ጳውሎስን ተመለከተችው፤ ያን ጊዜ ሐዋርያው በመስቀል ምልክት ባማተበ ጊዜ ወደ እሳቱ ምድጃ ተወረወረች፡፡
✍️ “ፈነወ እግዚአብሔር ዝናመ ብዙኀ ወበረደ ወመብረቀ ወኮነ ዕቶነ እሳት ከመ ጠል ቈሪር ወሮጸት ቴክላ ወበጽሐት ኀበ ቅዱስ ጳውሎስ ኀበ ኀሎ መካነ ኅቡአ” ይላል፤
❖ ያን ጊዜ እግዚአብሔር ብዙ ዝናብን፣ በረድን፣ መብረቅን ላከ፤ የእሳቱም ምድጃ እንደ ቀዝቃዛ ጠል ኾነ፤ ቴክላም ሩጣ ቅዱስ ጳውሎስ ተሰዉሮ ወደ አለበት ቦታ በመድረስ፤ ወንጌልን ለመማር በኼደበት ኹሉ ትከተለው ዘንድ ለመነችው፡፡
❖ ከዚያም ከርሱ ጋር አንጾኪያ ከተማ በመኼድ ለዐዲስ አማኞች የእግዚአብሔርን ቃል ትነግራቸው ነበር፤ ከመልኳ ውበትም የተነሣ ከመኳንንቶቹ አንዱ ሊአገባት ፈለገ፤ ርሷ ግን ዘለፈችው፤ ከዚያም ለአንበሶች እንድትጣል ቢደረግም ልክ እንደ ነቢዩ ዳንኤል አንበሶቹ ሳይነኳት በነርሱ መኻከል ኹለት ቀናት ቆየች፤ ከዚኽም በኋላ በኹለት በሬዎች መኻከል አስረው በከተማው ውስጥ አስጐተቷት፤ ነገር ግን ምንም ክፉ ነገር አልደረሰባትም፤ ከዚያም በኋላ ለቀቁዋት፡፡
❖ ርሷም ወደ ቅዱስ ጳውሎስ ኼደች ርሱም አጽንቶና አረጋግቶ የሰማችውን እንድትመሰክር አዘዛት፡፡ ርሷም ወደ ወላጆቿ ሀገር በመኼድ ስለ ክርስቶስ መሰከረች፤ አባትና እናቷም አምነው ክርስቲያን ኾኑ፤ ሀብተ ፈውስም ተሰጥቷት ብዙዎችን ትፈውሳቸው ነበር በዚኽም “የሕሙማን እናት” በመባል ትታወቃለች፤ በመጨረሻም ተጋድሎዋን ፈጽማ ሐምሌ 25 ዐረፈች፤ መስከረም 27 ትታሰባለች፤ ሥጋዋም በግብጽ ደቡብ ሰንጋር በሚባል ቦታ ተቀመጠ፤ በዚያም ከሥጋዋ የተነሣ ብዙ ድንቅ ተአምር ተገልጧል፡፡
❖ በርካቶች ቅዱሳን አበው በየድርሳናቸው የቅድስት ቴክላን ቅድስናና ተጋድሎ ጽፈውላታል፤ በተለይ ቅዱስ ሜቶዲየስ ቅድስት ቴክላ ከቅዱስ ጳውሎስ በተማረችው ትምህርት ምን ያኽል ጠንካራ እንደነበረች፤ በጊዜው ከነበሩት የደናግል ኅብረት ከፍ ከፍ ያለች፤ ድንግልናቸውን ጠብቀው እንዲኖሩ በዝማሬም ትመራቸው እንደነበር ይገልጣል ፡፡
❖ ሊቁ ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅም ስለ ርሷ ክብር ሲጽፍላት የተባረከች ድንግል ቴክላ ንጽሕናዋን ሰማዕትነቷን ለልዑል እግዚአብሔር በማቅረብ በአንድ እጇ በሥጋው በደማዊ ፈቃድ ላይ የድል ዘውድን ስትይዝ፤ በሌላኛው እጇ በአደገኛ ሥቃይና መከራ ላይ የክብር አክሊሏን እንደያዘች ዐውቃለኊ ብሏል፡፡
❖ ቅዱስ ጀሮምም በደብዳቤው ላይ “የጌታ እናት ቅድስት ድንግል ማርያም የደናግልን ማኅበር አስከትላ እናንተን ለመገናኘት የምትመጣባት የዚያቺ ቀን ክብር እንደምን ያለ ነው!... ያን ጊዜ ቴክላ እናንተን ለማቀፍ በደስታ ትበርራለች ብሏል፡፡
❖ ቅዱስ ሳዊሮስ ዘአንጾኪያም የድንግልና ሕይወቷን አብነት እንዲያደርጉ ሲያስተምር
✍️“የንጽሕና አምሳል ከምትኾን ወደር ከሌላት ከአምላክ እናት በመቀጠል ከሴቶች አስቀድማ ሰማዕት የኾነች ቴክላን ምሳሌ አድርጌ አነሣለኊ፤ እናንተም የርሷን መንፈሳዊ ውበት ተላብሳችኊ ሰማያዊ ጸጋን ለማግኘት ነፍሳኹን በተለያዩ መንፈሳዊ መልካሞች ሥራዎች ታስጌጧት ዘንድ ይገባል” በማለት አስተምሯል፡፡
❖ ኢትዮጵያዊዉ ሊቅ አርከ ሥሉስም ተጋድሎዋን በማዘከር
✍️“ሰላም እብል ለሐዋርያዊት ቴክላ እግዚአብሔር ዘአኀየላ ኢያቊስልዋ አናብስት ወእሳተ ዕቶን ኢያሕልላ እስመ አምነት ትምህርተ ጽድቅ ከመ ጳውሎስ ይቤላ እስከኀደገት አበዊሃ ወገደፈት ብዕላ”
👉አንበሶች እንዳያቈስሏት የእሳት ምድጃም እንዳያቃጥላት እግዚአብሔር ያበረታት ሐዋርያዊት ለኾነች ለቴክላ ሰላምታ ይገባል፤ አባቶቿን እስክትተውና ሀብቷን እስክትጥል ድረስ ደርሳ ጳውሎስ እንዳላት የእውነት ትምህርትን አምናለችና እያለ የተቀደሰ ሕይወቷን በአድናቆት ጽፎላታል፡፡
❖ ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫም በተአምኆ ቅዱሳን መጽሐፉ ላይ
✍️“ሰላም ለጤቅላ (ቴክላ) ዘሞአቶ ለተኲላ በገድል ንጽሕት ድንግል”
👉ንጽሕት ድንግል በገድል ተኲላውን ያሸነፈችው ለኾነች ለጤቅላ ሰላምታ ይገባል)እያለ ያወድሳታል።
የቅድስት ቴክላ በረከት ረድኤት ይደርብን
https://t.me/zikirekdusn
ምንጭ ገብረ ክርስቶስ መርዓዊ አቡየ