Репост из: EFDA የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን
ዓለም አቀፍ የፀረ - ተህዋስያን መድኃኒቶች በጀርሞች መለመድ የግንዛቤ ማስጨበጫ የፓናል ውይይት ተካሄደ
ህዳር 12/2017 አዲስ አበባ፡ የጤና ሚኒስቴርና የግብርና ሚኒስቴር ከአጋር አካላት ጋር በጋራ ያዘጋጁት የፓናል ውይይት ላይ በመገኘት የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ እንደተናገሩት የፀረ - ተህዋስያን መድኃኒቶች በጀርሞች መለመድ ዓለም አቀፋዊ ችግር መሆኑን በመግለፅ ለችግሩ ዓለም አቀፋዊ መፍትሄም ያስፈልጋል ያሉ ሲሆን ኢትዮጵያ የችግሩ አንድ አካል እንደመሆኗ በርካታ ህዝብ ጉዳት ላይ ከመውደቁም በተጨማሪ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጫና መፍጠሩን ገልፀው የሀገራችንን ህዝብ ግንዛቤ ለመጨመር በርካታ ስራዎች መሰራታቸውን አስታውቀዋል፡፡
የአፍሪካ ሲዲሲን ወክለው በፓናል ውይይቱ ላይ የተገኙት ዶከተር የዋንዴ አሊሚ በበኩላቸው የተባበሩት መንግስታት የፖለቲካል ዴክላሬሽንና የአፍሪካ ህብረትን አቋም ከፀረ - ተህዋስያን መድኃኒቶች በጀርሞች መለመድ አንፃር ፅሁፍ ያቀረቡ ሲሆን እንደዶክተር የዋንዴ ገለፃ ከሆነ አፍሪካ የችግሩ ግንባር ቀደም ተጠቂ ብትሆንም ተገቢው ድጋፍ እየተደረገት አይደለም ብለዋል፡፡ በፓናል ውይይቱ ከአለም ጤና ድርጅት የተገኙ ፅሁፍ አቅራቢዎቸ ጥናታዊ ፅሁፋቸውን ካቀረቡ በኋላ ሠፊ ውይይት ተደርጎ መድረኩ ተጠናቋል፡፡
ህዳር 12/2017 አዲስ አበባ፡ የጤና ሚኒስቴርና የግብርና ሚኒስቴር ከአጋር አካላት ጋር በጋራ ያዘጋጁት የፓናል ውይይት ላይ በመገኘት የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ እንደተናገሩት የፀረ - ተህዋስያን መድኃኒቶች በጀርሞች መለመድ ዓለም አቀፋዊ ችግር መሆኑን በመግለፅ ለችግሩ ዓለም አቀፋዊ መፍትሄም ያስፈልጋል ያሉ ሲሆን ኢትዮጵያ የችግሩ አንድ አካል እንደመሆኗ በርካታ ህዝብ ጉዳት ላይ ከመውደቁም በተጨማሪ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጫና መፍጠሩን ገልፀው የሀገራችንን ህዝብ ግንዛቤ ለመጨመር በርካታ ስራዎች መሰራታቸውን አስታውቀዋል፡፡
የአፍሪካ ሲዲሲን ወክለው በፓናል ውይይቱ ላይ የተገኙት ዶከተር የዋንዴ አሊሚ በበኩላቸው የተባበሩት መንግስታት የፖለቲካል ዴክላሬሽንና የአፍሪካ ህብረትን አቋም ከፀረ - ተህዋስያን መድኃኒቶች በጀርሞች መለመድ አንፃር ፅሁፍ ያቀረቡ ሲሆን እንደዶክተር የዋንዴ ገለፃ ከሆነ አፍሪካ የችግሩ ግንባር ቀደም ተጠቂ ብትሆንም ተገቢው ድጋፍ እየተደረገት አይደለም ብለዋል፡፡ በፓናል ውይይቱ ከአለም ጤና ድርጅት የተገኙ ፅሁፍ አቅራቢዎቸ ጥናታዊ ፅሁፋቸውን ካቀረቡ በኋላ ሠፊ ውይይት ተደርጎ መድረኩ ተጠናቋል፡፡