" 10ኛ ክፍል ላይ ሀገር አቀፍ ፈተና ሳይወስዱ ወደ 11 የተዘዋወሩ ተማሪዎች ልዩ የማካካሻ ትምህርት ሊሰጣቸው ይገባል፣ ካልሆነ ግን መውደቅ ይቀጥላል " - ትምህርት ሚኒስቴር
ትምህርት ሚኒስቴር ወደ ዩኒቨርስቲ የሚገቡ ተማሪዎች ቁጥር በየጊዜው በከፍተኛ ሁኔታ እየቀነሰ መሆኑን ተከትሎ አካሄድኩት ባለው እና ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባቀረበው ጥናት ዘርፈ ብዙ ችግሮች መገኘታቸውን ገልጿል።
የትምህርት ዘርፍ ሪፎርም ከተካሄደ በኋላ ትምህርት ቤቶች ማስተማር ከሚችሉት በላይ ተማሪዎችን ያስተምራሉ ያለ ሲሆን ከዚህ በፊት 10ኛ ክፍል ይሰጥ የነበረውን ፈተና በመቅረቱ ሳይፈተኑ 11ኛ ክፍል መግባታቸው ለችግሩ ዋና ተጠቃሽ ምክንያት መሆኑን አመላክቷል።
በትምህርት ቤቶች በሚሰጠው የሞዴል ፈተና እና ትምህርት ሚኒስቴር በሚሰጠው የሀገር አቀፍ ፈተና ሰፊ ልዩነት እንዳለውም ገልጿል።
" በማህበራዊ እና በተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች መካከል የማለፍ ንፅፅር ሲታይ ልዩነት አለ " ያለው ሚኒስቴሩ " የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች የተሻለ ውጤት በማምጣት ወደ ከፍተኛ ተቋም ይገባሉ፣ ይሁን እንጂ በቂ አይደለም፣ ብዙ ነገሮች መሻሻል እንዳለባቸው ጥናቱ አሳይቶናል " ብሏል።
ጥናቱ ምን አይነት የትምህርት ዘርፍ ችግር ነው ይሄን ያክል ውድቀት ያመጣብን ፣ ከተማሪዎች መውደቅ እና ማለፍ ጋር ተያይዞ የትምህርቱ ባህሪ ምንድን ነው የሚለውን እና በአጠቃላይ በትምህርት ዘርፉ ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን የያዘ ነው።
በሁሉም የትምህርት ዘርፍ ላይ ያሉ ችግሮችን ያሳየው ይሄ ጥናት በመጨረሻም የመፍትሄ ሃሳቦችንም አቅርቧል።
ትምህርት ሚኒስቴር ምን የመፍትሄ ሃሳብ አቀረበ ?
" ከዚህ በፊት 10ኛ ክፍል ላይ ይሰጥ የነበረውን ሀገራዊ ፈተና ሳይወስዱ 11ኛ ክፍል የሚማሩ ተማሪዎች ልዩ የማካካሻ ፕሮግራም ያስፈልጋቸዋል። ይሄ ካልሆነ ግን መውደቅ ይቀጥላል ፣ ምክንያቱ የሚፈለገውን ያህል እውቀት እና ክህሎት ይዘው አይወጡም።
በገጠር በተለይም በአርብቶ አደሮች አካባቢዎች ላይ ያለው የትምህርት ዘርፍ ልማት አነስተኛ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ እጅግ ወደ ኋላ እየቀረ ስለሆነ ማካካሻ መሰራት አለበት።
ሌላው ደግሞ ከትምህርት አመራር፣ መምህራን እና ከአቅም ግንባታ ጋር ተያይዞ ያሉ ጉዳዮች ውጤት በሚያመጡ ጉዳዮች ላይ ብቻ ትኩረት ተደረጎ የትምህርት አመራሩ አቅም እስካልሰጠ ችግሮቹ ይቀጥላሉ።
ለመምህራን የደመወዝ ጭማሪ ብቻ ሳይሆን መምህሮችን የሚያቅፍ የ insensitive package እስካልመጣ ድረስ ችግሮቹ ይባባሳሉ።
በተጨማሪም በሀብት ክፍፍል ላይ ክፍተት በመኖሩ በትምህርት ዘርፉ ልማት ላይ ተግዳሮት መኖሩን ያሳያል፣ ይሄም መፈታት አለበት " ሲል መፍትሄ ያለውን ሃሳብ አቅርቧል።
ትምህርት ሚኒስቴር ጥናቱን ባቀረበበት ወቅት የህዝብ ተወካዮች የተለያዩ አስተያየቶች፣ ጥያቄዎች እና ሃሳቦችን አቅርበዋል።
በጥናቱ ላይ የመፍትሄ ሃሳቦች መቅረባቸው ጥሩ ሁነው ሳለ እንደዚሁ ተወርተው መሬት ላይ ሳይወርዱ ከቀሩ ትርጉም አልባ ናቸው፣ በመሆኑም ሁሉም በአፅንኦት ሊመለከተው እንደሚገባ በተወካዮች ተጠቁሟል።
ከ1 እስከ 8ኛ ክፍል ላሉ ተማሪዎች የሚደረገው ድጋፍ አነስተኛ ነው፣ ይሄም አሁን ላለንበት ውጤት ማጣት ትልቁን ድርሻ ይወስዳል ፤ በጥናቱስ ላይ ለምን ይሄ ሳይካተት ቀረ፣ ምክንያቱም የትምህርት መሰረቱ ከታች ጀምሮ ስለሆነ የሚሉ ጥያቄዎች ተነስቷል።
የተለያዩ ተማሪዎች በህገወጥ መንገድ ወደተለያዩ ሀገሮች እየተሰደዱ ነው፣ ተማሪዎች ይሄ ሲፈጠር ተረጋግተው መማር እየቻሉ አይደለም፣ ትምህርት ሚኒስቴር ትኩረት ሊሰጠው ይገባል ተብሏል።
👍 @QesemAcademy
ትምህርት ሚኒስቴር ወደ ዩኒቨርስቲ የሚገቡ ተማሪዎች ቁጥር በየጊዜው በከፍተኛ ሁኔታ እየቀነሰ መሆኑን ተከትሎ አካሄድኩት ባለው እና ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባቀረበው ጥናት ዘርፈ ብዙ ችግሮች መገኘታቸውን ገልጿል።
የትምህርት ዘርፍ ሪፎርም ከተካሄደ በኋላ ትምህርት ቤቶች ማስተማር ከሚችሉት በላይ ተማሪዎችን ያስተምራሉ ያለ ሲሆን ከዚህ በፊት 10ኛ ክፍል ይሰጥ የነበረውን ፈተና በመቅረቱ ሳይፈተኑ 11ኛ ክፍል መግባታቸው ለችግሩ ዋና ተጠቃሽ ምክንያት መሆኑን አመላክቷል።
በትምህርት ቤቶች በሚሰጠው የሞዴል ፈተና እና ትምህርት ሚኒስቴር በሚሰጠው የሀገር አቀፍ ፈተና ሰፊ ልዩነት እንዳለውም ገልጿል።
" በማህበራዊ እና በተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች መካከል የማለፍ ንፅፅር ሲታይ ልዩነት አለ " ያለው ሚኒስቴሩ " የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች የተሻለ ውጤት በማምጣት ወደ ከፍተኛ ተቋም ይገባሉ፣ ይሁን እንጂ በቂ አይደለም፣ ብዙ ነገሮች መሻሻል እንዳለባቸው ጥናቱ አሳይቶናል " ብሏል።
ጥናቱ ምን አይነት የትምህርት ዘርፍ ችግር ነው ይሄን ያክል ውድቀት ያመጣብን ፣ ከተማሪዎች መውደቅ እና ማለፍ ጋር ተያይዞ የትምህርቱ ባህሪ ምንድን ነው የሚለውን እና በአጠቃላይ በትምህርት ዘርፉ ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን የያዘ ነው።
በሁሉም የትምህርት ዘርፍ ላይ ያሉ ችግሮችን ያሳየው ይሄ ጥናት በመጨረሻም የመፍትሄ ሃሳቦችንም አቅርቧል።
ትምህርት ሚኒስቴር ምን የመፍትሄ ሃሳብ አቀረበ ?
" ከዚህ በፊት 10ኛ ክፍል ላይ ይሰጥ የነበረውን ሀገራዊ ፈተና ሳይወስዱ 11ኛ ክፍል የሚማሩ ተማሪዎች ልዩ የማካካሻ ፕሮግራም ያስፈልጋቸዋል። ይሄ ካልሆነ ግን መውደቅ ይቀጥላል ፣ ምክንያቱ የሚፈለገውን ያህል እውቀት እና ክህሎት ይዘው አይወጡም።
በገጠር በተለይም በአርብቶ አደሮች አካባቢዎች ላይ ያለው የትምህርት ዘርፍ ልማት አነስተኛ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ እጅግ ወደ ኋላ እየቀረ ስለሆነ ማካካሻ መሰራት አለበት።
ሌላው ደግሞ ከትምህርት አመራር፣ መምህራን እና ከአቅም ግንባታ ጋር ተያይዞ ያሉ ጉዳዮች ውጤት በሚያመጡ ጉዳዮች ላይ ብቻ ትኩረት ተደረጎ የትምህርት አመራሩ አቅም እስካልሰጠ ችግሮቹ ይቀጥላሉ።
ለመምህራን የደመወዝ ጭማሪ ብቻ ሳይሆን መምህሮችን የሚያቅፍ የ insensitive package እስካልመጣ ድረስ ችግሮቹ ይባባሳሉ።
በተጨማሪም በሀብት ክፍፍል ላይ ክፍተት በመኖሩ በትምህርት ዘርፉ ልማት ላይ ተግዳሮት መኖሩን ያሳያል፣ ይሄም መፈታት አለበት " ሲል መፍትሄ ያለውን ሃሳብ አቅርቧል።
ትምህርት ሚኒስቴር ጥናቱን ባቀረበበት ወቅት የህዝብ ተወካዮች የተለያዩ አስተያየቶች፣ ጥያቄዎች እና ሃሳቦችን አቅርበዋል።
በጥናቱ ላይ የመፍትሄ ሃሳቦች መቅረባቸው ጥሩ ሁነው ሳለ እንደዚሁ ተወርተው መሬት ላይ ሳይወርዱ ከቀሩ ትርጉም አልባ ናቸው፣ በመሆኑም ሁሉም በአፅንኦት ሊመለከተው እንደሚገባ በተወካዮች ተጠቁሟል።
ከ1 እስከ 8ኛ ክፍል ላሉ ተማሪዎች የሚደረገው ድጋፍ አነስተኛ ነው፣ ይሄም አሁን ላለንበት ውጤት ማጣት ትልቁን ድርሻ ይወስዳል ፤ በጥናቱስ ላይ ለምን ይሄ ሳይካተት ቀረ፣ ምክንያቱም የትምህርት መሰረቱ ከታች ጀምሮ ስለሆነ የሚሉ ጥያቄዎች ተነስቷል።
የተለያዩ ተማሪዎች በህገወጥ መንገድ ወደተለያዩ ሀገሮች እየተሰደዱ ነው፣ ተማሪዎች ይሄ ሲፈጠር ተረጋግተው መማር እየቻሉ አይደለም፣ ትምህርት ሚኒስቴር ትኩረት ሊሰጠው ይገባል ተብሏል።
👍 @QesemAcademy