Репост из: አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ
#ሰማዕቱ_ቅዱስ_እስጢፋኖስ
በስመ #አብ_ወወልድ_ወመንፈስ_ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን አምላካችን መድኃኒታችን #ኢየሱስ_ክርስቶስን በሰማዕቱ ስም ለምናመሰግንበት #ለቅዱስ_እስጢፋኖስ ወርኀዊ መታሠቢያ ክብረ በዓል እንኳን አደረሰን።
የትውልድ ሀገሩ #ኢየሩሳሌም ሲሆን አባቱ #ስምዖን እናቱ ደግሞ #ማርያም ይባላሉ ዘመኑም የመጀመርያው ምእተ ዓመት ነው
እንግዲህ በዘመነ ሐዋርያት የማዕዱን እና የውስጡን አገልግሎት እንዲያስተናብሩ መንፈስ እና ጥበብ የሞላባቸው ሰባት ሰዎች ተመርጠው በሐዋርያት አንብሮተ ዕድ ከተሾሙት ሰባቱ ዲያቆናት መካከል በቅድስና ሕይወቱ ለክርስቲያኖች አብነት የሆነው ሰማዕቱ #ቅዱስ_እስጢፋኖስ ይገኝበታል እስጢፋኖስ የሚለው ቃል የግሪክ ቃል ሲሆን ትርጉሙም #አክሊል ማለት ነው።
መጽሐፍ ቅዱስን ወደ ግእዝ በኋላም ወደ አማርኛ የመለሱት አባቶች በቀጥታ የግሪኩን እስጢፋኖስ የሚለውን ቃል ተጠቅመዋል #ቅዱስ_እስጢፋኖስ ምንም እንኳን ስሙ የግሪክ ስም ይሁን እንጂ በትውልዱ አይሁዳዊ ነው።
ወላጆቹ ይህንን ስም የሰጡት ተብሎ የሚታመነዉ ወላጆቹ በፍልስጤም ጠረፋማ ከተሞች ይኖሩ ስለ ነበር የግሪክ ባሕልና ቋንቋ ተጽእኖ አድሮባቸው ይሆናል ተብሎ ይገመታል።
#ቅዱስ_እስጢፋኖስ በሐዋርያት ጥበቃ የነበረችውን ቤተ ክርስቲያን ከአምላክ ዘንድ ባገኘው የማስተማርና የፈውስ ሀብት ያገለግል ነበር በእርሱም ታላላቅ ተአምራት ይፈፀሙ ነበር።
ስለዚህም ሕዝቡ ከፊት ይልቅ እጅግ እየበዛና በትምህርት እየጠነከረ መጣ አይሁድም ይህን ተመልክተው በቅዱስ #እስጢፋኖስ ላይ በቅናትና በጠላትነት ተነሡበት ነገር ግን ከመንፈስ ቅዱስ ባገኘው ጥበብና ኃይል እነርሱን በቃልም በድርጊትም ይቃወማቸው ነበርና ሊረቱት አልተቻላቸውም።
ስለዚህም #እግዚአብሔርን ሙሴን ሲሳደብ ሰምተነዋል ሙሴ የሠራልንን ሥርዐት ይለውጣል በዚህ ቤተ መቅደስና በሕጉ ላይ የስድብን ቃል ይናገራል ይህንንም ቤተ መቅደስ የናዝሬቱ ኢየሱስ አፍርሱ ብሏል እያለ ያስተምራል እያሉ ሕዝቡን ሽማግሌዎችንና ጸሐፍትን በማናደድ ይዘው ከሸንጎ ፊት አቆሙት
ቅዱስ #እስጢፋኖስን በሸንጎ ፊት ባቆሙት ጊዜም ፊቱ ልክ እንደ #መልአክ ፊት ሆኖ በርቶ ነበር እርሱም ለተከሰሰበት ነጥብ መልስ ሰጠ ከአብርሃም እስከ ክርስቶስ ለእነርሱ የተሰጣቸውን በረከት በመቃወማቸው ከተስፋ ቃል እርቀው እንደተወገዱ ገለጠላቸው።
#ክርስቶስንም ባለመቀበላቸው ወቀሳቸው በዚህም ምክንያት በቁጣ ተነሣስተው ከከተማ ውጭ በመውሰድ በድንጋይ ወግረው ገደሉት #ቅዱስ_እስጢፋኖስ አይሁድ በድንጋይ እየወገሩት ሳለ ሰማያት ተከፍተው #ክርስቶስን በአብ ቀኝ ቆሞ ተመለከተ ይህንን ራእይ የክርስቶስን ትንሣኤ ለማይቀበሉት አይሁድ አሰምቶ ተናገረ።
እነርሱ ከፊት ይልቅ በእርሱ ጨከኑ በድንጋይም ወገሩት ነገር ግን #ቅዱስ_እስጢፋኖስ ጌታውን ክርስቶስን መስሎ ነበርና ልክ እንደ መምህሩ #አቤቱ_ይህን_ኃጢአት_አትቁጠርባቸው” ብሎ በታላቅ ድምፅ ጮኾ ነፍሱን ሰጠ በቤተክርስቲያንም ታሪክ ስለ ክርስቶስ መስክሮ ሰማዕትነትን የተቀበለ የመጀመሪያው ሰማዕት ሆኗል።
በደማስቆ መንገድ ላይ ክርስቲያኖችን ያሳድድ የነበረ ሳውል በኋላም ቅዱስ ጳውሎስ ተብሎ ስያሜ የተሰጠው ሐዋርያ ቅዱስ እስጢፋኖስ በድንጋይ በሚወግሩበት ወቅት በእርሱ ሞት ተስማምቶና ድንጋይን በእስጢፋኖስ ላይ ያነሡትን የአይሁድ ልብስ ይጠብቅ የነበረ ብላቴና ነበር
ነገር ግን #ቅዱስ_ጳውሎስ ሐዋርያ ከሆነ በኋላ የሰማዕቱ #የእስጢፋኖስን ቤተሰቦች አጥምቋቸዋል ይህ ደግሞ ድንቅ ነው የሰማዕቱ መታሠቢያ በቤተክርስቲያን መጽሐፈ ስንክሳር የበዓላት ዝርዝር ላይ ቀን ተሰጥቶት ይከበራል ይኽም
በመስከረም 17 በዓለ ፍልሰተ አጽሙ፤ ጥቅምት 17 ቀን የዲቍና ማዕረግን በአንብሮተ ዕድ በሐዋርያት የተቀበለበት፤ ጥር 1 ደግሞ የልደቱ እና የዕረፍቱ መታሰቢያ ሆኖ ይከበራል በየወሩ በ 17 የሰማዕቱ መታሠቢያም ነው።
#በረከቱ_ምልጃና_ጸሎቱ_አይለየን!
#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!
አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube
Sador Sisay on Youtube
Sador Sisay on Instagram
Sador Sisay on Facebook
Sador Sisay on Tiktok
#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏
በስመ #አብ_ወወልድ_ወመንፈስ_ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን አምላካችን መድኃኒታችን #ኢየሱስ_ክርስቶስን በሰማዕቱ ስም ለምናመሰግንበት #ለቅዱስ_እስጢፋኖስ ወርኀዊ መታሠቢያ ክብረ በዓል እንኳን አደረሰን።
የትውልድ ሀገሩ #ኢየሩሳሌም ሲሆን አባቱ #ስምዖን እናቱ ደግሞ #ማርያም ይባላሉ ዘመኑም የመጀመርያው ምእተ ዓመት ነው
እንግዲህ በዘመነ ሐዋርያት የማዕዱን እና የውስጡን አገልግሎት እንዲያስተናብሩ መንፈስ እና ጥበብ የሞላባቸው ሰባት ሰዎች ተመርጠው በሐዋርያት አንብሮተ ዕድ ከተሾሙት ሰባቱ ዲያቆናት መካከል በቅድስና ሕይወቱ ለክርስቲያኖች አብነት የሆነው ሰማዕቱ #ቅዱስ_እስጢፋኖስ ይገኝበታል እስጢፋኖስ የሚለው ቃል የግሪክ ቃል ሲሆን ትርጉሙም #አክሊል ማለት ነው።
መጽሐፍ ቅዱስን ወደ ግእዝ በኋላም ወደ አማርኛ የመለሱት አባቶች በቀጥታ የግሪኩን እስጢፋኖስ የሚለውን ቃል ተጠቅመዋል #ቅዱስ_እስጢፋኖስ ምንም እንኳን ስሙ የግሪክ ስም ይሁን እንጂ በትውልዱ አይሁዳዊ ነው።
ወላጆቹ ይህንን ስም የሰጡት ተብሎ የሚታመነዉ ወላጆቹ በፍልስጤም ጠረፋማ ከተሞች ይኖሩ ስለ ነበር የግሪክ ባሕልና ቋንቋ ተጽእኖ አድሮባቸው ይሆናል ተብሎ ይገመታል።
#ቅዱስ_እስጢፋኖስ በሐዋርያት ጥበቃ የነበረችውን ቤተ ክርስቲያን ከአምላክ ዘንድ ባገኘው የማስተማርና የፈውስ ሀብት ያገለግል ነበር በእርሱም ታላላቅ ተአምራት ይፈፀሙ ነበር።
ስለዚህም ሕዝቡ ከፊት ይልቅ እጅግ እየበዛና በትምህርት እየጠነከረ መጣ አይሁድም ይህን ተመልክተው በቅዱስ #እስጢፋኖስ ላይ በቅናትና በጠላትነት ተነሡበት ነገር ግን ከመንፈስ ቅዱስ ባገኘው ጥበብና ኃይል እነርሱን በቃልም በድርጊትም ይቃወማቸው ነበርና ሊረቱት አልተቻላቸውም።
ስለዚህም #እግዚአብሔርን ሙሴን ሲሳደብ ሰምተነዋል ሙሴ የሠራልንን ሥርዐት ይለውጣል በዚህ ቤተ መቅደስና በሕጉ ላይ የስድብን ቃል ይናገራል ይህንንም ቤተ መቅደስ የናዝሬቱ ኢየሱስ አፍርሱ ብሏል እያለ ያስተምራል እያሉ ሕዝቡን ሽማግሌዎችንና ጸሐፍትን በማናደድ ይዘው ከሸንጎ ፊት አቆሙት
ቅዱስ #እስጢፋኖስን በሸንጎ ፊት ባቆሙት ጊዜም ፊቱ ልክ እንደ #መልአክ ፊት ሆኖ በርቶ ነበር እርሱም ለተከሰሰበት ነጥብ መልስ ሰጠ ከአብርሃም እስከ ክርስቶስ ለእነርሱ የተሰጣቸውን በረከት በመቃወማቸው ከተስፋ ቃል እርቀው እንደተወገዱ ገለጠላቸው።
#ክርስቶስንም ባለመቀበላቸው ወቀሳቸው በዚህም ምክንያት በቁጣ ተነሣስተው ከከተማ ውጭ በመውሰድ በድንጋይ ወግረው ገደሉት #ቅዱስ_እስጢፋኖስ አይሁድ በድንጋይ እየወገሩት ሳለ ሰማያት ተከፍተው #ክርስቶስን በአብ ቀኝ ቆሞ ተመለከተ ይህንን ራእይ የክርስቶስን ትንሣኤ ለማይቀበሉት አይሁድ አሰምቶ ተናገረ።
እነርሱ ከፊት ይልቅ በእርሱ ጨከኑ በድንጋይም ወገሩት ነገር ግን #ቅዱስ_እስጢፋኖስ ጌታውን ክርስቶስን መስሎ ነበርና ልክ እንደ መምህሩ #አቤቱ_ይህን_ኃጢአት_አትቁጠርባቸው” ብሎ በታላቅ ድምፅ ጮኾ ነፍሱን ሰጠ በቤተክርስቲያንም ታሪክ ስለ ክርስቶስ መስክሮ ሰማዕትነትን የተቀበለ የመጀመሪያው ሰማዕት ሆኗል።
በደማስቆ መንገድ ላይ ክርስቲያኖችን ያሳድድ የነበረ ሳውል በኋላም ቅዱስ ጳውሎስ ተብሎ ስያሜ የተሰጠው ሐዋርያ ቅዱስ እስጢፋኖስ በድንጋይ በሚወግሩበት ወቅት በእርሱ ሞት ተስማምቶና ድንጋይን በእስጢፋኖስ ላይ ያነሡትን የአይሁድ ልብስ ይጠብቅ የነበረ ብላቴና ነበር
ነገር ግን #ቅዱስ_ጳውሎስ ሐዋርያ ከሆነ በኋላ የሰማዕቱ #የእስጢፋኖስን ቤተሰቦች አጥምቋቸዋል ይህ ደግሞ ድንቅ ነው የሰማዕቱ መታሠቢያ በቤተክርስቲያን መጽሐፈ ስንክሳር የበዓላት ዝርዝር ላይ ቀን ተሰጥቶት ይከበራል ይኽም
በመስከረም 17 በዓለ ፍልሰተ አጽሙ፤ ጥቅምት 17 ቀን የዲቍና ማዕረግን በአንብሮተ ዕድ በሐዋርያት የተቀበለበት፤ ጥር 1 ደግሞ የልደቱ እና የዕረፍቱ መታሰቢያ ሆኖ ይከበራል በየወሩ በ 17 የሰማዕቱ መታሠቢያም ነው።
#በረከቱ_ምልጃና_ጸሎቱ_አይለየን!
#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!
አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube
Sador Sisay on Youtube
Sador Sisay on Instagram
Sador Sisay on Facebook
Sador Sisay on Tiktok
#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏