#በዓለ_ለጥንተ_ትንሣኤ_እና_በዓለ_ፅንሰተ_ኢየሱስ ክርስቶስ
#እግዚአብሔር_ዓለምን_ከፈጠረበት_ጥበቡ_ይልቅ_ከድንግል_ማርያም_ሰው_ሆኖ_ዓለምን_ያዳነበት_ጥበቡ_ይበልጣል ምክንያቱም እግዚአብሔር ዓለምን የፈጠረበት ጥበቡ 7ቱ ዕለታትን 20ው ዓለማትን 22ት ሥነ ፍጥረታትን ካለመኖር ወደ መኖር ከፈጠራቸውም ላይ አሻሽሎ አስገኘ ዓለምን ያዳነበት ጥበብ ግን ሰማይና ምድር የማይወስኑት ከጽርሐ አርያም በላይ ጠፈሩ ከበርባሮስ በታች መሠረቱ ለአድማስና ለናጌብ ዳርቻቸው የኾነ አምላክ በአጭር ቁመትና በጠባብ ደረት ለሰው ልጅ ቤዛ ለመሆን ወደ ፈጠረው ምድር በፈጠረው አካል ላይ የሰማይ ዙፋኑን ሳይለይ መጥቷል።
#ብሥራትና ፅንሰት በአንድ ዕለት ነው የተከናወኑት #ኢየሱስ ክርስቶስ በማህፀነ #ማርያም የተፀነሰው ልክ ቅዱስ #ገብርኤል ትፀንሲ ትፀንሺያለሽ ሲላት እርሷም “ይኩነኒ በከመ ትቤለኒ” እንደቃልህ ይደረግልኝ ብላ በተቀበለች ጊዜ የእግዚአበሔር ቃል በማሕፀነ ድንግል ማርያም ተፀነሰ፡፡ አብ አፀናት መንፈስቅዱስ አነጻት ወልድ በተለየ አካሉ ከሥጋዋ ስጋ ከነፍሷ ነፍስ ነስቶ ተዋሐዳት ሉቃ፡ 1፥33
እመቤታችን እናቱ ቅድስት ድንግል ማርያም ንጽሕት መቅደሱ ናትና ነገሩን አስቀድማ ጠንቅቃ ትወቅ ሲል ቅዱስ ገብርኤልን ልኮታል ሉቃ፡ 1፥26-28
ብሥራቱን የነገራት መጋቢት 29 ቀን በዕለተ እሑድ ከቀኑ ሦስት ሰዓት ላይ ነው ቅዱስ ገብርኤልም ብርሃናዊ መልአክ መሆኑን ለማጠየቅ እና የሥላሴ ማደርያ መኾኗን ለማስረዳት 3 ጊዜ ተመላልሷል።
ሉ፡ 1፥33፤ ማቴ፡ 18፥16
#ሊቀ_መላእክት ቅዱስ ገብርኤልም በደስታ ተውጦ ለመላእክት ጉባኤ “በቅድስት ድንግል ማርያም የይሁንታ ቃል ምክንያት ዓለም ዳነች” ብሎ የምስራች አላቸው ነቢዩ ሕዝቅኤል “… በዙፋኑም አምሳያ ላይ እንደ ሰው መልክ አምሳያ ነበረ” ሕዝ፡1፥26 ብሎ እንደገለጠው እግዚአብሔር አምላክ ለመላእክት በሰው ምሳሌ ተገልጦ ይታያቸው ነበር እንጂ እርሱን ገጽ በገጽ አያዩም ነበር ነገር ግን ቅዱስ ገብርኤል የፅንሰቱን ነገር ለመላእክት በነገራቸው ጊዜ ፈጣሪያቸው እግዚአብሔር ቃል ሰው በመሆን በአካል ሊያዩት እንደተቃረቡ ተረድተው ከዚህ በፊት ተሰምቶ የማያውቅ ታላቅ የሆነ የደስታ ዝማሬ ዘመሩ በዚያን ጊዜ ቅዱሳን መላእክት ደስታቸው ድርብ ነበር የመጀመሪያው ደስታቸው የሰው ልጆች መዳን ሲሆን ሁለተኛው ግን አምላካቸውን በጠባብ ደረት በአጭር ቁመት ተወስኖ ለማየት በመብቃታቸው ነበር፡፡
ቅዱስ ገብርኤል ለማብሰር የተመረጠውም
#በማብሠር_የታወቀ_ስለሆነ መሳ፡ 13፤ ሊቃ፡ 1 #የስሙ_ትርጓሜ_ሥራውን_ስለሚገልጽ ገብር ሰው ማለት ሲሆን ኤል ደሞ አምላክ ማለት ነው ስለዚህ አምላክ ወሰብእ ማለት ነው (አምላክም ሰውም) ስለዚህ የአምላክ ሰው የመሆንን ምሥጢር እንዲያበስር ተልኳል።
#ሳጥናኤል አምላክ እኔ ነኝ ብሎ መላእክትን ባሸበራቸውጊዜ ‹‹ንቁም በበህላዌነ እስከ ንረክቦ ለአምላክነ (የፈጠረን ይህ አይደለምና ፈጣሪያችንን እስክናገኝ ድረስ በያለንበት እንጽና ) ብሏል፡፡ ይህን ያለበት አንደበቱ የአምላክን ሥጋዌ ለእመቤታቸን ለመንገር አብቅቶታል።
ይህ በቅዱስ ገብርኤል ብሥራት አምላክ በማኅፀነ ማርያም ያደረበትን የፅንሰቱን በዓል ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን በታላቅ ድምቀት በማኅሌት እና በቅዳሴ በትምህርትም መጋቢት 29 ቀን ስታስብ ከጌታችን ዘጠኙ ዐበይት በዓላት ውስጥ አንደኛውና የመጀመሪያው አድርጋ ታስበዋለች፡፡
ይህ በዓል በፆም ወቅት ሰለሚውል መጋቢት 29 አበው በሰሩልን ሥርዓት መሠረት ልዋጭ በዓሉን ታኀሣሥ 22 ብሥራቱን በድምቀት እናከብረዋለን
ፍትሐ ነ አንድምታ አ.15
#ጥንተ ትንሣኤ
#ትንሣኤ የሚለው ቃል የግእዝ ቃል ነው መገኛ ቃሉም ተንሥአ ተነሣ የሚለው ግስ ሲሆን ትንሣኤ ማለት መነሣት አነሣሥ ሐዲስ ሕይወት ማግኘት ማለትን ያመለክታል፡፡
ጌታችን በመስቀል ላይ ተሰቅሎ በሥጋ ከሞተበት ቀን መጋቢት 27 ሦስተኛው ቀን መጋቢት 29 ነውና ይህች ዕለት ቅድስት ትንሣኤው ውሎባታል በከበረች ልዩ የሆነች ትንሣኤው የዓለም ድኀነት ሆነ በረቀቀ ጥበቡ በዚህች ቀን ከሙታን ተለይቶ ተነሥቷል
የጽንሰቱ በዓል ተደርቦበት ነው እንጂ ልናስበው የሚገባ ትልቅ ዕለት ነው።
#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!
@zechristos?si=zUG3tBXDKFNQT5i5' rel='nofollow'>አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube
@sadorsisay294?si=c13-BuI8aZPW8chG' rel='nofollow'>Sador Sisay on Youtube
Sador Sisay on InstagramSador Sisay on Facebook@sadorudnsador12?_t=8lAVjDFAsIH&_r=1' rel='nofollow'>Sador Sisay on Tiktok
#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏