የቅዱሳን ታሪክ


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: не указана


በዚህ ቻናል ውስጥ፦
በኦርቶዶክስ ተዋህዶ ብቻ የሚገኙ ስዕላትን
የቤተክርስቲያን ትውፊት የጠበቁ ስዕላት የአድባራት እና የገዳማት ፎቶዎችን ያገኛሉ

የተለያዩ ስዕለ አድዕኖ ለመላክ
@kidanemiherat_bot

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
не указана
Статистика
Фильтр публикаций


Репост из: አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ
ለኢትዮጵያ_ውበቷ_የኩራት_መቀነቷ_ሊቀ_ተዋሕዶ_ያሬድ_አባታችን
༺◉❖═───◉●◉🌹🌹🌹◉●◉───═❖◉༻

#ቅዱስ_ያሬድ ሲታስብ በሁላችን ኅሊና ውስጥ ወይም በሁላችንም ዕውቀት ውስጥ የሚመጣው #ዜማ የሚላው ቃል ነው ። የቅዱስ ያሬድ ዝርዝር ታሪክና ያበረከተው ሰፊ አስተዋፅኦ በተወሰነ ካህናትና ምእመናን ቢታወቅም በአብዛኛው ምእመናን ዘንድ ግን ስለቅዱስ ያሬድ ያለን ግንዛቤና መረጃ በጣም ውሱን ነው ፡፡

ስለዚህ የቤተ ክርስቲያናችን ብርሃን የሀገራችን ወርቃማ ሀብት ስለሆነው ታላቅ ሊቅ ይመለከተኛል በምንለው በተዋሕዶ ልጆች እንኳን የጠለቀ ግንዛቤ አለመኖሩ ሥራዎቹ ከቤተ ክርስቲያንም አልፎ ለሀገር ፣ ከሀገርም አልፎ ለዓለም እንዳይተርፍ አድርጎታል ።

ቅዱስ ያሬድ ለነፍስም ለሥጋም በሰማይ ለሚጠብቀን ሕይወታችንም ሆነ በምድር ላለው ሕይወታችንም የሚሆን ቁስለ ነፍስን የሚያክም አጥንትን የሚያለመልም ድንቅ ድርሰቶችን አበርክቶልናል ፡፡

ዛሬ በሠለጠኑ ሀገሮች የነበሩ ፈላስፎች ሥራዎቻቸውን በዓለም መድረክ ስላስተዋወቁላቸው መካነ መቃብሮቻቸውና ይገለገሉበት የነበረው ቁሳቁስ ሳይቀር እየተጎበኙ ለሀገራቸው በሕይወት እያሉ ካበረከቱት ጥቅም በላይ ከሞቱ በኋላ ያበረከቱት ጥቅምና አገልግሎት እየበለጠ ሄዷል ፡፡

በዚህ መልኩ የሰለጠኑ ሀገሮች የቱሪስቶቻቸውን ፍሰት ከጨመሩበት መንገዱች አንዱ የሊቃውንቶቻቸውን ታሪክ ማስተዋወቅ ነው ። ቅዱስ ያሬድ በመንፈስ ቅዱስ ቃኝነት ያበረከተልን በዓለም ተወዳዳሪ የሌለውን ይህን ዜማ በከፍተኛ ተጋድሎ ጠብቀው ከትውልድ ወደ ትውልድ በማስተላለፍ እስካሁን ላደረሱልን #የኢትዮጵያ_ሊቃውንት_አባቶቻችን ከፍተኛ የሆነ አድናቆትና ምስጋና ሊሰጣቸው ይገባል ፤ የአሁኑ ትውልድም ለዘመናት ተጠብቆ የኖረውን ዜማና ባህል ዘመኑ በሚጠይቀው ሁኔታ ተንከባክቦ ለቀጣዩ ትውልድ ማስተላለፍ ይጠበቅበታል ።

የዝማሬ ፣ የፍልስፍና ፤ የስነ ከዋክብት ፤ የሕግ የታሪክ ፣ የመልክዐ ምድርና የቋንቋ ሊቅ የሆነው ቅዱስ ያሬድ ዛሬ ዓለም ለደረሰበት የዜማ ፣ የተፈጥሮ ሳይንስና የማኅበራዊ ሕይወት ፍልስፍናም መሠረት ነው ሊያስብል የሚያስችሉ ሰማያዊ ሰነዶችን ትቶልን ሄዷል
#ከቅዱስ_ያሬድ_ረድኤት_በረከትን_ያሳትፈን

#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

@zechristos?si=zUG3tBXDKFNQT5i5' rel='nofollow'>አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

@sadorsisay294?si=c13-BuI8aZPW8chG' rel='nofollow'>Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

@sadorudnsador12?_t=8lAVjDFAsIH&_r=1' rel='nofollow'>Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏




Репост из: አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ
#ሰማዕታት_ዘሊቢያ
#ክቡር_ዕንባ

እነሆ ያቺ ሰዓት ደረሠች የመጨረሻዋ ደቂቃ ለመሠዋት የተዘጋጀችሁበትን ትዕይንት የተመከተ በልቡ ኃዘን ሞላ፡፡ በዚያች ቅጽበት ደም በግፍ ፈሷልና ፍጥረት ሁሉ አነባ… ይህ ዕንባ የሰው ልጅ ጭካኔ የደረሠበትን ደረጃና የገዳዮቹን ኢ-ሰብዓዊነት የሚያሳይ ነው፡፡ የክርስቶስ ተቃዋሚ ምን ያህል ከሰውነት ተራ ወጥቶ የአውሬውን ባህሪ እንደተላበሰ የሚገልፅ መሪር ዕንባ ነው፡፡ በዚህ ሁሉ ውስጥ እኛ ሁላችን የክርስቶስ ተከታይ ነንና ክፉዎች ከክፉ ሥራቸው እንዲመለሱ፤ ጌታን ወደ ማወቅ እንዲደርሱ የክርስቶስ የማዳን ሥራ እንዲገልፅላቸው የሚያሳስብ ዕንባም ነው፡፡ ጳውሎስ በክርስቶስ ምህረት የጌታ ምርጥ እቃ ተብሏልና፡፡ (የሐዋ ሥራ ም.9)

ይህ ዕንባ በግፍ በመሠዋታችሁ በቤተሠቦቻችሁ ላይ የደረሠውን ጥልቅ ኃዘን የተካፈልንበት የአንድነታችን መገለጫ ነው፡፡ ይህ ዕንባ የምሬት ዕንባ ብቻ አይደለም፤ ይልቁንም ከድካም ወደ ብርታት ከምድር ወደ ሠማይ በክብር የተጠራችሁ፤ በደም የክርስቶስ ምስክር ናችሁና ይህ ዕንባ የደስታ ዕንባም ነው፡፡ በዘመናችን ዓይናችን እያየ እንደ ደመና በዙያችን ከበውን ካሉት የድል አድራጊዎች ማህበር ጋር የተደመራችሁ እናንተ፤ ከመላእክት ጋር ክርስቶስን ለማመስገን እድል ፈንታ አግኝታኋልና ዕንባችን የምሬት ብቻ አይደለም፡፡ በሠማይ ያሉ ቅዱሳን እናንተን እንዴት እንደተቀበሏችሁ ስናስብ በጌታ ላይ ላለን ተስፋ የዘወትር ተስፋችን ሆኗል፡፡ ይህ ዕንባ በእውነት የንስሃ ዕንባ ነው፡፡ በዓለም ያሉ አማኞች ሁሉ ከኃጢአት ይነፁ ዘንድ፤ በእምነት በርትተው አዳኛቸውን ክርስቶስ የሚለምኑበት ክቡር ዕንባ ነው፡፡ እንደ እናንተ አምላክ እቅፍ ለማረፍ ፍጥረት ሁሉ ያነባው ዕንባ ነው፡፡

#የዝምታችሁ_ቃል
‹‹በባህሩ ላይ የሚነፍሰው ነፋስ ያፏጫል እነሆ የሞት ሥጋን እንጂ ነፍስን መግደል ከማይችሉት ዘንድ ይታወጃል፡፡ አውሬው በአሸዋው ላይ ቆሟል፡፡ በዚህ ሁሉ ውስጥ ግን የእናንተ ዝምታ ሁሉን አሸንፎ ሠማያትን ሰንጥቆ ከጸባዖት ደርሷል›› አዎን!!! በዚያች ደቂቃ ለመሠዋት በተዘጋጃችሁበት ሠዓት ተንበርክካችሁ የገዳዮቻችሁ ሠይፍ በእናንተ ላይ በተመዘዘ ቅፅበት አንዳች ነገር ልባችንን ገዛው፤ ከሁሉ በላይ ጎልቶ የሚሰማው ዝምታችሁ፤ እርግጥ ነው ይህን ዝምታ ማንም ላይሠማው ይችል ይሆናል፡፡ ግና የሠማይ አባታችሁ በሚገባ አድምጧል፡፡ ዝምታችሁ በእርሱ ዘንድ የሚወደድ ቃል የሚደመጥ ምስጋና ነበር፡፡ በልባችሁ ጌታን ስታከብሩ የእግዚአብሔር መንፈስ ከእናንተ ጋር ነበር፡፡ ከስሞች በላይ የሆነውን ስም በጠራችሁ ሰዓት ፍርሃታችሁ ተወግዷል፡፡ ‹‹ኢየሱስ ክርስቶስ›› የሚለው ስም የጽናታችሁ ኃይል ነበርና ደስ ይበላችሁ፡፡

በምድር ሳለን የጌታን መምጣት ለምንጠባበቅ የዝምታችሁ ድምፅና የእምነታችሁ ጥንካሬ ከመቼውም ጊዜ ከሠማነው የስብከት ቃል ጮክ ብሎ ተሠምቶናል ለልባችንም ብርታት ሆኗል፡፡ ስብከትን በተግባር ከናንተ አይተናልና በእምነት ፀንተናል፡፡ ይህም ሰማዕትነታችሁ በሄሮድስ ሠይፍ በቤተልሔም የተሠውትን ንፁሃንን ያስታውሠናል፡፡ ተጋድሎአችሁን በደም ጽፋችኋልና ደስ ይበላችሁ፡፡

#በጉብዝናህ_ወራት

በዕለተ ዓርብ በጌታ ቀኝ የተሠቀለው እንዲህ አለ ‹‹አቤቱ በመንግሥትህ በመጣህ ጊዜ አስበኝ›› በዚያች የስቃይ ሰዓት በተግባር የተገለፀ የመስቀል ስብከት በክርስቶስ አምኖ የጌታን መንግሥት እንደወረሠ ሁሉ የእናንተም ሕይወት በመውደቅና በመነሣት፣ በማመንና ባለማመን በታላቅ ተጋድሎ የሚወረሠውን የዘላለም ህይወት በሰዓታት ጊዜያት ውስጥ በጉብዝባችሁ ወራት በእምነታችሁ በመፅናት እስከ ሞት ድረስ በመታመን በደማችሁ ምስክርነታችሁ ተገልጧልና ክብር ይገባችኋል!!!

አዎን ምስጋና በእናንተ ይገባል፡- በስሙ ጸንታችኋልና!!!

አዎን ምስጋና ለእናንተ ይገባል፡- መንግሥቱን ለመውረስ በሞታችሁ ጌታን ሰብካችኋልና!!!

እነሆ በሠማያዊ ክብር ከፍ ብላችኋልና ደግሞም ስለእኛ ጸልዩልን በክብሩ ዙፋን ፊት ቆማችኋልና ስለ ሠው ልጆች ሁሉ አሳስቡ እኛም ወደ ሰማያዊ ክብር በእምነት ፀንተን እስክንመጣ ድረስ ፀሎታችሁ አይለየን!!! አሜን!!!


ምንጭ፡- ሴንት ጆን፣ የግብጽ ኦርቶዲክስ ቤተክርስቲያን ዳቤ መጽሔት

#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

@zechristos?si=zUG3tBXDKFNQT5i5' rel='nofollow'>አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

@sadorsisay294?si=c13-BuI8aZPW8chG' rel='nofollow'>Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

@sadorudnsador12?_t=8lAVjDFAsIH&_r=1' rel='nofollow'>Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏




Репост из: አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ
#በመከራህ_ከመከራ_አድነኝ

በመልዕልተ መስቀል በተቀበልከው መከራ ከደዌ ኃጢአት አድነኝ።በመከራህ ከመከራ አድነኝ ደሜን በደምህ አንጻው ከኃጢአት ከፍዳ የሚያድን ደምህን ከሥጋዮ ጋር አዋህድልኝ።በመሰቀል ላይ በጠጣኽው ሐሞት ሰይጣን እሷን ከሚያሰራት ኃጢአት ለይተህ ለይተህ ሰውነቴን ጣዕም አሳድርባት

በመስቀል ላይ የተዘረጋ ስጋህ በመሰቀል ላይ አጋንንት በምክራቸው ወደ ገሃነም ለማውረድ ያሰቧት ልቡናዬን ወደ አንተ ይስቀለው።ወደ ፍያታዊ ዘየማን ዘለፍ ባለ እራስህ አጋንንት በበተር ኃጢአት የመቱት ራሴን ከፍ ከፍ አድርገው። "እስመ ከመ ተለዓልኩ እምድር እስሕብ ኩሉ ኃቤየ"ብለህ በማይታበል ቃልህ እንደተናገርህ በመሰቀል የተቸነከሩ በመሰቀል የተቸነከሩ እጆችህ ከፍ ከፍ ያድርጉኝ።

እርኩሳን አይሁድ ትፍ ያሉበት የጸፉት ፊትህ ኃጢአት ሰርቶ ያደፈ ፊቴን ያጽራው።በመሰቀል ላይ ሳለህ "አባ አመኃጽን ነፍስየ ውስተ እዴከ "ብለህ የለየኸት ነፍስህ በቸርነትህ መርታ አንተ ወደ አለህበት ታደርሰኝ።ምነው አታዘንም ትለኝ እንደሆነ አንተነ ለመሻት ያዘነ ልቡና የለኝም ምነው ንሰሐ አትገባም ትለኝ እንደሆነ ጻድቃን ወደማታልፍ እርስታቸው ወደ መንግሥተሰማያት ተመርተው የሚደርሱባት ንሰሐ ኃዘን የለኝም

ጌታዬሆይ ኃጢአት የሚያስተሰርይ እንባ የለኝም የዚህን ዓለም ሥራ በማሰብ ልቡናዬ ደከመ ተቆርቁሮ ወደ አንተ ያለቅስ ዘንድ አይቻለውም፡፡
እነሆ በኃጢአት ብዛት ልቡናዬ ተባረደ፡፡አንተን ወዶ በሚያፈሰው እንባ መናደድ አይቻለውም የሃብታት የምሥጢራት መገኛ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ አንተ ግን ራርተህ መልስንስጠኝ ያዘነ ልቡናን ስጠኝ በፍጹም ልቡና አንተን ለመሻት እወጣ ዘንድ ካንተ በመራቅ ካንተ በመለየት ተሰጥቶኝ የነበረውን ክብር አጣዋለሁ።

ቸር ንጉሥ ዛሬ ግን በለጋስነትህ ስጠኝ ጣልኩህ አንተ ግን አትጣለኝ ከከበረ ሕግህ ወጣሁ አንተም እኔን ለመፈለግ ውጣ ማለትም እንደገባ ይውጣ እንደወጣ ይቅር አትበለኝ።ምዕመናን ወዳሉበት ወደ መንግሥተ ሰማያት አግባኝ ከመንጋ በጉችህ ከተመረጡ ከጻድቃን ጋራ እንድ ቆጠር አርገኝ የአምላክነትህ ገንዘብ የምትሆን እህል ምሥጢርህን መግበኝ ካንተ የተገኝውን ምሥጢር የሚያዩበት ባንተ ስላመኑ ለሚጨነቁ
የሚሰጥ ክብር ነው፡፡{በጹዕ ማር ይስሐቅ)

#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

@zechristos?si=zUG3tBXDKFNQT5i5' rel='nofollow'>አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

@sadorsisay294?si=c13-BuI8aZPW8chG' rel='nofollow'>Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

@sadorudnsador12?_t=8lAVjDFAsIH&_r=1' rel='nofollow'>Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏




Репост из: አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ
“#ጌታችሁ_በምን_ሰዓት_እንዲመጣ_አታውቁምና_እንግዲህ_ንቁ።”
ማቴ፡ 24፥42

ጊቢ ተማሪ በነበርኩበት ወቅት እንደ ድንገት የኮረና ወረርሽኝ ስለመጣ ጊቢውን ለቀን በቶሎ እንድን ወጣ ተነገረን በሰዓቱ ደግሞ ለፈተና ዝግጁ ሆኖ ለመቅረብ በጥናት ተጠምደን ሰዓቶች ሁሉ ፍጥን ፍጥን እያሉ ያሚያንሱን ነበር ። ይዘን የሄድናቸውን እንደ ቆሎ በሶ ጭቆ ያሉ የርሃብ ማስታገሻ እህሎችን የምንወጣበት ቀን ስለማይታወቅ አብቃቅተን ቀስ እያልን በየተራ ነበር ስንጠቀም የከረምነው ቶሎ ለቃቹሁ ውጡ የሚል ቃል እንደደረሰን አእምሮአችን ሲግት የነበረውን ሀንዳውት እርግፍ አርጎ በቅስፈት ጥሎ ቤት መሄዱን ዶርሶም ማረፍን ይመኝ ጀመር ። እየተጠነቀቅን እየቆጠብን የምንጠቀማቸው እህሎች ከሎከር ወጥተው ከወንበሩ ተቆለሉ ሳይበላ እንደከረመ ሰው ወረድንባቸው አወደምናቸው ። ይሄ ሁሉ የምንሄድበት ቀን ተቆርጦ በመነገሩ የተፈጠረ ነው ጥንቁቅ እና ትጉህነት በአንዴ አፈር በላው ፈተና እወድቃለሁ በማለት ፍርሃት ከሌሎች ከደስታና ጫወታ ታቅቦ ይጠና የነበረው ዶርሙን በጩህት ሞላነው ።

ይህን ሁሉ እንድናገር ያረገኝ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ስለጌታ አመጣጥ እኛ ደግሞ ያን ቀን ስለማናውቅ ተዘጋጅተን መጠበቅ እንዳለብን ያስተማረውን ባነበብኩ ወቅት ነው

“የጌታ ቀን ሌባ በሌሊት እንደሚመጣ እንዲሁ ይመጣ ዘንድ ራሳችሁ አጥብቃችሁ አውቃችኋልና” 1ኛተሰ፡ 5፥2

የጌታ ቀን ድንገት እንደ ሌባ እንደሚመጣ በዚህ ቀን ተብሎ አለመታወቁን በተመለከተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ይሄን ተሰሎንቄ በተረጎመበት ድርሳኑ እንዲህ ይላል ጌታ እንደ ሌባ በሌሊት የሚመጣው ራሳችንን ለክፍት እና ለስንፍና አሳልፈን እንዳንሰጥ ሽልማታችን ከእኛ እንዳይወሰድ በዚህ ምክንያት ነው ራሳችውን አውቃችኋልና ይላል ታድያ ካወቃችሁ ለምን ትጓጓላችሁ የወደፊቱ አለመታወቁን ክርስቶስ ካለው ተማሩ። ይኽን ያለው በዚኽ ምክንት ነው ያለውን ጌታችን በምን ሰዓት እንዲመጣ አታውቁምና እንግዲህ ንቁ ማቴ፤ 24፥42 ከዚህ እንጻር ጳውሎስ ተናግሯል ይለናል።

ለፈተና መውደቅ ፍርሃት ትጉዎች እንድንሆን እንዳረገን የዛች ቀን ድንገት ሳይታሰብ መምጣት ከእግዚአብሔር ጋር ሕጉን በመጠበቅ እንዲኖር ያደርጋል ቀኑ ይሄነው ተብሎ ተነግሮን ሁሉን እረስተን እንደተውን ጥንቁቅነታችንን እንደተውን የዚያችን አለመታወቅም ሰዎች ደካሞች እንዳይሆኑ ልል ዘሊል እንዳንሆን ያደርጋል።

#በዲያቆን_ፍጹም_እንደተጻፈ

#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

@zechristos?si=zUG3tBXDKFNQT5i5' rel='nofollow'>አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

@sadorsisay294?si=c13-BuI8aZPW8chG' rel='nofollow'>Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

@sadorudnsador12?_t=8lAVjDFAsIH&_r=1' rel='nofollow'>Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏




Репост из: አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ
#ደብረ_ዘይት

#ደብረ_ዘይት ከጌታችን ዘጠኙ ንዑሳን በዓላት መካከል ስምንተኛው ሲሆን በዚህ ዕለት የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዳግም መምጣት ይታሰብበታል።

#ደብረ_ዘይት ማለት የወይራ ተራራ (የወይራ ዛፍ ያለበት ተራራ) ማለት ነው። ይህም ቦታ ከኢየሩሳሌም በስተምሥራቅ ከቄድሮስ ሸለቆ ራቅ ብሎ የሚገኝ ተራራ ነው።

#ደብረ_ዘይት ጌታችን ዳግም የመምጣቱን ምልክት የገለጸበትና የዚህን ዓለም ተልእኮ ሲያጠናቅቅ ያረገበት ተራራ ነው። በዚህ ሰንበት የክርስቶስ ምጽአት የተነገረበት ከመሆኑ በተጨማሪ ክርስቶስ ይመጣል ተብሎም ይታመናል።

ማቴ. 24 ፥ 3 – 35፦ “ጌታችንም በደብረ ዘይት ተቀምጦ ሳለ ደቀ መዛሙርቱ ለብቻቸው ወደ እርሱ ቀረቡና እንዲህ አሉት፦ 'ንገረን ይህ መቼ ይሆናል? የመምጣትህና የዓለሙ ፍጻሜስ ምልክቱ ምንድን ነው?'። ጌታችን ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አላቸው፦ የሚያስታችሁ እንዳይኖር ተጠንቀቁ፡፡ ብዙዎች ‘እኔ ክርስቶስ ነኝ’ እያሉ በስሜ ይመጣሉና፤ ብዙዎችንም ያስታሉ። ጦርነትን የጦርንም ወሬ ትሰሙ ዘንድ አላችሁ፤ ይህ ሊሆን ግድ ነውና፤ ተጠንቀቁ አትደንግጡ። ነገር ግን ፍጻሜው ገና ነው። ሕዝብ በሕዝብ ላይ፣ መንግሥት በመንግሥት ላይ ይነሣሉ። በየሀገሩም ረሃብ ቸነፈር የምድር መናወጥም ይሆናል። እነዚህ ሁሉ የምጥ መጀመሪያ ናቸው። ያን ጊዜም ለመከራ አሳልፈው ይሰጧችኋል፤ ይገድሏችኋልም። ስለ ስሜ በሰው ሁሉ ዘንድ የተጠላችሁ ትሆናላችሁ። ያንጊዜም ብዙዎች ሃይማኖታቸውን ይለውጣሉ፣ እርስ በእርሳቸው አሳልፈው ይሰጣጣሉ፣ እርስ በእርሳቸው ይጣላሉ፤ ብዙዎች ሐሰተኞች ነቢያትም ይመጣሉ፤ ብዙዎችን ያስታሉ። ከዓመፅም ብዛት የተነሣ ፍቅር ከብዙዎች ዘንድ ትጠፋለች። እስከ መጨረሻው የሚታገስ ግን እርሱ ይድናል። በአሕዛብ ሁሉ ላይ ምስክር ሊሆን ይህ የመንግሥት ወንጌል በዓለም ሁሉ ይሰበካል፤ ያንጊዜም ፍጻሜ ይደርሳል።”

መዝሙረኛው ቅዱስ ዳዊትም ስለ ጌታችን ለፍርድ መምጣት ሲናገር “እግዚአብሔር ከክብሩ ውበት ግልጥ ሆኖ ይመጣል፤ ዝምም አይልም፤ እሳት በፊቱ ይነድዳል።” ይላል። (መዝ. 49 ፥ 2)

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ “ሁልጊዜ ተዘጋጅታችሁ ኑሩ፤ ሽሽታችሁም በሰንበት አሊያም በክረምት እንዳይሆንባችሁም ጸልዩ” ያለው ቃል በስፋትና በጥልቀት ይሰበካል። (ማቴ. 24 ፥ 20)

#ተዘጋጅታችሁ_ኑሩ፦ ማለት ጌታችን መቼና በምን ዓይነት ሰዓት እንደሚመጣ ስለማይታወቅ ሰው ሁልጊዜ በንስሐ ታጥቦ ሥጋ ወደሙን ተቀብሎ መኖር አለበት ማለት ነው። የጌታችን መምጣት ሲባል የመጨረሻው የፍርድ ቀን ብቻ ሳይሆን ነፍሳችን ከሥጋችን ተለይታ የምትሄድበትን ቀን ማሰብም ይገባል፤ ምክንያቱም ከሞት በኋላ ንስሐ መግባት ጽድቅን መሥራት አይቻልምና።

#ሽሽታችሁም_በሰንበት_እንዳይሆን፦ ማለቱ በአይሁድ ሕግ ሰንበት ከዘረጉበት ሳያጥፉ ካጠፉበትም ሳይዘረጉ ሳይለብሱና ሳይታጠቁ የሚውሉበት ቀን ነውና ስለዚህ እናንተ በሃይማኖት ጠንክራችሁ በንስሐ ታጥባችሁ ለሥጋ ወደሙ በቅታችሁ ኑሩ እንጂ እንደ አይሁድ ሰንበት ሳትለብሱና ሳትታጠቁ አትኑሩ ማለቱ ነው።

#በክረምትም_እንዳይሆን_ጸልዩ፦ ማለቱ ክረምት ከላይ ዶፍ እየወረደ ከታችም ምንጭ እየፈለቀ ምድር የምትጨቀይበት ጉምና ደመና ጭጋግና ጤዛ ከጭቃ ጋር አንድ ላይ ሆነው አሳዶ ለመያዝ ሩጦ ለማምለጥ የማይቻልበት ወቅት ነው። በዚህ ዓይነት በኃጢአት ጨለማ በወደቃችሁበትና በጨቀያችሁበት ወቅት እንዳትጠሩ ጸልዩ ማለቱ ነው። አንድም ክረምት ቅጠል እንጂ ፍሬ አይገኝበትምና በስመ ክርስቲያን ብቻ እየኖራችሁ ለመንግሥተ ሰማያት የሚያበቃ ፍሬ ሳታፈሩ የጌታ መምጫ እንዳይሆን ተጠንቀቁ ማለቱ ነው።

ስለሆነም በአጠቃላይ ይህ ሳምንት እነዚህንና መሰል ምሥጢራትን በስፋት የምንማርበት ነውና ይህ ምሥጢር የተገለጠበትን ቦታ መነሻ ተደርጎ ደብረ ዘይት ተብሎ ይጠራል።

#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

@zechristos?si=zUG3tBXDKFNQT5i5' rel='nofollow'>አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

@sadorsisay294?si=c13-BuI8aZPW8chG' rel='nofollow'>Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

@sadorudnsador12?_t=8lAVjDFAsIH&_r=1' rel='nofollow'>Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏




Репост из: አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ
#በዓለ_ለጥንተ_ትንሣኤ_እና_በዓለ_ፅንሰተ_ኢየሱስ ክርስቶስ

#እግዚአብሔር_ዓለምን_ከፈጠረበት_ጥበቡ_ይልቅ_ከድንግል_ማርያም_ሰው_ሆኖ_ዓለምን_ያዳነበት_ጥበቡ_ይበልጣል ምክንያቱም እግዚአብሔር ዓለምን የፈጠረበት ጥበቡ 7ቱ ዕለታትን 20ው ዓለማትን 22ት ሥነ ፍጥረታትን ካለመኖር ወደ መኖር ከፈጠራቸውም ላይ አሻሽሎ አስገኘ ዓለምን ያዳነበት ጥበብ ግን ሰማይና ምድር የማይወስኑት ከጽርሐ አርያም በላይ ጠፈሩ ከበርባሮስ በታች መሠረቱ ለአድማስና ለናጌብ ዳርቻቸው የኾነ አምላክ  በአጭር ቁመትና በጠባብ ደረት ለሰው ልጅ ቤዛ ለመሆን ወደ ፈጠረው ምድር በፈጠረው አካል ላይ የሰማይ ዙፋኑን ሳይለይ መጥቷል።

#ብሥራትና  ፅንሰት በአንድ ዕለት ነው የተከናወኑት #ኢየሱስ ክርስቶስ በማህፀነ #ማርያም የተፀነሰው ልክ ቅዱስ #ገብርኤል ትፀንሲ ትፀንሺያለሽ ሲላት እርሷም “ይኩነኒ በከመ ትቤለኒ” እንደቃልህ ይደረግልኝ ብላ በተቀበለች ጊዜ የእግዚአበሔር ቃል በማሕፀነ ድንግል ማርያም ተፀነሰ፡፡  አብ አፀናት መንፈስቅዱስ አነጻት ወልድ በተለየ አካሉ ከሥጋዋ ስጋ ከነፍሷ ነፍስ ነስቶ ተዋሐዳት ሉቃ፡ 1፥33

እመቤታችን እናቱ ቅድስት ድንግል ማርያም ንጽሕት መቅደሱ ናትና ነገሩን አስቀድማ ጠንቅቃ ትወቅ ሲል ቅዱስ ገብርኤልን ልኮታል ሉቃ፡ 1፥26-28
ብሥራቱን የነገራት መጋቢት 29 ቀን በዕለተ እሑድ ከቀኑ ሦስት ሰዓት ላይ ነው ቅዱስ ገብርኤልም  ብርሃናዊ መልአክ መሆኑን ለማጠየቅ እና የሥላሴ ማደርያ መኾኗን ለማስረዳት 3 ጊዜ ተመላልሷል። 
ሉ፡ 1፥33፤ ማቴ፡ 18፥16

#ሊቀ_መላእክት ቅዱስ ገብርኤልም በደስታ ተውጦ ለመላእክት ጉባኤ “በቅድስት ድንግል ማርያም የይሁንታ ቃል ምክንያት ዓለም ዳነች” ብሎ የምስራች አላቸው ነቢዩ ሕዝቅኤል “… በዙፋኑም አምሳያ ላይ እንደ ሰው መልክ አምሳያ ነበረ” ሕዝ፡1፥26 ብሎ እንደገለጠው እግዚአብሔር አምላክ ለመላእክት በሰው ምሳሌ ተገልጦ ይታያቸው ነበር እንጂ እርሱን ገጽ በገጽ አያዩም ነበር ነገር ግን ቅዱስ ገብርኤል የፅንሰቱን ነገር ለመላእክት በነገራቸው ጊዜ ፈጣሪያቸው እግዚአብሔር ቃል ሰው በመሆን በአካል ሊያዩት  እንደተቃረቡ ተረድተው ከዚህ በፊት ተሰምቶ የማያውቅ ታላቅ የሆነ የደስታ ዝማሬ ዘመሩ በዚያን ጊዜ ቅዱሳን መላእክት ደስታቸው ድርብ ነበር የመጀመሪያው ደስታቸው የሰው ልጆች መዳን ሲሆን ሁለተኛው ግን አምላካቸውን በጠባብ ደረት በአጭር ቁመት ተወስኖ ለማየት በመብቃታቸው ነበር፡፡

ቅዱስ ገብርኤል ለማብሰር የተመረጠውም
#በማብሠር_የታወቀ_ስለሆነ መሳ፡ 13፤ ሊቃ፡ 1  #የስሙ_ትርጓሜ_ሥራውን_ስለሚገልጽ ገብር ሰው ማለት ሲሆን ኤል ደሞ አምላክ ማለት ነው ስለዚህ  አምላክ ወሰብእ ማለት ነው (አምላክም ሰውም) ስለዚህ የአምላክ ሰው የመሆንን ምሥጢር እንዲያበስር ተልኳል።
#ሳጥናኤል አምላክ እኔ ነኝ ብሎ መላእክትን ባሸበራቸውጊዜ ‹‹ንቁም በበህላዌነ እስከ ንረክቦ ለአምላክነ (የፈጠረን ይህ አይደለምና ፈጣሪያችንን እስክናገኝ ድረስ በያለንበት እንጽና ) ብሏል፡፡ ይህን ያለበት አንደበቱ የአምላክን ሥጋዌ ለእመቤታቸን ለመንገር አብቅቶታል።

ይህ በቅዱስ ገብርኤል ብሥራት አምላክ በማኅፀነ ማርያም ያደረበትን የፅንሰቱን በዓል ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን በታላቅ ድምቀት በማኅሌት እና በቅዳሴ በትምህርትም መጋቢት 29 ቀን ስታስብ ከጌታችን ዘጠኙ ዐበይት በዓላት ውስጥ አንደኛውና የመጀመሪያው አድርጋ ታስበዋለች፡፡

ይህ በዓል በፆም ወቅት ሰለሚውል  መጋቢት 29 አበው በሰሩልን ሥርዓት መሠረት ልዋጭ በዓሉን ታኀሣሥ 22 ብሥራቱን በድምቀት እናከብረዋለን
ፍትሐ ነ አንድምታ አ.15

#ጥንተ ትንሣኤ
#ትንሣኤ የሚለው ቃል የግእዝ ቃል ነው መገኛ ቃሉም ተንሥአ ተነሣ የሚለው ግስ ሲሆን ትንሣኤ ማለት መነሣት አነሣሥ ሐዲስ ሕይወት ማግኘት ማለትን ያመለክታል፡፡

ጌታችን በመስቀል ላይ ተሰቅሎ  በሥጋ ከሞተበት ቀን መጋቢት 27 ሦስተኛው ቀን መጋቢት 29 ነውና ይህች ዕለት ቅድስት ትንሣኤው ውሎባታል  በከበረች ልዩ የሆነች ትንሣኤው የዓለም ድኀነት ሆነ በረቀቀ ጥበቡ በዚህች ቀን ከሙታን ተለይቶ ተነሥቷል

የጽንሰቱ በዓል ተደርቦበት ነው እንጂ ልናስበው የሚገባ ትልቅ ዕለት ነው።

#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

@zechristos?si=zUG3tBXDKFNQT5i5' rel='nofollow'>አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

@sadorsisay294?si=c13-BuI8aZPW8chG' rel='nofollow'>Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

@sadorudnsador12?_t=8lAVjDFAsIH&_r=1' rel='nofollow'>Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏




Репост из: አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ
#ደብረ__ዘይት

ደብረ ዘይት ማለት የወይራ ዛፍ ያለበት ተራራ ማለት ሲሆን ከኢየሩሳሌም በስተምሥራቅ ጥቂት ኪ.ሜ ራቅ ብሎ የሚገኝ ተራራ ነው።

በብሉይ ኪዳን ዘመን ዳዊት ከአቤሴሎም በሸሸ ጊዜ የደብረ ዘይትን አቀበት እንደ ወጣ እናነባለን 2ሳሙ፡ 15፥30

ዘሩባቤል ከሠራው ቤተ መቅደስ አደባባይ ደብረ ዘይት ሰባ አምስት ሜትር ገደማ ከፍ ብሎ ይገኛል ቤተ ፋጌና ቢታንያ የሚባሉት ታሪካውያን ቦታዎች ከደብረ ዘይት ግርጌ ይገኛሉ።

መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሆሣዕና ዕለት ከደብረ ዘይት ወደ ኢየሩሳሌም እንደ ገባ እናነብባለን። ማር፡ 1፥11

ጌታችን የጸለየበት ጌቴሴማኒ የሚባለው ቦታም ከደብረ ዘይት ሥር ይገኛል። ማቴ፡ 26፥30-36

ጌታችን ወደ ሰማይ ያረገው በደብረ ዘይት ላይ ነው ። ሉቃ፡ 24፥52፤ ሐዋ፡ 1፥12

መድኃኒታችን በደብረ ዘይት ተራራ በዓለም ፍጻሜ ዓለሙን ለማሳለፍ እንደሚመጣ ተተንብዮአል። ዘካ፡ 14፥4

መድኃኒታችንም ነገረ ምጽአቱን/ ዳግም ምጽአቱን በደብረ ዘይት ተራራ ላይ በሰፊው አስተምሯል። ማር፡ 13፥3

በመሆኑም 5ኛው የዐቢይ ጾም ሰንበት የክርስቶስ ነገረ ምጽአት የሚታሰብበት የሚሰበክበት የሚዘመርበት ዕለት ስለ ሆነ በደብረ ዘይት ተሰይሟል ስያሜው የቅዱስ ያሬድ ነው።

መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከመቅደስ ወጥቶ ወደ ደብረ ዘይት በሄደበት ሰዓት ደቀ መዛሙርቱ አጠገቡ ቀርበው ዘሩባቤል ያሳነጸውን የመቅደስ ግንቦች እያሳዩት ሳለ ‹‹እውነት እላችኋለሁ ድንጋይ በድንጋይ ላይ ሳይፈርስ በዚህ አይቀርም›› አላቸው፡፡ ከዚህ በኋላ የኢየሩሳሌምን መፍረስ የእርሱን ዳግም መምጣት አስፍቶ አምልቶ ከነምልክቱ አስተማራቸው።


#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

@zechristos?si=zUG3tBXDKFNQT5i5' rel='nofollow'>አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

@sadorsisay294?si=c13-BuI8aZPW8chG' rel='nofollow'>Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

@sadorudnsador12?_t=8lAVjDFAsIH&_r=1' rel='nofollow'>Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏




Репост из: አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ
🌹🌹🌹🌹🌹🌹ወንጌል🌹🌹🌹🌹🌹🌹

ኢየሱስም ከመቅደስ ወጥቶ ሄደ ደቀ መዛሙርቱም የመቅደሱን ግንቦች ሊያሳዩት ቀረቡ እርሱ ግን መልሶ ይህን ሁሉ ታያላችሁን? እውነት እላችኋለሁ ድንጋይ በድንጋይ ላይ ሳይፈርስ በዚህ አይቀርም አላቸው እርሱም በደብረ ዘይት ተቀምጦ ሳለ ደቀ መዛሙርቱ ለብቻቸው ወደ እርሱ ቀርበው ንገረን ይህ መቼ ይሆናል? የመምጣትህና የዓለም መጨረሻ ምልክቱስ ምንድር ነው? አሉት ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አላቸው ማንም እንዳያስታችሁ ተጠንቀቁ ብዙዎች እኔ ክርስቶስ ነኝ እያሉ በስሜ ይመጣሉና ብዙዎችንም ያስታሉ ጦርንም የጦርንም ወሬ ትሰሙ ዘንድ አላችሁ ይህ ሊሆን ግድ ነውና ተጠበቁ አትደንግጡ ዳሩ ግን መጨረሻው ገና ነው ሕዝብ በሕዝብ ላይ መንግሥትም በመንግሥት ላይ ይነሣልና፥ ራብም ቸነፈርም የምድርም መናወጥ በልዩ ልዩ ስፍራ ይሆናል እነዚህም ሁሉ የምጥ ጣር መጀመሪያ ናቸው በዚያን ጊዜ ለመከራ አሳልፈው ይሰጡአችኋል ይገድሉአችሁማል ስለ ስሜም በአሕዛብ ሁሉ የተጠላችሁ ትሆናላችሁ በዚያን ጊዜም ብዙዎች ይሰናከላሉ እርስ በርሳቸውም አሳልፈው ይሰጣጣሉ እርስ በርሳቸውም ይጣላሉ ብዙ ሐሰተኞች ነቢያትም ይነሣሉ ብዙዎችንም ያስታሉ ከዓመፃም ብዛት የተነሣ የብዙ ሰዎች ፍቅር ትቀዘቅዛለች እስከ መጨረሻ የሚጸና ግን እርሱ ይድናል ለአሕዛብም ሁሉ ምስክር እንዲሆን ይህ የመንግሥት ወንጌል በዓለም ሁሉ ይሰበካል በዚያን ጊዜም መጨረሻው ይመጣል እንግዲህ በነቢዩ በዳንኤል የተባለውን የጥፋትን ርኩሰት በተቀደሰችው ስፍራ ቆሞ ስታዩ፥ አንባቢው ያስተውል በዚያን ጊዜ በይሁዳ ያሉት ወደ ተራራዎች ይሽሹ በሰገነትም ያለ በቤቱ ያለውን ሊወስድ አይውረድ በእርሻም ያለ ልብሱን ይወስድ ዘንድ ወደ ኋላው አይመለስ በዚያችም ወራት ለርጉዞችና ለሚያጠቡ ወዮላቸው ነገር ግን ሽሽታችሁ በክረምት ወይም በሰንበት እንዳይሆን ጸልዩ በዚያን ጊዜ ከዓለም መጀመሪያ ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ ያልሆነ እንግዲህም ከቶ የማይሆን ታላቅ መከራ ይሆናልና እነዚያ ቀኖችስ ባያጥሩ ሥጋ የለበሰ ሁሉ ባልዳነም ነበር ነገር ግን እነዚያ ቀኖች ስለ ተመረጡት ሰዎች ያጥራሉ በዚያን ጊዜ ማንም እነሆ ክርስቶስ ከዚህ አለ ወይም ከዚያ አለ ቢላችሁ አትመኑ ሐሰተኞች ክርስቶሶችና ሐሰተኞች ነቢያት ይነሣሉና ቢቻላቸውስ የተመረጡትን እንኳ እስኪያስቱ ድረስ ታላላቅ ምልክትና ድንቅ ያሳያሉ እነሆ አስቀድሜ ነገርኋችሁ እንግዲህ እነሆ በበረሀ ነው ቢሉአችሁ አትውጡ እነሆ በእልፍኝ ነው ቢሉአችሁ፥ አትመኑ መብረቅ ከምሥራቅ ወጥቶ እስከ ምዕራብ እንደሚታይ የሰው ልጅ መምጣት እንዲሁ ይሆናልና በድን ወዳለበት በዚያ አሞራዎች ይሰበሰባሉ ከዚያች ወራትም መከራ በኋላ ወዲያው ፀሐይ ይጨልማል ጨረቃም ብርሃንዋን አትሰጥም ከዋክብትም ከሰማይ ይወድቃሉ
የሰማያትም ኃይላት ይናወጣሉ በዚያን ጊዜም የሰው ልጅ ምልክት በሰማይ ይታያል በዚያን ጊዜም የምድር ወገኖች ሁሉ ዋይ ዋይ ይላሉ የሰው ልጅንም በኃይልና በብዙ ክብር በሰማይ ደመና ሲመጣ ያዩታል መላእክቱንም ከታላቅ መለከት ድምፅ ጋር ይልካቸዋል ከሰማያትም ዳርቻ እስከ ዳርቻው ከአራቱ ነፋሳት ለእርሱ የተመረጡትን ይሰበስባሉ ምሳሌውንም ከበለስ ተማሩ ጫፍዋ ሲለሰልስ ቅጠልዋም ሲያቈጠቍጥ ያን ጊዜ በጋ እንደ ቀረበ ታውቃላችሁ እንዲሁ እናንተ ደግሞ ይህን ሁሉ ስታዩ በደጅ እንደ ቀረበ እወቁ እውነት እላችኋለሁ ይህ ሁሉ እስኪሆን ድረስ ይህ ትውልድ አያልፍም ሰማይና ምድር ያልፋሉ፥ ቃሌ ግን አያልፍም ስለዚያች ቀንና ስለዚያች ሰዓት ግን ከአባት ብቻ በቀር የሰማይ መላእክትም ቢሆኑ ልጅም ቢሆን የሚያውቅ የለም። ማቴ፡ 24፥1-36

#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

@zechristos?si=zUG3tBXDKFNQT5i5' rel='nofollow'>አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

@sadorsisay294?si=c13-BuI8aZPW8chG' rel='nofollow'>Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

@sadorudnsador12?_t=8lAVjDFAsIH&_r=1' rel='nofollow'>Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏


Репост из: አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ
🌹🌹🌹🌹🌹#ምንባባቱ🌹🌹🌹🌹🌹

#የመጀመርያዉ_ዲያቆን

ነገር ግን ወንድሞች ሆይ ተስፋ እንደሌላቸው እንደ ሌሎች ደግሞ እንዳታዝኑ አንቀላፍተው ስላሉቱ ታውቁ ዘንድ እንወዳለን ኢየሱስ እንደ ሞተና እንደ ተነሣ ካመንን እንዲሁም በኢየሱስ ያንቀላፉቱን እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ያመጣቸዋልና በጌታ ቃል የምንላችሁ ይህ ነውና እኛ ሕያዋን ሆነን ጌታ እስኪመጣ ድረስ የምንቀር ያንቀላፉቱን አንቀድምም ጌታ ራሱ በትእዛዝ በመላእክትም አለቃ ድምፅ በእግዚአብሔርም መለከት ከሰማይ ይወርዳልና በክርስቶስም የሞቱ አስቀድመው ይነሣሉ ከዚያም በኋላ እኛ ሕያዋን ሆነን የምንቀረው ጌታን በአየር ለመቀበል ከእነርሱ ጋር በደመና እንነጠቃለን እንዲሁም ሁልጊዜ ከጌታ ጋር እንሆናለን ስለዚህ እርስ በርሳችሁ በዚህ ቃል ተጽናኑ። 1ኛ ተሰ፡ 4፥13-ፍጻሜ

#ሁለተኛዉ_ዲያቆን

አሁን ያሉ ሰማያትና ምድር ግን እግዚአብሔርን የማያመልኩት ሰዎች እስከሚጠፉበት እስከ ፍርድ ቀን ድረስ ተጠብቀው በዚያ ቃል ለእሳት ቀርተዋል እናንተ ግን ወዳጆች ሆይ፥ በጌታ ዘንድ አንድ ቀን እንደ ሺህ ዓመት ሺህ ዓመትም እንደ አንድ ቀን እንደ ሆነ ይህን አንድ ነገር አትርሱ ለአንዳንዶች የሚዘገይ እንደሚመስላቸው ጌታ ስለ ተስፋ ቃሉ አይዘገይም ነገር ግን ሁሉ ወደ ንስሐ እንዲደርሱ እንጂ ማንም እንዳይጠፋ ወዶ ስለ እናንተ ይታገሣል የጌታው ቀን ግን እንደ ሌባ ሆኖ ይመጣል በዚያም ቀን ሰማያት በታላቅ ድምፅ ያልፋሉ የሰማይም ፍጥረት በትልቅ ትኵሳት ይቀልጣል ምድርም በእርስዋም ላይ የተደረገው ሁሉ ይቃጠላል ይህ ሁሉ እንዲህ የሚቀልጥ ከሆነ፥ የእግዚአብሔርን ቀን መምጣት እየጠበቃችሁና እያስቸኰላችሁ በቅዱስ ኑሮ እግዚአብሔርንም በመምሰል እንደ ምን ልትሆኑ ይገባችኋል? ስለዚያ ቀን ሰማያት ተቃጥለው ይቀልጣሉ የሰማይም ፍጥረት በትልቅ ትኵሳት ይፈታል ነገር ግን ጽድቅ የሚኖርባትን አዲስ ሰማይና አዲስ ምድር እንደ ተስፋ ቃሉ እንጠብቃለን ስለዚህ፥ ወዳጆች ሆይ ይህን እየጠበቃችሁ ያለ ነውርና ያለ ነቀፋ ሆናችሁ በሰላም በእርሱ እንድትገኙ ትጉ የጌታችንም ትዕግሥት መዳናችሁ እንደ ሆነ ቍጠሩ እንዲህም የተወደደው ወንድማችን ጳውሎስ ደግሞ እንደ ተሰጠው ጥበብ መጠን ጻፈላችሁ በመልእክቱም ሁሉ ደግሞ እንደ ነገረ ስለዚህ ነገር ተናገረ። 2ኛ ጴጥ፡ 3፥7-15

#ሁለተኛዉ_ካህን

ከአምስት ቀንም በኋላ ሊቀ ካህናቱ ሐናንያ ከሽማግሌዎችና ጠርጠሉስ ከሚሉት ከአንድ ጠበቃ ጋር ወረደ እነርሱም ስለ ጳውሎስ ለአገረ ገዡ አመለከቱት በተጠራም ጊዜ ጠርጠሉስ ይከሰው ዘንድ ጀመረ እንዲህ እያለ ክቡር ፊልክስ ሆይ በአንተ በኩል ብዙ ሰላም ስለምናገኝ ለዚህም ሕዝብ በአሳብህ በየነገሩ በየስፍራውም መልካም መሻሻል ስለሚሆንለት በፍጹም ምስጋና እንቀበለዋለን ነገር ግን እጅግ እንዳላቆይህ በቸርነትህ በአጭሩ ትሰማን ዘንድ እለምንሃለሁ ይህ ሰው በሽታ ሆኖ በዓለም ባሉት አይሁድ ሁሉ ሁከት ሲያስነሣ፥ የመናፍቃን የናዝራውያን ወገን መሪ ሆኖ አግኝተነዋልና መቅደስንም ደግሞ ሊያረክስ ሲሞክር ያዝነው እንደ ሕጋችንም እንፈርድበት ዘንድ ወደድን ነገር ግን የሻለቃው ሉስዮስ መጥቶ በብዙ ኃይል ከእጃችን ወሰደው ከሳሾቹንም ወደ አንተ ይመጡ ዘንድ አዘዘ፤ አንተም ራስህ እርሱን መርምረህ እኛ ስለምንከስበት ነገር ሁሉ ልታውቅ ትችላለህ አይሁድም ደግሞ፦ ይህ ነገር እንዲሁ ነው እያሉ ተስማሙ ገዡም በጠቀሰው ጊዜ ጳውሎስ መለሰ እንዲህ ሲል ከብዙ ዘመን ጀምረህ ለዚህ ሕዝብ አንተ ፈራጅ እንደ ሆንህ አውቃለሁና ደስ እያለኝ ስለ እኔ ነገር እመልሳለሁ እሰግድ ዘንድ ወደ ኢየሩሳሌም ከወጣሁ ከአሥራ ሁለት ቀን እንዳይበልጥ ልታውቀው ትችላለህ ከአንድም ስንኳ ስነጋገር ወይም ሕዝብን ስሰበስብ በመቅደስ ቢሆን በምኵራብም ቢሆን በከተማም ቢሆን አላገኙኝም አሁንም ስለሚከሱኝ ያስረዱህ ዘንድ አይችሉም ነገር ግን ይህን እመሰክርልሃለሁ በሕጉ ያለውን በነቢያትም የተጻፉትን ሁሉ አምኜ የአባቶቼን አምላክ እነርሱ ኑፋቄ ብለው እንደሚጠሩት መንገድ አመልካለሁ እነዚህም ራሳቸው ደግሞ የሚጠብቁት ጻድቃንም ዓመፀኞችም ከሙታን ይነሡ ዘንድ እንዳላቸው ተስፋ በእግዚአብሔር ዘንድ አለኝ ስለዚህ እኔ ደግሞ በእግዚአብሔርና በሰው ፊት ሁልጊዜ ነውር የሌለባት ሕሊና ትኖረኝ ዘንድ እተጋለሁ ከብዙ ዓመትም በኋላ ለሕዝቤ ምጽዋትና መሥዋዕት አደርግ ዘንድ መጣሁ ይህንም ሳደርግ ሳለሁ ሕዝብ ሳይሰበሰብ ሁከትም ሳይሆን በመቅደስ ስነጻ አገኙኝ ነገር ግን በእኔ ላይ ነገር ያላቸው እንደ ሆነ በፊትህ መጥተው ይከሱኝ ዘንድ የሚገባቸው ከእስያ የመጡ አንዳንድ አይሁድ አሉ ወይም በመካከላቸው ቆሜ ዛሬ ስለ ሙታን መነሣት በፊታችሁ በእኔ ይፈርዱብኛል ብዬ ከጮኽሁት ከዚህ ከአንድ ነገር በቀር በሸንጎ ፊት ቆሜ ሳለሁ በእኔ አንድ ዓመፃ ያገኙ እንደ ሆን እነዚህ ራሳቸው ይናገሩ ፊልክስ ግን የመንገዱን ነገር አጥብቆ አውቆአልና የሻለቃው ሉስዮስ በወረደ ጊዜ ነገራችሁን እቆርጣለሁ ብሎ ወደ ፊት አዘገያቸው። ሐዋ፡ 24፥1-22

#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

@zechristos?si=zUG3tBXDKFNQT5i5' rel='nofollow'>አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

@sadorsisay294?si=c13-BuI8aZPW8chG' rel='nofollow'>Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

@sadorudnsador12?_t=8lAVjDFAsIH&_r=1' rel='nofollow'>Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏




🌹🌹#ደብረ_ዘይት🌹🌹
መዝሙር ዘደብረ ዘይት (ጾመ ድጓ ዘቅዱስ ያሬድ)

ሃሌ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ እንዘ ይነብር እግዚእነ ውስተ ደብረ ዘይት ወይቤሎሙ ለአርዳኢሁ ዑቁኬ ኢያስሕቱክሙ ወንበሩ ድልዋኒክሙ ብዙኃን ይመጽኡ በስምየ እንዘ ይብሉ አነ ውእቱ ክርስቶስ ወዘአዝለፈ ትዕግሥቶ ውእቱ ይድኅን ወአመ ምጽአቱሰ ለወልደ እጓለ እመሕያው ይትከወስ ኲሉ ኃይለ ሰማያት ወምድር አሜሃ ይበክዩ ኲሎሙ ኃጥአነ ምድር ወይወርድ እግዚእነ እምሰማይ ዲበ ምድር በትእዛዙ ወበቃሉ ወበ አዕላፍ መላእክቲሁ በንፍሐተ ቀርን ዘእምኀበ እግዚአብሔር ይምሐረነ አብ በይዕቲ ሰዓት እሞተ ኃጢአት እስመ ገባሬ ሕይወት ውእቱ እግዚኣ ለሰንበት፡፡

ጌታችን በደብረ ዘይት ተራራ ላይ ተቀምጦ ሳለ ለደቀ መዛሙርቱ ማንም እንዳያስታችሁ ተጠንቀቁ ተዘጋጅታችሁም ኑሩ ብዙዎች እኔ ክርስቶስ ነኝ እያሉ በስሜ ይመጣሉ እስከ መጨረሻው የጸና እርሱ ግን ይድናል የሰው ልጅ በሚመጣበት ጊዜ የሰማያትና የምድር ኃይላት ሁሉ ይናወጣሉ ያን ጊዜ በምድር ኃጢአት የአደረጉ ሁሉ ያለቅሳሉ አላቸው ጌታችንም ከባሕርይ አባቱ ከእግዚአብሔር አብ ዘንድ በመለከት ድምፅ ከአእላፍ መላእክት ጋር በግርማ መለኮቱ ከሰማይ ወደ ምድር ይወርዳል በዚች ዕለትም ከሞተ ኃጢአት አብ ይማረን የሕይወት ባለቤት የሰንበትም ጌታ ነውና።


🌹🌹#ምስባክ_ዘደብረ_ዘይት🌹🌹መዝ፡49፥3

እግዚአብሔርሰ ገኀደ ይመጽዕ
ወአምላክነሂ ኢያረምም
እሳት ይነድድ ቅድሜሁ

#ትርጉም
እግዚአብሔር በግልጥ ይመጣል
አምላካችን ዝምም አይልም
እሳትና ፍርድ በፊቱ ነዉና (ይነዳል)


🌹🌹#ምንባባት_ዘመጻጉዕ_ሰንበት🌹🌹

ገባሬ ዲያቆን 1ተሰ፡ 4፥13-ፍጻሜ
ንፍቅ ዲያቆን 2ጴጥ፡ 3፥7-15
ንፍቅ ካህን። ሐዋ፡ 24፥1-22

ወንጌል ማቴ፡ 24፥1-36
#ቅዳሴ_አትናቴዎስ




Репост из: አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ
#የራስ_ቅል_ሥፍራ

"ክርስቶስ በራስ ቅል ሥፍራ ተሰቀለ" ማለት ከዚያ ዘመን ጀምሮ እስከ ምጽአት ድረስ በሚነሱ ክርስቲያኖች ጭንቅላት ውስጥ ክርስቶስ ተሰቅሎ ይኖራል ማለት ነው። በእኔና በእናንተ ጭንቅላት ውስጥ ተሰቅሎ መኖር አለበት ማለት ነው። ፍቅሩ፣ መከራውና የመስቀሉ ነገር በጭንቅላታችን ተቋጥሮ እንዲኖር እንዳንረሳው ምንጊዜም ተቀርጾብን እንዲኖር ነው። አሁንም በጭንቅላታችን ውስጥ ክርስቶስ ተሰቅሎብን ይኖራል አይወርድም። ዛሬ የመስቀሉ ሥፍራ ቀራንዮ አይደለም የእኛ ጭንቅላት ነው። ቀራንዮ ዛሬ ይተረካል እንጂ መስቀሉ የለም። መስቀሉ ያለው በምእመናን ጭንቅላት ውስጥ ነው።

Показано 20 последних публикаций.