አሏህ ሁሉን ዐዋቂ ነው!
በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።
65፥11 "አሏህም ነገሩን ሁሉ ዐዋቂ ነው"፡፡ وَاللَّهُ بِكُلِّ شَيْءٍ عَلِيمٌ
አምላካችን አሏህ ሁሉንም "ነገር" ዐዋቂ ነው፥ "ሸይእ" شَيْء ማለት "ነገር" ማለት ሲሆን ይህም ነገር አጠቃላይ ፍጥረትን ሁሉ ያጠቃልላል፦
65፥11 "አሏህም ነገሩን ሁሉ ዐዋቂ ነው"፡፡ وَاللَّهُ بِكُلِّ شَيْءٍ عَلِيمٌ
ይህ ሆኖ ሳለ ሚሽነሪዎች "ዐሊመሏህ" عَلِمَ اللَّه የሚለው ቃል ወስደው "አሏህ ሁሉን ዐዋቂ ነውን? ብለው ይጠይቃሉ፦
2፥235 አሏህ እናንተ በእርግጥ የምታስታውሷቸው መኾናችሁን ዐወቀ፡፡ عَلِمَ اللَّهُ أَنَّكُمْ سَتَذْكُرُونَهُنَّ
2፥187 አሏህ እናንተ ነፍሶቻችሁን የምትበድሉ መኾናችሁን ዐወቀ፡፡ عَلِمَ اللَّهُ أَنَّكُمْ كُنتُمْ تَخْتَانُونَ أَنفُسَكُمْ
"አሏህ ዐወቀ" ማለት ጥንቱንም አለማወቁን በፍጹም አያሳይም፥ ምክንያቱም አሏህ ዘንድ አላፊ እና መጻዒ ጊዜ ስለሌለ በአሁናዊ ግሥ "አሏህ ዐወቀ" የሚለው ጭራሽ አሏህ ሁሉን ዐዋቂ እንደሆነ ያሳያል። ተመሳሳይ የሰዋስው አወቃቀር ከባይብል በንጽጽር እንመልከት! "የደ ኤሎሂም" יֵּ֖דַע אֱלֹהִֽים ማለት በአሁናዊ ግሥ "አምላክ አወቀ" ማለት ነው፦
ዘጸአት 2፥25 አምላክ የእስራኤልን ልጆች አየ፥ አምላክ በእነርሱ ያለውን ነገር "አወቀ"። וירא אלהים את בני ישראל וידע אלהים׃
"አምላክ ዐወቀ" ማለት ጥንቱንም አለማወቁን በፍጹም አያሳይም፥ ምክንያቱም አምላክ ዘንድ አላፊ እና መጻዒ ጊዜ ስለሌለ በአሁናዊ ግሥ "አምላክ ዐወቀ" የሚለው ጭራሽ አምላክ ሁሉን ዐዋቂ እንደሆነ ያሳያል" ካላችሁ እንግዲያውስ የቁርኣኑን አናቅጽ በዚህ መልክ እና ልክ ተረዱት! በሰፈሩት ቁና መሰፈር ይሉካል እንደዚህ ነው። አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይወፍቀን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።
65፥11 "አሏህም ነገሩን ሁሉ ዐዋቂ ነው"፡፡ وَاللَّهُ بِكُلِّ شَيْءٍ عَلِيمٌ
አምላካችን አሏህ ሁሉንም "ነገር" ዐዋቂ ነው፥ "ሸይእ" شَيْء ማለት "ነገር" ማለት ሲሆን ይህም ነገር አጠቃላይ ፍጥረትን ሁሉ ያጠቃልላል፦
65፥11 "አሏህም ነገሩን ሁሉ ዐዋቂ ነው"፡፡ وَاللَّهُ بِكُلِّ شَيْءٍ عَلِيمٌ
ይህ ሆኖ ሳለ ሚሽነሪዎች "ዐሊመሏህ" عَلِمَ اللَّه የሚለው ቃል ወስደው "አሏህ ሁሉን ዐዋቂ ነውን? ብለው ይጠይቃሉ፦
2፥235 አሏህ እናንተ በእርግጥ የምታስታውሷቸው መኾናችሁን ዐወቀ፡፡ عَلِمَ اللَّهُ أَنَّكُمْ سَتَذْكُرُونَهُنَّ
2፥187 አሏህ እናንተ ነፍሶቻችሁን የምትበድሉ መኾናችሁን ዐወቀ፡፡ عَلِمَ اللَّهُ أَنَّكُمْ كُنتُمْ تَخْتَانُونَ أَنفُسَكُمْ
"አሏህ ዐወቀ" ማለት ጥንቱንም አለማወቁን በፍጹም አያሳይም፥ ምክንያቱም አሏህ ዘንድ አላፊ እና መጻዒ ጊዜ ስለሌለ በአሁናዊ ግሥ "አሏህ ዐወቀ" የሚለው ጭራሽ አሏህ ሁሉን ዐዋቂ እንደሆነ ያሳያል። ተመሳሳይ የሰዋስው አወቃቀር ከባይብል በንጽጽር እንመልከት! "የደ ኤሎሂም" יֵּ֖דַע אֱלֹהִֽים ማለት በአሁናዊ ግሥ "አምላክ አወቀ" ማለት ነው፦
ዘጸአት 2፥25 አምላክ የእስራኤልን ልጆች አየ፥ አምላክ በእነርሱ ያለውን ነገር "አወቀ"። וירא אלהים את בני ישראל וידע אלהים׃
"አምላክ ዐወቀ" ማለት ጥንቱንም አለማወቁን በፍጹም አያሳይም፥ ምክንያቱም አምላክ ዘንድ አላፊ እና መጻዒ ጊዜ ስለሌለ በአሁናዊ ግሥ "አምላክ ዐወቀ" የሚለው ጭራሽ አምላክ ሁሉን ዐዋቂ እንደሆነ ያሳያል" ካላችሁ እንግዲያውስ የቁርኣኑን አናቅጽ በዚህ መልክ እና ልክ ተረዱት! በሰፈሩት ቁና መሰፈር ይሉካል እንደዚህ ነው። አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይወፍቀን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም