ወሒድ የዕቅበተ ኢሥላም መጣጥፍት"Wahid Articles of Islamic Apologetics"


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: не указана


ወንድም ወሒድ በኢሥላም እና በክርስትና መካከል ያለውን ልዩነት እና አንድነት በንጽጽር የሚያስቀምጥ ወንድም ነው። ለዚህም የቋንቋ፣ የሰዋስው፣ የዐውድ፣ የተዛማች እና የሥነ አመክንዮ ሙግት በማቅረብ የሚታወቅ ተሟጋች እና ጦማሪ ነው። ለሙግቱ ነጥብ በዋነኝነት የሚጠቀምባቸው ቋንቋ ዐማርኛ፣ ግዕዝ፣ እንግሊዝኛ፣ ዐረቢኛ፣ ዕብራይስጥ እና ግሪክ ናቸው። መልካም የንባብ፣ የጥናት፣ የማነጻጸር ጊዜ ይሁንልዎ!

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
не указана
Статистика
Фильтр публикаций


"ኑ በጨለማ ተመላለሱ የጥላቻን ሕይወት እንድትቀምሱ"
ቃሉ ኡመቱል ኦርቶዶክሲያህ


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
እዛው ቅኔ ማኅሌት ውስጥ የተቀረጸውን ተመልክታችሁ ፍረዱ! ሺርክ ትልቅ ኃጢአት ነው። የአሏህን ሐቅ አሳልፎ መስጠት ለጀሀነም የሚያዘወትር ዙልም ነው።


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
ሐምሌ 7 ለሚከበረው የሥላሴ ዓመታዊ በዓለ ዋዜማ ሐምሌ 6 ላይ ያለውን ስሙትና ፍረዱ!


አጋእዝተ ዓለም

በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኛ በሆነው፡፡

6፥164 በላቸው «እርሱ አሏህ የሁሉ ነገር ጌታ ሲሆን ከአሏህ በቀር ሌላን ጌታ እፈልጋለሁን? ነፍስም ሁሉ በራሷ ላይ እንጅ ክፉን አትሠራም፡፡ قُلْ أَغَيْرَ ٱللَّهِ أَبْغِى رَبًّۭا وَهُوَ رَبُّ كُلِّ شَىْءٍۢ ۚ وَلَا تَكْسِبُ كُلُّ نَفْسٍ إِلَّا عَلَيْهَا

"እግዚእ" ማለት "ጌታ" ማለት ነው፥ የእግዚእ ብዙ ቁጥር ደግሞ "አጋእዝት" ሲሆን "ጌቶች" ማለት ነው፦
ራእይ 22፥9 ወይቤለኒ፦ “ኢትስግድ ሊተ ዑቅ ዮጊ ገብረ አጋእዝቲከ አነ ወዘአኀዊከ ነቢያት ወዘእለ የዐቅቡ ቃለ ዝንቱ መጽሐፍ። ወአንተሰ ለእግዚአብሔር ስግድ።

በግዕዙ ባይብል "አጋእዝቲከ" የሚል ቃል ያለ ሲሆን "ጌቶችህ" ማለት ነው፥ በግዕዙ ባይብል ላይ መልአኩ ለዮሐንስ "ጌቶችህ" ሲለው በግሪኩ፣ በእንግሊዝኛው እና በዐማርኛው "ጌቶችህ"Your Lods" የሚለው ቃል ይቅርና "ጌታህ"Your Lod" የሚል ቃል የለም። አንድምታው ደግሞ እንደዚህ ይላል፦
ራእይ 22፥9 አንድምታ፦ "ገብረ አጋእዝቲከ አነ"
"የጌቶችህ የሥላሴ ተገዥ ነኝና" "የሐዋርያት ጌቶች የሆኑ የሥላሴ ተገዥ ነኝና"

እዚህ ላይ "አጋእዝት" የተባሉት "ሥላሴ" መሆናቸውን ለማሳየት ዳክረዋል። ለመሆኑ በኦርቶዶክሳዊ ሥላሴ ትምህርት ጽንፈ ዓለምን የሚገዙ ሦስት ጌቶች እንደሆኑ ያውቃሉን? "አጋእዝተ ዓለም" ማለት "የዓለም ጌቶች" ማለት ነው፥ ሐምሌ 7 ቀን አብርሃም ቤት የገቡት ሦስት ሰዎች "የአብርሃሙ ሥላሴ" ተብለው ይታመናሉ፦
ሰይፈ ሥላሴ ዘእሑድ ምዕራፍ 8 ቁጥር 24
"በሦስተኛው ቀን "አጋእዝተ ዓለም ሥላሴ" የአብርሃምን የልቡን ቆራጥነት እና የሰይጣንን ተንኮል ተመልክተው ወደ አብርሃም ቤት ሄዱ"።

"አጋእዝተ ዓለም" የሚለው ይሰመርበት! እውን ዓለም የሚገዛው ጌታ አንድ ነው ወይስ ሦስት? በእርግጥ በኦርቶዶክሳዊ ሥላሴ ትምህርት አብርሃም ቤት የገቡት ሥላሴ ሦስት ጌቶች ናቸው፦
እንዚራ ስብሐት ምዕራፍ 11 ቁጥር 69 “በአንቺ "ሦስቱ ጌቶች" የተጠለሉብሽ በድንኳን አጠገብ የቆምሽ ዕንጨት አንቺ ነሽ”

"ሦስቱ ጌቶች" የሚለው ይሰመርበት! አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በእንዚራ ስብሐት መድብሉ የአብርሃም ድንኳን የማርያም ምሳሌ በማድረግ አስቀምጧል። ታዲያ "ሥላሴ "አንድ ጌታ" ናቸው" ብላችሁ ሕዝቡን ታጃጅሉት ይሆን? በእርግጥም ሥላሴ ሦስት ልዑላን ገዢዎች፥ ሦስት ጌቶች ናቸው፦
ሰይፈ ሥላሴ ዘሐሙስ ምዕራፍ 5 ቁጥር 22-23
“ሦስት ልዑላን ገዢዎች፥ "ሦስት ጌቶች" ናቸው”።

ዓለምን የሚገዙ ሥላሴ ልዑላን ገዢዎች "ሦስት ጌቶች" መሆናቸው የሚያጅብ ነው፦
ገድለ እስጢፋኖስ ዘወርኃ መጋቢት 6፥2
"ያለ አጋእዝተ ዓለም ሥላሴ ቅጠል እንኳን ከግንዱ ተለይቶ አይረግፍምና"።

በኦርቶዶክሳዊ ሥላሴ ትምህርት ስንት እግዚአብሔር አለ? አብርሃም ቤት የገቡት አጋእዝተ ዓለም ሥላሴ ሦስት እግዚአብሔሮች ናቸው፥ እነዚህም ፦
፨ እግዚአብሔር አብ አንዱ እግዚአብሔር
፨ እግዚአብሔር አብ ሁለተኛው እግዚአብሔር
፨ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ሦስተኛው እግዚአብሔር ናቸው።

ሐምሌ 7 ለሚከበረው የሥላሴ ዓመታዊ በዓለ ዋዜማ ሐምሌ 6 ላይ እንዲህ የሚል ዜማ አለ፦
1. "ነአምን ወናመልክ በአሐዱ እግዚአብሔር ዘእምቅድመ ዓለም ሀሎ"

ትርጉም፦ "ከዓለም በፊት በነበረው በአንዱ እግዚአብሔር እናምናለን እናመልካለን"

2. "ወነአምን በካልኡ እግዚአብሔር ዘበምልክናሁ ለአብ ይመስሎ"

ትርጉም፦ "በአምላክነቱ አብን በሚመስለው በሁለተኛው እግዚአብሔር እናምናለን።

3. "ወነአምን በሣልሱ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ዘይመልዕ ኲሎ"

ትርጉም፦ "ሁሉን በሚመላ መንፈስ ቅዱስ በሦስተኛው እግዚአብሔር እናምናለን"

"አንድ እግዚአብሔር" "አንድ ጌታ" ብላችሁ ሕዝቡን ትሸውዱት ይሆን? በእርግጥ ነቢያት እና ሐዋርያት "አንድ እግዚአብሔር" "አንድ ጌታ" ብለው እንጂ "ሦስት ጌቶች" "ሁሉተኛው እግዚአብሔር" "ሦስተኛው እግዚአብሔር" ብለው አላስተማሩም፦
ዘዳግም 6፥4 እስራኤል ሆይ፥ ስማ፤ አምላካችን እግዚአብሔር አንድ እግዚአብሔር ነው።
ማርቆስ 12፥29 ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አለው፦ “ከትእዛዛቱ ሁሉ ፊተኛይቱ፦ ‘እስራኤል ሆይ፥ ስማ፤ ጌታ አምላካችን አንድ ጌታ ነው።

ሕዝቤ ሆይ! ነቢያትም ሐዋርያትም የማታውቋቸውን ሌሎች አማልክት "እናምልክ" ብሎ ቢያስትህ፥ እሺ አትበለው፦
ዘዳግም 13፥7 አንተም አባቶችህም የማታውቋቸውን ሌሎች አማልክት እናምልክ፡ ብሎ ቢያስትህ፥ እሺ አትበለው።

ሥላሴ መድብለ አጋእዝት ነው። አምላካችን አሏህ የሁሉ ነገር ጌታ ሲሆን ከአሏህ በቀር ሌላን ጌታ እፈልጋለሁን? እረ በፍጹም፦
6፥164 በላቸው «እርሱ አሏህ የሁሉ ነገር ጌታ ሲሆን ከአሏህ በቀር ሌላን ጌታ እፈልጋለሁን? ነፍስም ሁሉ በራሷ ላይ እንጅ ክፉን አትሠራም፡፡ قُلْ أَغَيْرَ ٱللَّهِ أَبْغِى رَبًّۭا وَهُوَ رَبُّ كُلِّ شَىْءٍۢ ۚ وَلَا تَكْسِبُ كُلُّ نَفْسٍ إِلَّا عَلَيْهَا

ሥሉሳውያን ክርስቲያኖች ሆይ! ከአጋእዝተ ዓለም ሥላሴ አምልኮ ነጻ ወጥታችሁ በአንድነቱ ሁለትነት ሦስትነት የሌለበትን አንዱን ጌታ አምላክ አሏህን እንድታመልኩ ጥሪያችን ነው። አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።

✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም


አሥ ሠላሙ ዐለይኩም ሙሥሊም ወንድሞቼ እና እኅቶቼ!

የማታ ማታ "የኢየሱስ ምንነት እና ማንነት" የሚለው መጽሐፍ በገበያ ላይ ውሏል። አል-ሐምዱ ሊላህ!

ክርስቲያኖች ሆይ! "ባይብልን አንብቡ" ባላችሁን መሠረት አንብበን ኢየሱስ ፍጡር፣ ሰው፣ መሢሕ፣ ነቢይ፣ መልእክተኛ እና ባሪያ መሆኑን ተረድተን በተገላቢጦሽ እንድታነቡ ጋብዘናችኃል። "ባመጣሽው ዳኛ ትሆኝ እስረኛ" የሚባል አገርኛ ብሂል አለ፥ እንግዲህ እውነቱን መጋፈጥ እንጂ ገሸሽ በማለት እውነትን ማዳፈን አዋጭ አይደለም።

ሙሥሊሞች ሆይ! ሙሥሊም ያልሆኑ አካላትን ወደ ኢሥላም በንጽጽር ለመጣራት ይህ መጽሐፍ "ይጠቅማል" ብዬ ስላሰብኩኝ አንብቡ እና ለክርስቲያኖች አስነብቡ! ወጀዛኩሙላህ ኸይራ!

መጽሐፉን የምትፈልጉ አገር ውስጥ ያላችሁ ሆነ ከአገር ውጪ ያላችሁ በ +251928444408 ዐብዱ መርካቶ ብላችሁ በቀጥታ አሊያም በዋትሳፕ ታገኙታላችሁ፥ እንዲሁ በቴሌ ግራም ይህንን ዩዘር ኔም በመጠቀም http://t.me/merkatozon ማግኘት ትችላላችሁ።

እንዲሁ ቤተል ተቅዋ መሥጂድ ሥር ስለሚገኝ ኩብራ ብላችሁ በመደወል ማግኘት ይችላሉ፦ +251911663699
አየር ጤና አንሷር መሥጂድ ሥር፦ 0963796354

ለብዙዎች ሠበቡል ሂዳያህ ለመሆን ሁሉም ቦታ ሼር አርጉት!
ወጀዛኩሙላህ ኸይራ!


"የተፀነሰው" ለሚለው የገባው ቃል "ጌኔቴን" γεννηθὲν ሲሆን ሥርወ ቃሉ "ጌናኦ" γεννάω ነው፥ የቀጥታ ትርጉም የሚባሉት "Literal Standard Version" እና "Young's Literal Translation" በግልጽ "የተወለደው"begotten" ብለው አስቀምጠውታል። "የተወለደው" ከመንፈስ ቅዱስ አሠራር ነው፥ የአምላክ እስትንፋስ የልዑል ኃይል ሲሆን ወደ ማርያም የመጣበት ምክንያት ይህ ፅንስ ሕይወት እንዲያገኝ ነው፦
ሉቃስ 1፥35 መልአኩም መልሶ እንዲህ አላት፦ “መንፈስ ቅዱስ በአንቺ ላይ ይመጣል፥ የልዑልም ኃይል ይጸልልሻል። καὶ ἀποκριθεὶς ὁ ἄγγελος εἶπεν αὐτῇ Πνεῦμα Ἅγιον ἐπελεύσεται ἐπὶ σέ, καὶ δύναμις Ὑψίστου ἐπισκιάσει σοι·

"መጸለል" ማለት "መጋረድ" ማለት ሲሆን የልዑል ኃይል መንፈስ ቅዱስ ዮሴፍ ቅር ብሎት በስውር ሊተዋት ሲያስብ ከነቄፌታ ጋርዷታል፦
ሉቃስ 1፥35 ስለዚህ "ከ-አንቺ" የሚወለደው ቅዱስ የአምላክ ልጅ ይባላል። διὸ καὶ τὸ γεννώμενον ἅγιον κληθήσεται Υἱὸς Θεοῦ.

"የሚወለደው" ለሚለው የገባው የግሥ መደብ "ጌኖሜኖን" γεννώμενον ሲሆን "ጊኖማይ" γίνομαι ማለትም "ሆነ" ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "የሚሆነው” ማለት ነው። "ከ" የሚለው መስተዋድድ "አንቺ" በሚለው ቃል ላይ መነሻ ሆኖ መግባቱ በራሱ ኢየሱስ ከማርያም መገኘቱን ያሳያል፥ በተጨማሪ "ዲኦ" διὸ ማለት "ስለዚህ"therefore" ማለት ሲሆን ከእርሷ የተገኘው ልጅ የአምላክ እስትንፋስ መንፈስ ቅዱስ ወደ ማርያም በመምጣቱ ምክንያት ነው። አምላክ መንፈሱን ሲልክ ፍጡራን ይፈጠራሉ፦
መዝሙር 104፥30 መንፈስህን ትልካለህ ይፈጠራሉም።

ስለዚህ ወልድ ከአብ ሕይወትን ከተቀበለ ሕይወት አልባ እና በባዶነት የተቀደመ ነው፥ ሕይወት ሳይሰጠው በፊት ህልውና የለውም። ሕይወት ከተቀበለ ደግሞ መነሾ እና ጅማሮ አለው፥ መነሾ እና ጅማሮ ያለው ማንነት ሆነ ምንነት ፍጡር ነው፦
ኢዮብ 31፥15 እኔን በማኅፀን የፈጠረ እርሱንስ የፈጠረው አይደለምን? በማኅፀንስ ውስጥ የሠራን አንድ አይደለንምን? πότερον οὐχ ὡς καὶ ἐγὼ ἐγενόμην ἐν γαστρί, καὶ ἐκεῖνοι γεγόνασι; γεγόναμεν δὲ ἐν τῇ αὐτῇ κοιλίᾳ.

እዚህ አንቀጽ ላይ "የፈጠረ" ለሚለው የገባው ቃል "ኤግኖሚን" ἐγενόμην ሲሆን ማኅፀን ውስጥ ሁሉንም ሰው በእስትንፋሱ የሚፈጥር አንድ ፈጣሪ ስለሆነ አብ ወልድን በመንፈስ ቅዱስ ፈጠረ፦
ሃይማኖተ አበው ምዕራፍ 68 ቁጥር 43
"እግዚአብሔር ሕያው አምላክ በመንፈስ ቅዱስ ሥጋን ፈጠረ"

ይህ በማኅፀን ውስጥ የተፈጠረ ፍጡር ከድንግል የተወለደ፣ ወደ ፊት የሚሞት እና በትንሣኤ ቀን የሚቀሰቀስ ነው፦
19፥33 «ሰላምም በእኔ ላይ ነው፡፡ በተወለድሁ ቀን፣ በምሞትበትም ቀን፣ ሕያው ኾኜ በምቀሰቀስበትም ቀን፡፡»  وَالسَّلَامُ عَلَيَّ يَوْمَ وُلِدتُّ وَيَوْمَ أَمُوتُ وَيَوْمَ أُبْعَثُ حَيًّا

ኢየሱስን በማኅፀን የፈጠረውን አንዱን አምላክ አሏህን እንድታመልኩ ጥሪያች ነው። አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይወፍቀን! አሚን።

✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም


ሕይወትን ሰጠው

በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

19፥33 «ሰላምም በእኔ ላይ ነው፡፡ በተወለድሁ ቀን፣ በምሞትበትም ቀን፣ ሕያው ኾኜ በምቀሰቀስበትም ቀን፡፡»  وَالسَّلَامُ عَلَيَّ يَوْمَ وُلِدتُّ وَيَوْمَ أَمُوتُ وَيَوْمَ أُبْعَثُ حَيًّا

"ሄዩቶ" ἑαυτῷ ማለት "ራስ"own self" ማለት ሲሆን አንድ ምንነት የራሱ ማንነት እንዳለው ለማመላከት የሚል ድርብ ተውላጠ ስም"Reflexive pronoun" ነው፦
ዮሐንስ 11፥51 ይህንም የተናገረ "ከራሱ" አይደለም። τοῦτο δὲ ἀφ’ ἑαυτοῦ οὐκ εἶπεν,

እዚህ አንቀጽ ላይ "ራሱ"himself" ለሚለው የገባው ቃል "ሄዩቱ" ἑαυτοῦ ሲሆን ሊቀ ካህናት የነበረው ቀያፋ የራሱ "እኔነት" እንዳለ አመላካች ነው። ይህንን ከተረዳን ዘንዳ "አብ በራሱ" ሲባል አብ የራሱ እኔነት እንዳለው ሁሉ ወልድም የራሱ እኔነት እንዲኖረው አብ ለወልድ ሕይወትን ሰጠው፦
ዮሐንስ 5፥26 አብ በራሱ ሕይወት እንዳለው እንዲሁ ደግሞ ለወልድ በራሱ እንዲኖረው ሕይወት ሰጥቶታልና። ὥσπερ γὰρ ὁ Πατὴρ ἔχει ζωὴν ἐν ἑαυτῷ, οὕτως καὶ τῷ Υἱῷ ἔδωκεν ζωὴν ἔχειν ἐν ἑαυτῷ.

"ሕይወትን ሰጥቶታልና" የሚለው ይሰመርበት! "ኤዶኬን ዞኤን" ἔδωκεν ζωὴν ማለት "ሕይወት ሰጠው" ማለት ነው። ወልድ በራሱ የራሱ ማንነት እንዲኖረው አብ ለወልድ የሰጠው ሕይወት ነው፥ "አብ ሕይወት አለው" ማለት "አብ ህልውና አለው" ማለት ከሆነ "ወልድ ሕይወት እንዲኖረው" ማለት "ወልድ ህልውና እንዲኖረው" ማለት ነው። እዚህ ዐውድ ላይ "ሕይወት" የተባለው የራስ ሃልዎት"self existence" ነው፥ እያንዳንዱ ማንኛውም ማንነት የራሱ ሃልዎት አለው። አንዱ አምላክ አብ ለእያንዳንዱ ሰው በራሱ ሕይወት እንዲኖረው ሕይወትን ይሰጣል፦
የሐዋያት ሥራ 17፥25 እርሱም ሕይወትን እና እስትንፋስን ሁሉንም ለሁሉ ይሰጣልና። αὐτὸς διδοὺς πᾶσι ζωὴν καὶ πνοὴν καὶ τὰ πάντα·

አብ የሕይወት ምንጭ ስለሆነ አብ የወልድ ሕይወት ምንጭ እና ሥር መሆኑን አንብሮስ ዘሚለን"Ambrose of Milan" ተናግሯል፦
"አብ የወልድ ኑባሬ ምንጭ እና ሥር ነው"
Exposition of the Christian Faith (Ambrose)> Book IV(4) Chapter 10 Number 133

አውግስጢኖስ ዘሂፓ"Augustine of Hippo" አብ ለወልድ ሕይወትን እንደሰጠው አስረግጦ እና ረግጦ ተናግሯል፦
"ያ በመወለድ አብ ለወልድ የሰጠው ሕይወት ከሰጠው ከአብ ሕይወት ጋር አብሮ-ዘላለማዊ ነው"።
On the Trinity(Augustine) Book XV(15) Chapter 26 Number 47
"እንዲህ አለ፦ "በራሱ እንዲኖረው ለወልድ ሕይወት ሰጥቶታልን" በአጭሩም እላለሁኝ፦ "እርሱ(አብ) ወልድን ወልዶታል"።
Tractates on the Gospel of John (Augustine) > Tractate 19 Number 13

ኢየሱስ ሕያው ሆኖ በሕይወት የሚኖረው ሕያው አብ ሕያው ስላረገው ነው፥ ኢየሱስ በሕይወት የሚኖረው በአምላክ ኃይል ነው፦
ዮሐንስ 6፥57 ሕያው አብ እንደ ላከኝ እኔ ከአብ የተነሳ የምኖር ነኝ። καθὼς ἀπέστειλέν με ὁ ζῶν Πατὴρ κἀγὼ ζῶ διὰ τὸν Πατέρα, 
2 ቆሮንቶስ 13፥4 ነገር ግን በአምላክ ኃይል በሕይወት ይኖራል። ἀλλὰ ζῇ ἐκ δυνάμεως Θεοῦ. 

ኢየሱስ አብ ሕይወት ከሰጠው በኃላ ይሞት እና ድጋሚ ሕይወት እንደሚቀበል እራሱ ተናግሯል፦
ዮሐንስ 10፥17 ሕይወቴን "ዳግም" እወስድ ዘንድ አኖራታለውና ስለዚህ አብ ይወደኛል። διὰ τοῦτό με ὁ Πατὴρ ἀγαπᾷ ὅτι ἐγὼ τίθημι τὴν ψυχήν μου, ἵνα πάλιν λάβω αὐτήν.

"ፓሊን" πάλιν ማለት "ድጋሚ" "ሁለተኛ" "ዳግም"again" ማለት ነው፥ ድጋሚ ሕይወቱን እንደሚቀበል መናገሩ በራሱ መጀመሪያ ሕይወት እንደተሰጠው አመላካች ነው። "አኖራታለውና" ማለቱ ወልድ ሕይወቱን በጽድቅ ለሚፈርደው ለአብ እንደሚሰጥ ነው፥ ነፍሱን ከሰጠ በኃላ ይሞታል። ከሞተ በኃላ "ድጋሚ" ሕይወትን ከአብ ይቀበላል፦
ዮሐንስ 10፥18 እኔ በራሴ አኖራለው እንጂ ከእኔ ማንም አይወስዳትም። ላኖራት ሥልጣን አለኝ "ዳግምም" ልቀበላት ሥልጣን አለኝ ይህችን ትእዛዝ ከአባቴ ተቀበልሁ። οὐδεὶς ἦρεν αὐτὴν ἀπ’ ἐμοῦ, ἀλλ’ ἐγὼ τίθημι αὐτὴν ἀπ’ ἐμαυτοῦ. ἐξουσίαν ἔχω θεῖναι αὐτήν, καὶ ἐξουσίαν ἔχω πάλιν λαβεῖν αὐτήν· ταύτην τὴν ἐντολὴν ἔλαβον παρὰ τοῦ Πατρός μου.

ሕይወት ዳግም እንደሚቀበል መናገሩ ቅድሚያ ሕይወት እንደተሰጠው አመላካች ነው። እንደ ባይብሉ ፈጣሪ ለፍጡሩ ሕይወትን የሚሰጠው በአፉ እስትንፋስ ነው፦
ኢዮብ 33፥4 የያህዌህ መንፈስ ፈጠረችኝ፥ የሁሉን ቻዩ እስትንፋስ ሕይወት ሰጠችኝ። רֽוּחַ־אֵ֥ל עָשָׂ֑תְנִי וְנִשְׁמַ֖ת שַׁדַּ֣י תְּחַיֵּֽנִי׃

በአንስታይ የሴት አንቀጽ የተቀመጡት የግሥ መደብ "ዓሳቴኒይ" עָשָׂתְנִי ማለት "ፈጠረችኝ" ሲሆን "ታሐዪኒይ" תְּחַיֵּֽנִי ማለት ደግሞ "ሕይወትን ሰጠችኝ" ነው፥ ከአፉ የሚወጣው እስትንፋስ ማርያም ማኅፀን ውስጥ ፅንስ እንዲፈጠር ምክንያት ሆኗል፦
ማቴዎስ 1፥20 ከእርስዋ የተፀነሰው ከመንፈስ ቅዱስ ነውና። τὸ γὰρ ἐν αὐτῇ γεννηθὲν ἐκ Πνεύματός ἐστιν Ἁγίου·


ደርሥ በትግሪኛ ተለቋል። ትግሪኛ ተናጋሪዎች ሠበቡል ሂዳያህ ለመሆን አንብቡ አስነብቡ፦ https://t.me/wahidtigriga/43

ወጀዛከላህ ኸይራ!


የተሰደሩ መጣጥፋት
ክፍል አንድ
ክፍል ሁለት
ክፍል ሦስት
ክፍል አራት
ክፍል አምስት
ክፍል ስድስት

ባይጠቅምም አይጎዳም። ለሌሎች ሠበቡል ሂዳያህ ይሆን ይሆናል። ኢንሻላህ!


ኢየሱስ አልተፈጠረምን?

በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

3፥47 ፦ "ጌታዬ ሆይ! ሰው ያልነካኝ ስኾን ለኔ እንዴት ልጅ ይኖረኛል? አለች፡፡ "ነገሩ እንዳልሽው ነው፡፡ አሏህ የሚሻውን ይፈጥራል፡፡ አንዳችን በሻ ጊዜ ለእርሱ ኹን ይለዋል፤ ወዲውኑም ይኾናል" አላት፡፡ قَالَتْ رَبِّ أَنَّىٰ يَكُونُ لِى وَلَدٌۭ وَلَمْ يَمْسَسْنِى بَشَرٌۭ ۖ قَالَ كَذَٰلِكِ ٱللَّهُ يَخْلُقُ مَا يَشَآءُ ۚ إِذَا قَضَىٰٓ أَمْرًۭا فَإِنَّمَا يَقُولُ لَهُۥ كُن فَيَكُونُ

በ325 ድኅረ ልደት በንጉሥ ቆስጠንጢኖስ ሊቀ መንበርነት የኒቂያ ጉባኤ ላይ 318 ኤጲጵ ቆጶሳት ከመላው ዓለም ተሰብስበው ጉባኤው የማታ ማታ ኢየሱስ "ቴዎን ኤክ ቴዉ" Θεὸν ἐκ Θεοῦ ማለትም "ከአምላክ የተገኘ አምላክ ነው" በማለት አጸደቀ፥ ቅሉ እና ጥቅሉ ግን ከአምላክ ፍጡር ሰው እንጂ አምላክ አይገኝም። ሔዋን፦ "ሰው ከያህዌህ አገኘሁ” አለች፦
ዘፍጥረት 4፥1 እርስዋም፦ “ሰው ከያህዌህ አገኘሁ” አለች። וַתֹּ֕אמֶר קָנִ֥יתִי אִ֖ישׁ אֶת־יְהוָֽה׃

"አገኘሁ" ለሚለው የገባው ቃል "ካኒቲ" קָנִ֥יתִי ሲሆን ያገኘችው ወንድ ልጅ ከአምላክ የተፈጠረ ሰው መሆኑን ጉልኅ ማሳያ ነው። ኢየሱስም በትንቢት መነጽር "ያህዌህ ፈጠረኝ" በማለት ተናግሯል፦
ምሳሌ 8፥22 "ያህዌህ ፈጠረኝ"። יְֽהוָ֗ה קָ֭נָנִי

"ካናኒ" קָ֭נָנִי ማለት "አስገኘኝ" "ፈጠረኝ" ማለት ነው፥ "ካናህ" קָנָה ማለት "ፈጠረ" በሚል ብዙ ቦታ መጥቷል፥ ለምሳሌ፦
መዝሙር 139፥13 አቤቱ አንተ ኵላሊቴን "ፈጥረሃልና"።  כִּֽי־אַ֭תָּה קָנִ֣יתָ כִלְיֹתָ֑י

እዚህ አንቀጽ ላይ "ፈጥረሃልና" ለሚለው የገባው ቃል "ካኒታ" קָנִ֣יתָ ሲሆን ሥርወ ቃሉ "ካናህ" קָנָה ነው፥ ስለዚህ ኢየሱስ ፍጡር መሆኑን በማያሻማ መልኩ የሚያሳይ ነው። በግሪክ ሰፕቱአጀንት ላይም "ፈጠረኝ" በማለት ተርጉመውታል፦
ምሳሌ 8፥22 "ጌታ ፈጠረኝ"። κύριος ἔκτισέν με

"ኤክቲሴን ሜ" ἔκτισέν με ማለት "ፈጠረኝ" ማለት ነው፥ "ኤክቲሴን" ἔκτισέν በግሪክ ሰፕቱአጀንት ለሰው አፈጣጠር ብዙ ቦታ ውሏል። ለምሳሌ፦
ሚልክያስ 2፥10 አንድ አምላክስ "የፈጠረን" አይደለምን? οὐχὶ Θεὸς εἷς ἔκτισεν ὑμᾶς;

እዚህ አንቀጽ ላይ "የፈጠረ" ለሚለው የገባው ቃል "ኤክቲሴን" ἔκτισέν መሆኑን ልብ አድርግ! ግዕዙም በግልጽ "ፈጠረኝ" ብሎ አስቀምጦታል፦
ምሳሌ 8፥22 "ፈጠረኒ እግዚእ መቅድመ ተግባሩ"።

"ፈጠረኒ" ማለት "ፈጠረኝ" ማለት እንጂ ሌላ ማለት አይደለም፥ "ቃናኒ" קָ֭נָנִי ማለት "ፈጠረኝ" ማለት ባይሆን ኖሮ ግሪኩ እና ግዕዙ እንዴት ሊሳሳት ይችላል? የዐማርኛ የትርጉም ሥራዎችም "ፈጠረኝ" ብለው አስቀምጠዋል፦
፨ ምሳሌ 8፥22 "እግዚአብሔር ከሁሉ በፊት ፈጠረኝ"።
1980 አዲስ ትርጉም

፨ ምሳሌ 8፥22 "እግዚአብሔር ለሥራው የመንገዱ መጀመሪያ አድርጎ ፈጠረኝ"።
2000 ዕትም ሰማንያ አሐዱ

ብዙ የእንግሊዝኛ ትርጉምም "ፈጠረኝ" ብለው አስቀምጠዋል፥ ለምሳሌ፦
1. New American Standard Bible
“The LORD created me"
2. Good News Translation
"The LORD created me"
3. Majority Standard Bible
"The LORD created me"
4. NET Bible
"The LORD created me"
5. New Revised Standard Version
"The LORD created me"
6. New Heart English Bible
"The LORD created me"

ኤዎስጣቴዎስ ዘአንጾኪያ"Eustathius of Antioch" በ 337 ድኅረ ልደት " ጌታ ፈጠረኝ" የሚለው ድንግል ማርያም ማኅፀን ውስጥ መፈጠሩን ለማሳየት አስቀምጦታል፦
"በድንግል ማኅፀን በመንፈስ ቅዱስ ተተከለ፥ ከሴትም ሰው ሆኖ ተወለደ። በመጽሐፍ፦ "በመንገዱ መጀመሪያ ጌታ ፈጠረኝ" ይላልና"።
Eustathius of Antioch on proverb 8፥22

አንብሮስ ዘሚለን"Ambrose of Milan" በ 397 ድኅረ ልደት "ጌታ ፈጠረኝ" የሚለውን "ኢየሱስ ከድንግል ተፈጠረ" በሚል ፈሥሮታል፦
"የተሠግዎት ትንቢቱን በዚህ እንረዳለን፦ "በመንገዱ መጀመሪያ ጌታ ፈጠረኝ" የሚለውን ጌታ ኢየሱስ ከድንግል ተፈጠረ ማለት ነው"።
Ambrose of Milan on proverb 8፥22

ባስልዮስ ዘቂሳሪያ"Basil of Caesarea" በ 360 ድኅረ ልደት “ፈጠረኝ” ማለት ሰው ስለ መሆኑ ተርጉሞታል፦
ሃይማኖተ አበው ምዕራፍ 32 ቁጥር 18
“ፈጠረኝ” ማለት ሰው ስለ መሆኑ ይተረጎማል"።

ቄርሎስ ዘእስክንድርያ"Cyril of Alexandria" በ 431 ድኅረ ልደት በተመሳሳይ “ፈጠረኝ” ማለት ሰው ስለ መሆኑ ተርጉሞታል፦
ሃይማኖተ አበው ምዕራፍ 124 ቁጥር 25
"በእውነት ሰው ስለመሆኑ “እግዚአብሔር ፈጠረኝ” ይላል።

"ጌታ" ባለቤት ሲሆን ኢየሱስ ተሳቢ ነው፥ በባለቤት እና በተሳቢ መካከል "ፈጠረኝ" የሚል ተሻጋሪ ግሥ"transitive verb" አለ። ይህም ፈጣሪ እና ፍጡር ሁለት የተለያየ ማንነት እና ምንነት መሆናቸውን ቁልጭ አርጎ የሚያሳይ ነው፥ ፈጣሪ እራሱን የቻለ ኑባሬ ሲሆን ፍጡር የፈጣሪ ጥገኛ ኑባሬ ነው። ጌታ በማኅፀን ውስጥ የፈጠረው ፍጡር የመርየምን ልጅ ዒሣን ነው፦
3፥47 ፦ "ጌታዬ ሆይ! ሰው ያልነካኝ ስኾን ለኔ እንዴት ልጅ ይኖረኛል? አለች፡፡ "ነገሩ እንዳልሽው ነው፡፡ አሏህ የሚሻውን ይፈጥራል፡፡ አንዳችን በሻ ጊዜ ለእርሱ ኹን ይለዋል፤ ወዲውኑም ይኾናል" አላት፡፡ قَالَتْ رَبِّ أَنَّىٰ يَكُونُ لِى وَلَدٌۭ وَلَمْ يَمْسَسْنِى بَشَرٌۭ ۖ قَالَ كَذَٰلِكِ ٱللَّهُ يَخْلُقُ مَا يَشَآءُ ۚ إِذَا قَضَىٰٓ أَمْرًۭا فَإِنَّمَا يَقُولُ لَهُۥ كُن فَيَكُونُ

ኢየሱስን የፈጠረ ጌታ አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይወፍቀን! አሚን።

✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
የአሏህ እጆች


እዚህ አንቀጽ ላይ ማርያም እና አሮን ሁለት ማንነት ሆነው ሳለ በነጠላ ግሥ "ትዳቤር" תְּדַבֵּ֨ר እንጂ በብዜት "ዮምሩ" יֹּאמְר֖וּ አልተባሉም፥ "ትዳቤር" תְּדַבֵּ֨ר ማለት በነጠላ "ተናገረ" ማለት ሲሆን "ዮምሩ" יֹּאמְר֖וּ ደግሞ በብዜት "ተናገሩ" ማለት ነው። እናማ ያህዌህን እና መልአኩን በነጠላ ግሥ "ይቫሬኽ"  יְבָרֵךְ֮ ስለተባሉ አንድ ማንነት ናቸው ካልን እንግዲያውስ ማርያም እና አሮን በነጠላ ግሥ "ትዳቤር" תְּדַבֵּ֨ר ስለተባሉ አንድ ማንነት ናቸውን? እንቀጥል፦
1ኛ ሳሙኤል 26፥7 ዳዊት እና አቢሳ ወደ ሕዝቡ በሌሊት "መጡ"። וַיָּבֹא֩ דָוִ֨ד וַאֲבִישַׁ֥י ׀ אֶל־הָעָם֮ לַיְלָה֒ 

እዚህ አንቀጽ ላይ ዳዊት እና አቢሳ ሁለት ማንነት ሆነው ሳለ በነጠላ ግሥ "ያቮ"  יָּבֹא֩ እንጂ በብዜት "ያቮኡ" יָּבֹ֥אוּ አልተባሉም፥ "ያቮ"  יָּבֹא֩  תְּדַבֵּ֨ר ማለት በነጠላ "መጣ" ማለት ሲሆን "ያቮኡ" יָּבֹ֥אוּ ደግሞ በብዜት "መጡ" ማለት ነው። ያህዌህን እና መልአኩን በነጠላ ግሥ "ይቫሬኽ"  יְבָרֵךְ֮ ስለተባሉ አንድ ማንነት ናቸው ካልን እንግዲያውስ ዳዊት እና አቢሳ በነጠላ ግሥ "ያቮ"  יָּבֹא֩ ስለተባሉ አንድ ማንነት ናቸውን? አንድ ናሙና እንጨምር፦
ዘኍልቍ 20፥8 በትርህን ውሰድ! አንተ እና ወንድምህ አሮን ማኅበሩን "ሰብስቡ"። קַ֣ח אֶת־הַמַּטֶּ֗ה וְהַקְהֵ֤ל אֶת־הָעֵדָה֙ אַתָּה֙ וְאַהֲרֹ֣ן אָחִ֔יךָ

እዚህ አንቀጽ ላይ ሙሴ እና አሮን ሁለት ማንነት ሆነው ሳለ በነጠላ ግሥ "ሀክሀል" הַקְהֵ֤ל እንጂ በብዜት "ሊክቱ" לִקְט֣וּ አልተባሉም፥ "ሀክሀል" הַקְהֵ֤ל ማለት በነጠላ "ሰብስብ" ማለት ሲሆን "ሊክቱ" לִקְט֣וּ ደግሞ በብዜት "ሰብስቡ" ማለት ነው። ያህዌህን እና መልአኩን በነጠላ ግሥ "ይቫሬኽ"  יְבָרֵךְ֮ ስለተባሉ አንድ ማንነት ናቸው ካልን እንግዲያውስ ሙሴ እና አሮን በነጠላ ግሥ "ሀክሀል" הַקְהֵ֤ל ስለተባሉ አንድ ማንነት ናቸውን?

የኢየሱስ አምላክ አብ እና የአምላክ መልእክተኛ ወልድ ሁለት የተለያዩ ለየቅል ማንነት ቢሆንም "ያቅና" በሚል ነጠላ ግሥ መጥቷል፦
1ኛ ተሰሎንቄ 3፥11 አሁን ራሱ አምላካችንና አባታችን እና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ እናንተ መንገዳችንን ያቅና። Αὐτὸς δὲ ὁ Θεὸς καὶ Πατὴρ ἡμῶν καὶ ὁ Κύριος ἡμῶν Ἰησοῦς κατευθύναι τὴν ὁδὸν ἡμῶν πρὸς ὑμᾶς·

ለአንባቢያን እንዳይንዛዛ እንጂ ብዙ የሰዋስው ናሙናዎችን ማቅረብ ይቻል ነበር። ያዕቆብ "ከክፉ ነገር ሁሉ ያዳነኝ መልአክ" ሲል አንዱ አምላክ መልአክን እየላከ በመልአክ ያድናል ማለት እንጂ መልአኩ በራሱ ያድናል ማለት አይደለም፦
ዳንኤል 3፥28 ቡከደነፆርም አለ፦ "መልአኩን የላከ የሲድራቅ፣ የሚሳቅ እና የአብደናጎ አምላክ ይባረክ! በእርሱ የታመኑትን ባሪያዎቹን "ያዳነ" ነው። עָנֵ֨ה נְבֽוּכַדְנֶצַּ֜ר וְאָמַ֗ר בְּרִ֤יךְ אֱלָהֲהֹון֙ דִּֽי־שַׁדְרַ֤ךְ מֵישַׁךְ֙ וַעֲבֵ֣ד נְגֹ֔ו דִּֽי־שְׁלַ֤ח מַלְאֲכֵהּ֙ וְשֵׁיזִ֣ב לְעַבְדֹ֔והִי דִּ֥י הִתְרְחִ֖צוּ עֲלֹ֑והִי
ዳንኤል 6፥22 አምላኬ መልአኩን ልኮ የአንበሶችን አፍ ዘጋ፥ እነርሱም አልጐዱኝም። אֱלָהִ֞י שְׁלַ֣ח מַלְאֲכֵ֗הּ וּֽסֲגַ֛ר פֻּ֥ם אַרְיָוָתָ֖א וְלָ֣א חַבְּל֑וּנִי

ተግባባን መሰለኝ? አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።

✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም


ፈጣሪ እና መልአክ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

33፥56 አሏህ እና መላእክቱ በነቢዩ ላይ የአክብሮት እዝነትን ያወርዳሉ፡፡ إِنَّ اللَّهَ وَمَلَائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى النَّبِيِّ

"ሶለዋህ" صَلَوٰة የሚለው ቃል "ሶላ" صَلَّى ማለትም "ባረከ" ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "ቡራኬ" "ረድኤት" በሚል ይመጣል፥ ለምሳሌ፦
33፥56 አሏህ እና መላእክቱ በነቢዩ ላይ የአክብሮት እዝነትን ያወርዳሉ፡፡ إِنَّ اللَّهَ وَمَلَائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى النَّبِيِّ

መላእክት ከአሏህ ጋር በመስተጻም ተጫፍረው እና ተዛርፈው መምጣታቸው ከአሏህ ጋር የማንነት እና የምንነት ልዩነት እንደሌላቸው አያመላክትም። ለምሳሌ በባይብል፦ ፈጣሪ ከፍጡር ጋር ስግደት የተቀበለበት ጥቅስ እንመልከት፦
1ኛ ዜና 29፥20 ራሳቸውንም አዘንብለው ለያህዌህ እና ለንጉሡ ሰገዱ። וַיִּקְּד֧וּ וַיִּֽשְׁתַּחֲו֛וּ לַיהוָ֖ה וְלַמֶּֽלֶךְ׃

ንጉሡ የተባለው ዳዊት ሲሆን "ሰገዱ" በሚል በአንድ ግሥ እና "እና" በሚል መስተጻምር ተጫፍሮ መጥቷል። በተጨማሪም፦
ምሳሌ 24፥21 ልጄ ሆይ! ያህዌህን እና ንጉሥን ፍራ። יְרָֽא אֶת־ יְהוָ֣ה בְּנִ֣י וָמֶ֑לֶךְ
ምሳሌ 24፥22 መከራቸው ድንገት ይነሣልና፥
ከሁለቱ የሚመጣውን ጥፋት ማን ያውቃል? כִּֽי־פִ֭תְאֹם יָק֣וּם אֵידָ֑ם וּפִ֥יד נֵיהֶ֗ם מִ֣י יֹודֵֽעַ׃ ס

ይህንን ከተረዳን ዘንዳ ወደ ዋናው ነጥብ እንግባ! ያህዌህ አብርሃምን ከከለዳውያን ዑር ካወጣው በኃላ "እኔ ኤልሻዳይ ነኝ፤ በፊቴ ሂድ፥ ፍጹምም ሁን" አለው፦
ዘፍጥረት 15፥7 ይህችን ምድር ትወርሳት ዘንድ እንድሰጥህ ከከለዳውያን ዑር ያወጣሁህ ያህዌህ እኔ ነኝ" አለው። וַיֹּ֖אמֶר אֵלָ֑יו אֲנִ֣י יְהוָ֗ה אֲשֶׁ֤ר הֹוצֵאתִ֙יךָ֙ מֵא֣וּר כַּשְׂדִּ֔ים לָ֧תֶת לְךָ֛ אֶת־הָאָ֥רֶץ הַזֹּ֖את לְרִשְׁתָּֽהּ׃
ዘፍጥረት 17፥1 አብራምም የዘጠና ዘጠኝ ዓመት ሰው በሆነ ጊዜ ያህዌህ ለአብራም ተገለጠለትና፦ “እኔ ኤልሻዳይ ነኝ፤ በፊቴ ሂድ፥ ፍጹምም ሁን" አለው። וַיְהִ֣י אַבְרָ֔ם בֶּן־תִּשְׁעִ֥ים שָׁנָ֖ה וְתֵ֣שַׁע שָׁנִ֑ים וַיֵּרָ֨א יְהוָ֜ה אֶל־אַבְרָ֗ם וַיֹּ֤אמֶר אֵלָיו֙ אֲנִי־אֵ֣ל שַׁדַּ֔י הִתְהַלֵּ֥ךְ לְפָנַ֖י וֶהְיֵ֥ה תָמִֽים׃

"በፊቴ ሂድ" የሚለው ይሰመርበት! በመቀጠል ያህዌህ መልአኩን ወደ አብርሃም ሎሌ በፊቱ እንደላከ ይናገራል፦
ዘፍጥረት 24፥7 ከአባቴ ቤት ከተወለድሁባት ምድርም ያወጣኝ፦ "ይህችንም ምድር እሰጥሃለሁ’ ብሎ የነገረኝ እና የማለልኝ የሰማይ አምላክ ያህዌህ እርሱ መልአኩን በፊትህ ይልካል፥ ከዚያም ለልጄ ሚስትን ትወስዳለህ። יְהוָ֣ה ׀ אֱלֹהֵ֣י הַשָּׁמַ֗יִם אֲשֶׁ֨ר לְקָחַ֜נִי מִבֵּ֣ית אָבִי֮ וּמֵאֶ֣רֶץ מֹֽולַדְתִּי֒ וַאֲשֶׁ֨ר דִּבֶּר־לִ֜י וַאֲשֶׁ֤ר נִֽשְׁבַּֽע־לִי֙ לֵאמֹ֔ר לְזַ֨רְעֲךָ֔ אֶתֵּ֖ן אֶת־הָאָ֣רֶץ הַזֹּ֑את ה֗וּא יִשְׁלַ֤ח מַלְאָכֹו֙ לְפָנֶ֔יךָ וְלָקַחְתָּ֥ אִשָּׁ֛ה לִבְנִ֖י מִשָּֽׁם׃

የሰማይ አምላክ ያህዌህ እና መልአኩ ሁለት ለየቅል ማንነት እና ምንነት እንደሆኑ እዚህ ጥቅስ ላይ ቁልጭ ብሎ ይታያል። አብርሃም አካሄዱን በፊት ያደረገለት ያህዌህ አምላክ እና መልአኩ በኑባሬ አሁንም ተለያይተዋል፦
ዘፍጥረት 24፥40 እርሱም አለኝ፦ ‘አካሄዴን በፊቱ ያደረግሁለት ያህዌህ መልአኩን ከአንተ ጋር ይልካል። וַיֹּ֖אמֶר אֵלָ֑י יְהוָ֞ה אֲשֶׁר־הִתְהַלַּ֣כְתִּי לְפָנָ֗יו יִשְׁלַ֨ח מַלְאָכֹ֤ו אִתָּךְ֙

"አካሄዴን በፊቱ ያደረግሁለት ያህዌህ" የሚለው ይሰመርበት! አብርሃም እና ይስሐቅ በፊቱ የሄዱለት አምላክ ያህዌህ ያዕቆብን ከታናሽነቱ ጀምሮ እስከ ትልቅነቱ ድረስ የመገበው አምላክ ነው፦
ዘፍጥረት 48፥15 ያዕቆብም ዮሴፍን ባረከ እንዲህም አለ፦ “አባቶቼ አብርሃምና ይስሐቅ በፊቱ የሄዱለት አምላክ፥ ከታናሽነቴ ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ እኔን የመገበኝ አምላክ። וַיְבָ֥רֶךְ אֶת־יֹוסֵ֖ף וַיֹּאמַ֑ר הָֽאֱלֹהִ֡ים אֲשֶׁר֩ הִתְהַלְּכ֨וּ אֲבֹתַ֤י לְפָנָיו֙ אַבְרָהָ֣ם וְיִצְחָ֔ק הָֽאֱלֹהִים֙ הָרֹעֶ֣ה אֹתִ֔י מֵעֹודִ֖י עַד־הַיֹּ֥ום הַזֶּֽה׃

አብርሃም እና ይስሐቅ በፊቱ የሄዱለት አምላክ ያህዌህ ሲልከው የነበረው መልአክ በአመልካች መስተአምር "ሀ ማላኽ" הַמַּלְאָךְ֩ ተብሎ ከያህዌህ ጋር በነጠላ ግሥ ተጫፍሮ እና ተዛርፎ መጥቷል፦
ዘፍጥረት 48፥16 ከክፉ ነገር ሁሉ ያዳነኝ መልአክ እነዚህን ብላቴኖች "ይባርኩ"። הַמַּלְאָךְ֩ הַגֹּאֵ֨ל אֹתִ֜י מִכָּל־רָ֗ע יְבָרֵךְ֮ אֶת־הַנְּעָרִים֒

ያዕቆብ ያህዌህን እና መልአኩን በነጠላ ግሥ "ይቫሬኽ" יְבָרֵךְ֮ መባሉ በውስጠ ታዋቂነት "ይባርኩ" የሚል ፍቺ ይኖረዋል፥ "ይቫሬኽ" יְבָרֵךְ֮ ማለት "ይባርክ" ማለት ሲሆን ያህዌህ አምላክ እና የእርሱ መልአክ ሁለት ማንነት ናቸውና። "አምላክ እና መልአኩ ሁለት ማንነት ከነበሩ በብዜት ግሥ "ይትቫርኹ" יתברכו ማለትም "ይባርኩ" ለምን አልተባለም? የሚል ጥያቄ ከተነሳ ይህ በዕብራይስጥ ሰዋስው ውስጥ የተለመደ አወቃቀር ነው፦
ዘኍልቍ 12፥1 ሙሴም ኢትዮጵያይቱን አግብቶአልና ባገባት በኢትዮጵያይቱ ምክንያት ማርያም እና አሮን በእርሱ ላይ "ተናገሩ"። וַתְּדַבֵּ֨ר מִרְיָ֤ם וְאַהֲרֹן֙ בְּמֹשֶׁ֔ה עַל־אֹדֹ֛ות הָאִשָּׁ֥ה הַכֻּשִׁ֖ית אֲשֶׁ֣ר לָקָ֑ח כִּֽי־אִשָּׁ֥ה כֻשִׁ֖ית לָקָֽח׃


ይህ የዳዒ ዒምራን የይቱብ ቻናል ነው፦
https://youtube.com/@emranapologetics?si=YOHGjXbcxquJV16h

ሙሥሊም ወንድሞቼ እና እኅቶቼ መልእክቱ ተደራሽነት እንዲኖረው ላይክ፣ ኮሜንት፣ ሼር እና ሰብስክራይብ በማድረግ የአጅሩ ተካፋይ እንሁን። ወጀዛኩሙላህ ኸይራ!


የምርኮ ገንዘብ

በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

8፥1 ከአንፋል ይጠይቁሃል፡፡ በል፦ «አንፋል የአሏህ እና የመልእክተኛው ናቸው፡፡» يَسْأَلُونَكَ عَنِ الْأَنفَالِ ۖ قُلِ الْأَنفَالُ لِلَّهِ وَالرَّسُولِ

የግጭት አዙሪት እና የጭቅጭቅ ቀለበት አባዜ የተጠናወታቸው ሚሽነሪዎች "ቁርኣን ዝረፉ ይላል" በማለት መጥኔ የሌለው ሥርዋጽ ሲለቁ እያየን ነው፥ የመካከለኛው ምሥራቅ ትኩሳት ተስታኮ ለማሳጣት ሾርኔ መሆኑ ነው። "ጅብ በቀደደው ውሻ ይገባል" ነውና ነገሩ መስመር የሳተ አስተሳሰብ ቢሆንም ጥሩ የውይይት ማሳለጫ ነው፥ ከከርሞ ዘንድሮ ለያዥ ለገናዥ በማያመች መልኩ ቅሌቱ ቢያገረሽባቸውም እኛ ደግሞ "ከፋህም ከረፋህም" ሳንል መልስ እንሰጣለን።
"ነፈል" نَفَل የሚለው ቃል"ነፈለ" نَفَلَ ማለትም "ማረከ" ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "ምርኮ" ማለት ነው፥ የነፈል ብዙ ቁጥር ደግሞ "አንፋል" أَنفَال ሲሆን "ምርኮዎች" ማለት ነው፦
8፥1 ከአንፋል ይጠይቁሃል፡፡ በል፦ «አንፋል የአሏህ እና የመልእክተኛው ናቸው፡፡» يَسْأَلُونَكَ عَنِ الْأَنفَالِ ۖ قُلِ الْأَنفَالُ لِلَّهِ وَالرَّسُولِ

እዚህ አንቀጽ ላይ በዐማርኛ ትርጉም ላይ "የጦር ዘረፋ" "የዘረፋ ገንዘብ" ተብሎ የተቀመጠው ቃል "አል አንፋል" الْأَنفَال ሲሆን በቀላሉ ከጦነት በኃላ የሚገኙ "ምርኮዎች" ናቸው፥ 8ኛ ሡራህ እራሱ ስሙ "ሡረቱል አንፋል" سُورَة الْأَنفَال ነው። ይህም ምርኮ አንድ አምስተኛው ለአሏህ፣ ለመልእክተኛው፣ ለዝምድና ባለቤቶች፣ ለየቲሞች፣ ለምስኪኖች፣ ለመንገደኛ የተገባ ነው፦
8፥41 ከማንኛውም የምርኮ ገንዘብ የዘረፋችሁትም አንድ አምስተኛው ለአሏህ እና ለመልእክተኛው፣ የዝምድና ባለቤቶችም፣ ለየቲሞችም፣ ለምስኪኖችም፣ ለመንገደኛም የተገባ መኾኑን ዕውቁ። وَاعْلَمُوا أَنَّمَا غَنِمْتُم مِّن شَيْءٍ فَأَنَّ لِلَّهِ خُمُسَهُ وَلِلرَّسُولِ وَلِذِي الْقُرْبَىٰ وَالْيَتَامَىٰ وَالْمَسَاكِينِ وَابْنِ السَّبِيلِ

በቁርኣን ስለ አንፋል እዚህ ድረስ አጥለን እና አጠንፍፈን ከተረዳን ዘንዳ መጅ እና ወፍጮ ይዘን ስለ ምርኮ በባይብል የተነገሩት በቅጡ አድቅቀን እናያለን። ነቢዩ አብርሃም ነገሥታትን ገድሎ ሲመለስ ከነገሥታቱ የዘረፈውን ለሳሌም ንጉሥ ለመልከ ጼዴቅ ሰጥቶታል፦
ዕብራውያን 7፥4 የአባቶች አለቃ አብርሃም "ከዘረፋው" የሚሻለውን አስራት የሰጠው ይህ ሰው እንዴት ትልቅ እንደ ነበረ እስኪ ተመልከቱ።

"ከዘረፋው" የሚለው ይሰመርበት! አብርሃም በጦርነት ምርኮን ስለዘረፈ ሌባ ነውን? መዝረፉስ ሌብነት ነውን? ጉድ ፈላ፥ ይህ ከድጡ ወደ ማጡ ነው። የያዕቆብ ልጆች እኅታቸው ዲና ስለተደፈረች ደፋሪዎችን ገድለው በከተማይቱ ያሉትን በጎቻቸውን፣ ላሞቻቸውን፣ አህዮቻቸውን፣ በውጭም ያለው፣ ሀብታቸውን ሁሉ፣ ሕፃናቶቻቸውን፣ ሴቶቻቸውንም እና በቤት ያለውንም ሁሉ ዘረፉ፦
ዘፍጥረት 34፥27-29 የያዕቆብም ልጆች እኅታቸውን ዲናን ሰለ አረከሱአት ወደ ሞቱት ገብተው ከተማይቱን "ዘረፉ"፤ በጎቻቸውንም ላሞቻቸውንም አህዮቻቸውንም በውጭም በከተማም ያለውን ወሰዱ። ሀብታቸውን ሁሉ ሕፃናቶቻቸውንና ሴቶቻቸውንም ሁሉ ማረኩ፥ በቤት ያለውንም ሁሉ "ዘረፉ"።

"ዘረፉ" የሚለው ይሰመርበት! ይህንን ስታነቡ ሰኔ እና ሰኞ ይሆንባቸዋል። በዚህ ቢቆም ጥሩ ነበር፥ እስራኤላውያንም ከግብፅ ሲወጡ የግብፅ ንብረት በዝብዘው ነበር። ይህንን ያደረጉት ከተማይቱን በማቃጠል ነው፥ ይህንን ያዘዛቸው የእስራኤል አምላክ እንደሆነ ባይብሉ ይናገራል፦
ዘጸአት 3፥22 ነገር ግን እያንዳንዲቱ ሴት ከጎረቤትዋ በቤትዋም ካለችው ሴት የብር ዕቃ የወርቅ እቃ ልብስም ትለምናለች፤ በወንዶችና በሴቶች ልጆቻችሁ ላይ ታደርጉታላችሁ፤ ግብፃውያንንም "ትበዘብዛላች"።
ዘጸአት 12:36 እግዚአብሔርም ለሕዝቡ በግብፃውያን ፊት የፈለጉትን እንዲሰጡአቸው ሞገስን ሰጠ። እነርሱም ግብፃውያንን "በዘበዙ"።

"ትበዘብዛላች" የሚለው መጻኢ ግሥ እና "በዘበዙ" የሚለው አላፊ ግሥ ይሰመርበት! በትእዛዙ መሠረት በመንገድ ላይም ያደረጉት ይህንን ተግባር ነው ፦
ዘኍልቍ 31፥9-11 የእስራኤልም ልጆች የምድያምን ሴቶችና ልጆቻቸውን "ማረኩ"፤ እንስሶቻቸውንና መንጎቻቸውንም ዕቃቸውንም ሁሉ "በዘበዙ"። የተቀመጡባቸውን ከተሞቻቸውን ሁሉ ሰፈሮቻቸውንም ሁሉ በእሳት አቃጠሉ። "የሰውን እና የእንስሳን ምርኮና ብዝበዛ ሁሉ ወሰዱ"።
ዘኍልቍ 31፥53 ወደ ሰልፍ የወጡ ሰዎች ሁሉ "ከምርኮአቸው ለራሳቸው ወሰዱ"።
ኢያሱ 8፥27 ነገር ግን ያህዌህ ኢያሱን እንዳዘዘው ቃል የዚያችን ከተማ ከብት እና ምርኮ እስራኤል ለራሳቸው "ዘረፉ"።
ኢያሱ 11፥14 የእስራኤልም ልጆች የእነዚህን ከተሞች ምርኮ ሁሉ ከብቶቹንም ለራሳቸው "ዘረፉ"።

"የምርኮ ገንዘብ ለአሏህ ምን ያደርግለታል" የምትሉ ግን በጤናችሁ ነውን? የምርኮ ገንዘብ ከአምስት መቶ አንድ ለያህዌህ ነው፦
ዘኍልቍ 31፥28 ከእነዚያም ከተዋጉት ወደ ሰልፍም ከወጡት ሰልፈኞች ዘንድ፥ ከሰዎችም ከበሬዎችም ከአህዮችም ከመንጎችም ከአምስት መቶ አንድ ለያህዌ ግብር አውጣ።

ከአምስት መቶ አንድ ለያህዌህ ግብር ምን ያረግለታል? በሰፈሩት ቁና መሰፈር ይሉካል እንደዚህ ነው። ስለ ዘረፋ በባይብል ልቀጥል ብል ቦታ አይበቃኝም፥ አንባቢንም ማሰልቸት ነው። መቼም ሚሽነሪዎች የኢሥላም ትምህርት ጥንብ እኩሱን ቢወጣ እና ዶግ አመድ ቢሆንላቸው ደስታቸው እጥፍ ድርብ ነው፥ ይህ ጡዘቱ ጣራ የነካና ዙሪያ ገባ ምኞች ስለማይሳካ በቁጭ ይሙቱ! ከእነርሱ ቅንነት የተሞላው ትምህርት መጠበቅ ማለት ከጅብ አፍ ላይ ሥጋ እንደመጠበቅ ነው። እነርሱ የሚሰጡት ትችት እኛ ሙሥሊሞችን የሚያፍረከርክ ሳይሆን ከእለት ወደ እለት የሚያጀግን ነው፥ ለማንኛውም የተነሳውን ትችት አብጠርጥረን እና አንጠርጥረን መልስ ሰተናል። አሏህ ለእነርሱ ሂዳያህ ይስጣቸው! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።

✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም




ኒቂያ፣ ቆስጠንጢኒያ፣ ኤፌሶን እና ኬልቄዶን በጥንት ጊዜ ቱርክ ውስጥ የሚገኙ ከተሞች ናቸው። በ325 ድኅረ ልደት በንጉሥ ቆስጠንጢኖስ ሊቀ መንበርነት የኒቂያ ጉባኤ ላይ 318 ኤጲጵ ቆጶሳት ከመላው ዓለም ተሰብስበው የአርዮስን እና የአትናትዮስ ክርክሮችን ለመታደም መጡ።

፨አርዮስ፦ "ወልድ ፍጡር ነው፥ አንዱ አምላክ አብ እና ኢየሱስ  "የተለያየ ህላዌ" እንጂ ተመሳሳይ አይደለም" በማለት ኢየሱስ "ከአብ ጋር የተለያየ ህላዌ ነው" የሚል አቋም ነበረው።
፨አትናቴዎስ፦ "ወልድ ፍጡር አይደለም፥ አንዱ አምላክ አብ እና ኢየሱስ "ተመሳሳይ ህላዌ" እንጂ የተለያየ አይደለም" በማለት ኢየሱስ "ከአብ ጋር ተመሳሳይ ህላዌ ነው" የሚል አቋም ነበረው።

ጉባኤው የማታ ማታ "ከአምላክ የተገኘ አምላክ ነው" በማለት አጸደቀ፥ "አምላክ አምላክን አህሎ እና መስሎ፣ ከባሕርይ ባሕርይ ወስዶ፣ ከአካል አካል ወስዶ ተወለደ" በማለት "ሆ ቴዎስ ሆ ሁዎስ" Ο Θεός ο γιος ማለትም "እግዚአብሔር ወልድ"God the Son" የሚል የአቋም መግለጫ ተሰጠ። 

ይህ በምስሉ ላይ የምትመለከቱት መሥጂድ ጉባኤው የታደሙበት የነበረው አዳራሽ ነው፥ ከዚያ በኃላ እነርሱ እርስ በእርስ በነገረ ክርስቶስ እሳቤ ሲባሉ የኢሥላም ብርሃን ቦታ ላይ በማብራት አዳራሹ የዓለማቱ ጌታ አሏህ የሚመለክበት መሥጂድ ሆኗል። አልሐምዱ ሊላህ!

✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom


ግዝረተ ኢየሱስ

በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

21፥22 የዐርሹ ጌታ አሏህ ከሚሉት ሁሉ ጠራ። فَسُبْحَانَ اللَّهِ رَبِّ الْعَرْشِ عَمَّا يَصِفُونَ

ፈጣሪ ጾታ የለውም፥ ሴትም ወንድም አይደለም። ፈጣሪ የሴትም የወንድም ሩካቤ ሥጋ የሌለው ሲሆን ወንድ ልጅ ግን ሩካቤ ሥጋ"sex organ" አለው፥ ይህ ሩካቤ ሥጋ"sex organ" ሽንት ለመሽናት እና ከሴት ጋር ተራክቦ"intercourse" ለማድረግ ያገለግላል። ኢየሱስ ከሴት የተወለደ ወንድ ልጅ ነው፦
ሉቃስ 1፥31 እነሆም፥ ትፀንሻለሽ "ወንድ" ልጅም ትወልጃለሽ፥ ስሙንም ኢየሱስ ትዪዋለሽ።

"ወንድ" የሚለው ቃል የሥጋ መደብ እና አንቀጽ እንደሆነ ልብ አድርግ! እንደሚታወቀው ወንድ ሩካቤ ሥጋው ላይ ያለውን ሸለፈት በስምንተኛ ቀን ይገረዛል፦
ዘፍጥረት 17፥12 የስምንት ቀን ልጅ ይገረዝ፤ በቤት የተወለደ ወይም ከዘራችሁ ያይደለ በብርም ከእንግዳ ሰው የተገዛ፥ ወንድ ሁሉ በትውልዳችሁ ይገረዝ።

ኢየሱስም ስምንት ቀን ሲሞላው ተገርዟል፥ በማኅፀን ከመረገዙ ማለትም ከመፀነሱ በፊት ስም እንደወጣለት ስሙ ኢየሱስ ተብሎ ተጠራ፦
ሉቃስ 2፥21 ሊገርዙት ስምንት ቀን በሞላ ጊዜ፥ በማኅፀን ሳይጸነስ በመልአኩ እንደ ተባለ፥ ስሙ ኢየሱስ ተብሎ ተጠራ።
ሮሜ 15፥9 ክርስቶስ ስለ አምላክ እውነት የመገረዝ አገልጋይ ሆነ እላለሁ። λέγω γὰρ Χριστὸν διάκονον γεγενῆσθαι περιτομῆς ὑπὲρ ἀληθείας Θεοῦ,

አምላክ በሥጋ ሊገረዝ ይቅርና ክርስቶስ እራሱ ስለ አምላክ እውነት የተገረዘ አገልጋይ እንደሆነ በመግለጽ በአምላክ እና በክርስቶስ መካከል የምንነት ልዩነት እንዳለ ቁልጭ እና ፍንትው አርጎ ያሳያል። ይህ የተገረዘውን ሕፃን በጌታ ፊት ያቆሙት ዘንድ ዮሴፍ እና ማርያም ወደ ኢየሩሳሌም ወሰዱት፦
ሉቃስ 2፥24 እንደ ሙሴም ሕግ የመንጻታቸው ወራት በተፈጸመ ጊዜ፥ በጌታ ሕግ፦ የእናቱን ማኅፀን የሚከፍት ወንድ ሁሉ ለጌታ የተቀደሰ ይባላል ተብሎ እንደ ተጻፈ "በጌታ ፊት ሊያቆሙት፥ በጌታም ሕግ፦ ሁለት ዋሊያ ወይም ሁለት የርግብ ጫጩቶች እንደ ተባለ፥ መሥዋዕት ሊያቀርቡ ወደ ኢየሩሳሌም ወሰዱት"።

የሁሉ ጌታ እና ሕፃኑ ሁለት የተለያዩ ኑባሬ እንደሆኑ አያችሁን? ፈጣሪ ፆታ ኖሮት፣ ወንድ ሆኖ፣ ተገርዞ፣ ሕፃን ሆኖ በጌታ ፊት ሊያቆሙት ሲወስዱት አስቡት! የተገረዘው ወንድን ልጅ ወደ ጌታ አምላክ ከወሰዱት ዘንዳ የተገረዘው ወንድ ልጅ እንጂ ጌታ አምላክ አይደለም።

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ጥር 6 ቀን በዓመት አንዴ "ግዝረተ ኢየሱስ" ተብሎ የተገዘረበትን ዓመታዊ ክብረ በዓል ትዘክራለች፥ "ግዝረት" ማለት የግዕዝ ቃል ሲሆን "ግርዘት"circumcision" ማለት ነው፥ ቄርሎስ ዘእስክንድርያ ስለ ኢየሱስ መገረዝ እንዲህ ይለናል፦
ሃይማኖተ አበው ምዕራፍ 70 ቁጥር 24
"ሰውም እንደ መሆኑ ለሥጋ እንደሚገባ ተገዘረ"።

ኢየሱስ መገረዙን ከተረዳን ዘንዳ ይህ ተቆርጦ የተገዘረው ሸለፈት ሥጋ አምላክ እንደሆነ እራሱ ቄርሎስ ዘእስክንድርያ እና አትናቴዎስ ዘእስክንድርያ ይናገራሉ፦
ሃይማኖተ አበው ምዕራፍ 78 ቁጥር 31
"ዳግመኛ የጌታችን የክርስቶስ ሥጋ አምላክ እንደሆነ እንናገራለን"።
ሃይማኖተ አበው ምዕራፍ 29 ቁጥር 19
"ከእመቤታችን ከቅድስት ከድንግል ማርያም የነሳው ይህ ሥጋም እውነተኛ የባሕርይ አምላክ ነው"።

ተቆርጦ የተገረዘው ሸለፈታዊ ሥጋ እውነተኛ የባሕርይ አምላክ ተሸልቶ አፈር ሆኖ ታመልኩታላችሁን? "ያ ፍጥረትን የፈጠረውን አሏህን ማርያም የወለደችው ወንድ ልጅ ነው" ብለው ያሉ በእርግጥ ካዱ፡፡ የዐርሹ ጌታ አላም ከሚሉት ሁሉ ጠራ፦
5፥17 እነዚያ "አሏህ እርሱ የመርየም ልጅ አል መሢሕ ነው" ያሉ በእርግጥ ካዱ፡፡ لَّقَدْ كَفَرَ الَّذِينَ قَالُوا إِنَّ اللَّهَ هُوَ الْمَسِيحُ ابْنُ مَرْيَمَ
21፥22 *የዐርሹ ጌታ አላህም ከሚሉት ሁሉ ጠራ*። فَسُبْحَانَ اللَّهِ رَبِّ الْعَرْشِ عَمَّا يَصِفُونَ

"ከሚሉት" ለሚለው ቃል የገባው "የሲፉን" يَصِفُون ሲሆን "ባሕርይ ካደረጉለት"They attribute” ማለት ነው። አምላካችን አሏህ አባጣ እና ጎርባጣ ከሆነ የሺርክ ሕይወት አውጥቶ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይወፍቀን! አሚን።

✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
መምህር ያረጋል አበጋዝ በመጀመሪያ መቶ ክፍለ ዘመን ማለትም ከሐዋርያት ዘመን ጀምሮ ብዙ ወንጌላት ነበሩ፥ ከእነዚያ ውስጥ በአጥቢያ ጉባኤ(local chuch) የተመጠሩት አራት ብቻ ሲሆኑ ሌሎቹ ግን ስለ ክርስቶስ ህማማት(ስቅለት፣ ግድለት እና ሞት) አይናገሩም ነበር። ጉባኤው እምነቱን በሚገልጥ መልኩ ተገሏል ተሰቅሏል የሚሉትን አጽድቋል።

በስቅለት ዙሪያ የነበረውን ውዝግብ "አልገደሉትም አልቀቀሉትም" የሚለው ስንክሳሩን በአንድ ንዑስ መግቢያ በመሰነድ፣ በአምስት ዐበይት አርዕስት በመሰደር እና በአንድ ጉልኅ ማጠቃለያ በመሰነግ ረብጣ እይታ አቅርቤአለውና እናንተም ውድ አንባቢያን ሆይ! ይህንን መጽሐፌን ለማሳለጥ እና ለማረቅ ልባችሁን ክፍት እንደምታረጉ ተስፋ አለኝ።

መጽሐፉን የምትፈልጉ አገር ውስጥ ያላችሁ ሆነ ከአገር ውጪ ያላችሁ በ +251928444408 ዐብዱ መርካቶ ብላችሁ በቀጥታ አሊያም በዋትሳፕ ታገኙታላችሁ፥ እንዲሁ በቴሌ ግራም ይህንን ዩዘር ኔም በመጠቀም http://t.me/merkatozon ማግኘት ትችላላችሁ።

እንዲሁ ቤተል ተቅዋ መሥጂድ ሥር ስለሚገኝ ኩብራ ብላችሁ በመደወል ማግኘት ይችላሉ፦ +251911663699
አየር ጤና አንሷር መሥጂድ ሥር፦ 0963796354

ለብዙዎች ሠበቡል ሂዳያህ ለመሆን ሁሉም ቦታ ሼር አርጉት!
ወጀዛኩሙላህ ኸይራ!

Показано 20 последних публикаций.