💜 ዝማሬ ዳዊት 💜


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: не указана


#እነሆ_ድንቅ መዝሙሮች፣ ወረቦች፣ አስተማሪ ፅሁፎች እና ሌሎችንም የሚያገኙበት ቻናል ጌታችን በዓለት መሠረት የመሠረታት፤ አባቶቻችን ሐዋርያት ያስተማሩላት፣ነቅዕ የሌለባት የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ትምህርት መሠረት ያደረጉ ትምህርቶች የሚያገኙበት channel.
ተቀላቀሉን!
👇 👇
https://t.me/joinchat/vRKyRbcLVO1iYjVk
👆👆
Creater @Te_best

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
не указана
Статистика
Фильтр публикаций


1⃣7⃣ደቂቃ ቦኃላ ይጠፋል


የ 200 ብር ካርድ የሚያስሸልም ጥያቄ!

በኢትዮጵያ በጣም አስቸጋሪ የነበረዉ  ረሀብ መች አመተምህረት ነበረ


⁉️ጥያቄና መልስ
🌺🌺🌺🌺

'https://t.me/addlist/33Faa1YThXUwMjU0' rel='nofollow'>❤️፩. ኦርቶዶክስ ማለት ምን ማለት ነው?❤️

፪. ጌታ ለምን ድንግል ከሆነች ማርያም 'https://t.me/addlist/33Faa1YThXUwMjU0' rel='nofollow'>ተወለደ? (ለምን በድንግልና ተወለደ?)


Репост из: 🎤🌼ድምፀ ተዋህዶ🌼🎤
እንኳን ለጻድቁ አባታችን ለአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ አመታዊ ክብረ በዓል በሰላም አደርሳቹ❗️

ጥቅምት 5-ኑሮአቸው እንደሰው ያይደለ በምድረ በዳ እንደመላእክት የኖሩትና በዝቋላ ተራራ ባለው ባሕር ውስጥ 100 ዓመት ተዘቅዝቀው ለኢትዮጵያ ሰዎች ምሕረትን የለመኑት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ታላቅ ቃልኪዳን የተቀበሉበት ዕለት ነው፡፡ 

አባታችን አራት ሺህ እልፍ እየሰገዱ፣ 300 ጊዜ የቀኝ 300 ጊዜ ደግሞ የግራ ፊታቸውን በድንጋይ እየመቱ፣ መዝሙረ ዳዊትን እየደገሙ፣ 15ቱን መኅልየ ነቢያት፣ መኅልየ ሰለምንንና ውዳሴ ማርያም እየጸለዩ ለኃጥአን ምሕረትን ሲለምኑ ዕንባቸው እንደ ውኃ ይፈስ ነበር፡፡ ጌታችንም ‹‹በተወለድሁባት፣ በተጠመቅሁባትና ከሞት በተነሣሁባት ዕለት እልፍ እልፍ ነፍሳትን እምርልሃለሁ›› የሚል ቃል ኪዳን ሰጣቸዉ

አምላካችን በቃል ኪዳናቸው ይማረን


✝️#ድምፀ_ተዋህዶ ✝️


Репост из: 🎤🌼ድምፀ ተዋህዶ🌼🎤
“አሁን ባለን የአስተዳደር ክፍተቶችና በውስጣችን ያሉ ግልጽነት የጎደላቸው አሠራሮች ለአገልግሎታችን እንቅፋት እየሆኑብን ነው”ሲሉ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ገለጹ፡፡

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት 43ኛው ዓለም አቀፍ መደበኛ ጉባኤ መክፈቻ ላይ ለተገኙ ተሳታፊዎች መልእክት አስተላልፈዋል።

ቅዱስነታቸው በመልእክታቸው አሁን ባለን የአስተዳደር ክፍተቶችና በውስጣችን ያሉ ግልጽነት የጎደላቸው አሠራሮች ለአገልግሎታችን እንቅፋት እየሆኑብን ነው። በዚህ ጉባኤ በቤተ ክርስቲያናችን የሚታየውን  ችግር ለመፍታት በጥናት ላይ የተመሠረተ መፍትሔ ማምጣት ይገባል ሲሉ አፅዕኖት ሰጥተዋል፡፡

ቅዱስነታቸው ጨምረው እንደገለጹት ቅዱስ ሲኖዶስ ተግባራዊ እንዲሆን የወሰነውን የቤተ ክርስቲያን የ10 ዓመት መሪ ዕቅድ ውጤታማ ለማድረግ ሁላችንም በትብብር መሥራት ይገባናል ብለዋል።

በዛሬው ዕለት የተጀመረው 43ኛው አጠቃላይ መንፈሳዊ ጉባኤ ከሀገር ውስጥ እና ውጪ ከሚገኙ አህጉረ ስብከቶች፣ ከአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት አድባራት እና ገዳማት እንዲሁም ከተለያዩ መንፈሳዊ ማኅበራት የተወከሉ ተሳታፊዎች በተገኙበት እየተከናወነ ይገኛል።

#ድምፀ_ተዋህዶ


Репост из: 🎤🌼ድምፀ ተዋህዶ🌼🎤
"በሰማይ የምትኖር ሆይ፥ ዓይኖቼን ወደ አንተ አነሣሁ፤ እነሆ፥ የባሪያዎች ዓይኖች ወደ ጌታቸው እጅ እንደ ሆኑ፥ የባሪያይቱም ዓይን ወደ እመቤትዋ እጅ እንደ ሆነ፥ እንዲሁ እስኪምረን ድረስ፡ ዓይናችን ወደ አምላካችን ወደ እግዚአብሔር ነው'' መዝ. 122:1-3

#ድምፀ_ተዋህዶ

▫️https://t.me/dmtse_tewaedo




Репост из: 🎤🌼ድምፀ ተዋህዶ🌼🎤
#እንኳን #ለፆመ_ጽጌ በሳላም አደረሳቹህ

✤ወርኃ ጽጌ 40 ቀናት ነው፤ መስከረም 26 ተጀምሮ ኅዳር 5 ያልቃል፤ ጾመ ጽጌ የፈቃድ ጾም ነው (ከሰዓትም ቅዳሴ የሚቀደሰስባቸው አካባቢዎች አሉ (ጎንደር )፡፡
በግዕዝ ጸገየ ማለት   አበበ ፤ አፈራ ፣ በውበት ተንቆጠቆጠ ማለት ነው፡፡ 
በማኀሌቱም ወቅትን እመቤታቸንን 3 ዓመት ከ6 ወር እስከ ግብፅ ከዚያም የአሥራት ሀገሯ  በሆነችው በኢትዮጵያ የተሰደደችበትን ወቅት በማሰብ  በጽጌና በአበባ እመቤታቸንን እና ጌታቸንን በመመሰል ሲያመሰግኗት ፣  ከልጇ ጋር ያየችውን መከራ  እያሰቡ  እና  ምልጃዋን ሲለምኑ ያድራሉ ፡፡

✤እምግብጽ ጸዋዕክዎ ለወልድየ ለክብረ ቅዱሳን፤ ለቅዱሳን ክብር ልጄን ከግብጽ ጠራሁት››
በማለት ነቢዩ ሆሴዕ በምዕራፍ ፲፩ ቍጥር ፩ እና ፪ ላይ አስቀድሞ እንደ ተናገረው ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በልጅነቱ ወደ ምድረ #ግብጽ (ምስር) የተሰደደው የነቢያት ትንቢት ይፈጽም ዘንድ ነው፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ሕፃናትን በመፍጀት ከሚታወቀው ከአረመኔው ንጉሥ ከሄሮድስ ለማምለጥ ነው፡፡ አምላካችን ክርስቶስ ያለጊዜው (ዕለተ ዓርብ) #ደሙ #አይፈስምና፡፡ ስለዚህም ‹‹ሕፃኑንና እናቱን ይዘህ ወደ ምድረ ግብጽ ሽሽ፤ ሄሮድስ ሕፃኑን ለመግደል ይፈልጋልና›› ብሎ መልአኩ ቅዱስ #ገብርኤል ለዮሴፍ በነገረው ቃል መሠረት ሕፃኑንና እናቱን ይዞ በሌሊት ወደ ግብጽ ምድር ተሰደደ፡፡ ይህንን ስደት አስመልክቶ #ሰቆቃወ ድንግል የሚባለውን ቃለ እግዚአብሔር ካህናቱ በሚያሳዝን ዜማ ያደርሳሉ፤ ያቀርባሉ፡፡

#በመቶ ሺሕ የሚቆጠሩ ሕፃናትን ሄሮድስ አስፈጅቷል፡፡ ‹‹ድምፅ በራማ ተሰማ፤ ለቅሶና ብዙ ዋይታ፡፡ ራሔል ስለ ልጆቿ አለቀሰች፡፡ መጽናናትም አልወደደችም፤ የሉምና›› የሚለው ትንቢትም ተፈጸሟል፡፡

#ከሦስት ዓመት ከመንፈቅ የግብጽ ስደት በኋላ ሊቃውንቱ፡- ‹‹ተመየጢ ማርያም ሀገረኪ ናዝሬተ፣ በላዕሌኪ አልቦ ዘያበጽሕ ሁከተ፣ ወኢትጎንድዪ በግብጽ ከመ ዘአልብኪ ቤተ፣ ዘየኀሥሦ ለወልድኪ ይእዜሰ ሞተ፣ በከመ ነገሮ መልአክ ለዮሴፍ ብሥራተ›› እያሉ ከስደት መመለሷን ያበሥራሉ፡፡ ትርጉሙም፡- ‹‹ማርያም ሆይ! ወደ ሀገርሽ ወደ ናዝሬት ተመለሺ፡፡ በአንቺ ላይ ሁከት የሚያመጣ ማንም የለም፡፡ ቤት እንደሌለሽ ሁሉ በግብጽ አትቆይ፡፡ ለዮሴፍ በሕልሙ መልአክ እንደ ነገረው የሕፃኑን ነፍስ የፈለገው (ጠላት ሄሮድስ) ሞቷልና›› ማለት ነው፡፡ የኢትዮጵያ #ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምእመናን በዐርባው ቀን (በዘመነ ጽጌ) ወቅት የማርያምን የሽሽትና የመመለስ (የሚጠት) ታሪክ እያነሡ ውዳሴ የሚያቀርቡትና ማኅሌት የሚቆሙት በዚሁ ምክንያት ነው፡፡ በዚህ ወቅት ለእመቤታችን ክብር ሲባል የፈቃድ ጾም የሚጾሙ ምዕመናንና ምዕመናትም ብዙዎች ናቸው በመሃል ኢትዮጵያ  በፈቃድ ጾምነት ሲጾም ; በሰሜኑ አካባቢ ተጹሞ ከሰዓት ይቀደሳል ሌሎች ጋር ግን ጠዋት ያበቃል፡፡

የእመቤታችን ምልጃ ና ጸሎት አይለየን

#ማኅሌተ_ጽጌ
✤የማኅሌተ ጽጌ  የሰቈቃወ ድንግል ደራሲ አባ ጽጌ ድንግል ነው ፡፡
  ገዳሙም ትልቅና ሰፊ የኾነ የፍልፍል ዋሻ ሲኾን ወሎ ወግዲ ወለቃ ወንዝ አጠገብ በረሃ ላይ (ከጋሥጫ ገዳም የ4 ሰዓት የእግር መንገድ) ይገኛል፡፡
✤✤ በየዓመቱ ሳይመረገዱ ያመይታለፉ የማይቀሩ፤ ዚቃቸው የማይለወጥ፤
      እጅጉን በምንወደው የማኅሌተ ጽጌ ቁመት ላይ በየዓመቱ ሳይመረገዱ የማይታለፉ የማይቀሩ፤ ዚቃቸው የማይለወጥ
( ከማኅሌተ ጽጌ፤ ጽጌ አስተርአየ(የመጀመሪያው ሳምንት)፣ በከመ ይቤ መጽሐፍ፣ ትመስል እምኪ ማርያም፣ ዘኒ ስብሐተ ወዘኒ ማኅሌተ፣ ኢየሐፍር ቀዊመ ቅድመ ሥዕልኪ እና ኅብር ሐመልሚል (የመጨረሻው ሳምንት)ናቸው፡፡
✤ ከሰቈቃወ ድንግል፤ በስመ እግዚአብሔር ሥሉስ፣ ብክዩ ኅዙናን፣ እስከ ማዕዜኑ እግዝእትየ እና አብርሂ አብርሂ ናቸው፡፡
✤ከማኅሌተ ጽጌ ውስጥ እንዘ ተሐቅፊዮ ለሕፃንኪ እና ክበበ ጌራ ወርቅ በየሳምንቱ (በኹሉም ዓመታት) ይመረገዳሉ፤ ዚቁ ግን በዓሉን በተመለከተ ይኾናል፡፡
✤ ከላይ ካየናቸው ውጪ የሚገኙት #የማኅሌተ ጽጌና የሰቈቃወ ድንግል ክፍሎች ግን #በየሰባት ዓመት አንዴ ነው የሚመረገዱት፡፡
( የማኅሌቱ ሥርዐት የላይ ቤት (የጎንደር መካነ ነገሥት ግምጃ ቤት ማርያም አብነት) እና የታች ቤት (የጎንደር ደብረ ኀይል በዓታ ለማርያምን አብነት) የሚያደርግ ሲኾን፤

የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለም ወደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ የማኅሌት ቁመትም የላይ ቤትን አብነት የተከተለ ሲኾን የዚቁ ወረብ ግን የደብሩን የራሱን (የሸዋን) የተከተለ ነው፤
( የላይ ቤት ቁመት የሚቆሙ አድባራት #ዘግምጃ ቤት የሚለውን እንዲከተሉ፤ የታች ቤትን #ቁመት የሚቆሙ አድባራት ዘበዓታ የሚለውን እንዲከተሉ፡፡ የዚቁ ወረብን ግን የቀጨኔ ደብረ ሰላም
የቤቱን ቀለም አስቀድመን ቀጥሎ ደግሞ ዓዲ (ወይም) በማለት የጎንደርን ስላስቀመጥነው እንደ ደብራችሁ ይትበሃል መርጣችሁ  ተጠቀሙ፡፡

/በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት የተዘጋጀ ::/

    #ድምፀ_ተዋህዶ

https://t.me/dmtse_tewaedo


|°°ለጀማሪ የግእዝ ቋንቋ ወዳጆች ሁሉ
  🙌 ሰላም ጤና ይስጥልን ክቡራት እና ክቡራን የልሳነ ግእዝ ስልጠና በ @lesangeez128 እየሰጠን እንደሆነ ይታወቃል ሆኖም የጀማሪዎች ስልጠና  በቅርቡ በonline ስለሚጀመር በዚህ #ዙር ላይ 20 ተማሪዎች ብቻ ስለሚካተቱ ከወዲሁዠለጀማሪችሁን እንድታዘጋጁና በፍጥነት እንድትመዘገቡ መልእክታችንን እናስተላልፋለን።
#ለሁለት ወር የመማሪያ ክፍያ #250ብር ብቻ ለበለጠ መረጃ በ @asrategabriel ያነጋግሩን አልያም በ +251970908094 ይደውሉልን።

   🤲ሰብሕዎ የልሳነ ግእዝ ማሰልጠኛ ተቋም🧑‍🎓


Репост из: 🎤🌼ድምፀ ተዋህዶ🌼🎤
መስቀል ሃይላችን ነው ፣መስቀል መፅናኛችን ነው ፣ መስቀል የነፍሳችን መድሃኒት ነው፣ መስቀል ቤዛችን ነው ።
አይሁድ ይክዱታል እኛ ግን እናምነዋለን ያመነውም እኛ በመስቀሉ እንድናለን ድነንማል።
የተወደዳቹ የቻናላችን ቤተሰቦች
እንኳን ለታላቁ የመስቀል ደመራ በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን!

#ድምፀ_ተዋህዶ

https://t.me/dmtse_tewaedo


Репост из: 🎤🌼ድምፀ ተዋህዶ🌼🎤
መስከረም  ፲፮


በዚች ቀን በኢየሩሳሌም አገር ንግሥት ዕሌኒ የገለጠቻቸው የከበሩ ቦታዎች ሁሉ የተሠሩበትና የከበሩበት ሆነ ።

ቆስጠንጢኖስ ከነገሰ በኋላ እናቱ ቅድስት ዕሌኒ ልጄ ሆይ እኔ ወደ ቅድስት አገር ኢየሩሳሌም በመሔድ የክርስቶስን ዕፀ መስቀል ፈልጌ አወጣ ዘንድ ለእግዚአብሔር ስዕለትን ተስያለሁ አለችው ።

ቆስጠንጢኖስም ሰምቶ ደስ አለው ብዙ ሠራዊትና ገንዘብ ሰጥቶ ላካት። ኢየሩሳሌምም በደረሰች ጊዜ ከከበሩ ቦታዎች ተባረከች ። ከዚህም በኋላ የከበረና አዳኝ  የሆነ የክርስቶስን ዕፀ መስቀል ከብዙ ፍለጋ በኋላ አገኘች እግዚአብሔርንም አመሰገነች።

ከዚህም በኋላ በጎልጎታ፣ በቤተልሔም፣ በጽርሐ ጽዮን፣ በጌቴሴማኔ፣ በደብረ ዘይት እና በከበሩ ቦታዎች ሁሉ በዕንቁ በወርቅና በብር የቤተ መቅደስ መሠዊያዎች እንዲሠሩ አዘዘች።

ጻድቅ ንጉሥ ቆስጠንጢኖስም በነገሠ በ፴ ዓመቱ የከበሩ ቦታዎች ሕንፃቸው በተፈጸመ ጊዜ ለቁስጥንጥንያ፣ ለአንጾኪያ፣ለእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት ኤጲስቆጶሶቻቸውን በመያዝ ሁሉም በኢየሩሳሌም የታነፁትን አብያተ ክርስቲያናት እንዲያከብሩ አዘዘ። ንጉሡም እንዳዘዘ ሁሉም ተሰበሰቡ የቁርባን ቅዳሴንም ቀድሰው ለምእመናን ሥጋውንና ደሙን አቀበሉ በዚችም ቀን ከቶ እንደርሱ ሆኖ የማያውቅ ታላቅ ደስታ ሆነ።

የቅዱሳን በረከታቸው ይደርብን! አሜን!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር

#ድምፀ_ተዋህዶ
https://t.me/dmtse_tewaedo


Репост из: 🎤🌼ድምፀ ተዋህዶ🌼🎤
# ልዩ የመሰቀል ደመራ ፕሮግራም !!
     ✝️✝️✝️
#የሶዶ_ወረዳ_ቤተክህነት_ልዩ_የደመራ_ዝግጅት
በምሥራቅ ጉራጌ እና ማረቆ ልዩ ወረዳ ሀገረ ስብከት የሶዶ ወረዳ ቤተክህነት አስተባባሪነት በተዘጋጀው የደመራ በዓል የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስና የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ እንዲሁም የሀገረ ስብከቱ የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት ልዩ ፕሮግራም በቡኢ ከተማ በታላቅ ድምቀት ይከበራል።
✝️✝️✝️
እርስዎም የበዓሉ ተሳታፊ እንዲሆኑ እናሳስባለን።
እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ!
✝️✝️✝️
የምስራቅ ጉራጌና ማረቆ ልዩ ወረዳ ሀገረ ሰብከት !
መስከረም 11/01/2017 ዓ.ም
             ቡኢ
          ኢትዮጵያ
         ✝️✝️✝️

#ድምፀ_ተዋህዶ

https://t.me/dmtse_tewaedo


Репост из: 🎤🌼ድምፀ ተዋህዶ🌼🎤
👉 ያለፈው ዘመን ይበቃናል 👉
    ፩ ጴጥ ም ፬ ቁ ፫
                   4     3

✝ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ✝

🙏 እንኳን ለሊቀ መላዕክት ለቅዱስ ሩፋኤል በዓለ ሢመት አው ለካህኑ መልከጼዴቅ በዓል አደረሳችሁ አደረስን 🙏

👉 ጳጉሜን ፫ (3) በዓለ ሥሉስ ቅዱስ በዓሉ ለቅዱስ ሩፋኤል ሊቀ መላዕክት ወመልከጼድቅ ወሰራጵዮን ወዘርያዕቆብ ንጉሥ ኢትዮጵያ 👉

👉 ዘነግህ ምስባክ 👉

መሐለ እግዚአብሔር ወኢይኔስሕ
አንተ ካህኑ ለዓለም በከመ ሢመቱ ለመልከጼድቅ
እግዚአብሔር በየማንከ

✥ ትርጉም ✥

እንደ መልከጼዴቅ ሥርዓት አንተ ዘላለም ካህን ነህ ብሎ
እግዚአብሔር ማለ አይጸጸትም
እግዚአብሔር በቀኝህ
   
   መዝ ፻፱-፬
        109  4

✤ ወንጌል ✤

ሉቃ ም ፲፯ ቁ ፳-፴፩
           17   20  31

✝ የቅዳሴ ምንባባት ✝

ዕብ ም ፯ ቁ ፩-፭
ይሁዳ ም ፩ ቁ ፲፩-፲፯
ግብ.ሐዋ ም ፭ ቁ ፲፯-፳፮

❖ ምስባክ ❖

እግዚአብሔርሰ ገሃደ ይመጽእ
ወአምላክነሂ ኢያረምም
እሳት ይነደድ ቅድሜሁ

🙏 ትርጉም 🙏

እግዚአብሔር ግልጥ ሆኖ ይመጣል
አምላካችን ይመጣል ዝምም አይልም
እሳት በፊቱ ይነዳል
 
    መዝ ፵፱-፪
          49   2

❖ ወንጌል ❖

ማቴ ም ፳፭ ቁ ፴፩-ፍ.ም
            25    31   ፍፃሜው

❖ ቅዳሴ ❖

ያዕቆብ ዘሥሩግ(ተንሥኡ)

" የብርሃናት ፈጣሪ ሆይ ጨለማን የደፋው ጣዖትንም የሻረው በሞቱ ሞት ያጠፋው "
     ቅዳሴ ያዕቆብ ዘሥሩግ
           ም ፩ ቁ ፹፫
                1     83

✝ በዓሉ በዓለ ምህረት በዓለ ድኀነት ያድርግልን ቸሩ መድኃኔዓለም በቸርነቱ ይማረን እመ አምላክ እግዝእትነ ማርያም በምልጇዋ ትጠብቅን ከሊቀ መላዕክት ቅዱስ ሩፋኤል በረድኤቱ ይጠብቅን ካህኑ መልከጼዴቅ በረከቱ ይደርብን ድርሳነ ሩፋኤል ገድለ ቅዱሳን ዕጣነ አሮን መስዋዕት መልከጼዴቅ የተቀበለች የኛም ፆም ፀሎት ጥምቀት ምሕላ በቸርነቱ በብሩህ ገጽ ይቀበልልን ለበዓለ ዓውደ ዓመት በሰላም ያድርሰን ✝

                  ✧ ምስባክ ✧

#ድምፀ_ተዋህዶ

           YouTube chnnl
👇🏽🔻 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 𝒏𝒐𝒘 🔻👇🏽
        
የይቱብ ቻናላችን
             🔔
  🔺 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 𝒏𝒐𝒘🔺‌‌


❤️በናታኒም ቲዩብ❤️
         👇🏽👇🏽
https://youtu.be/MsXeCVCPxX
4
https://youtu.be/MsXeCVCPxX4
htt
ps://youtu.be/MsXeCVCPxX4




Репост из: 🎤🌼ድምፀ ተዋህዶ🌼🎤
Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram


Репост из: 🎤🌼ድምፀ ተዋህዶ🌼🎤
🔴አዲስ አበባ
ይህንን ቤተክርስቲያን ለኮሪደር ልማት በሚል ምክንያት እንደ ሱቅ መንገድ ላይ ቤተመቅደሱን ብቻ ባዶውን ሊያስቀሩት ነው።
በማንኛውም ማሕበራዊ ሚዲያ ድምፅ ሆነን ከመፍረስ እናድነው።
➟ከኪነ-ጥበብ


Репост из: 🎤🌼ድምፀ ተዋህዶ🌼🎤
† "በጽዮን መለከትን ንፉ:: ጾምንም ቀድሱ:: ጉባዔውንም አውጁ:: ሕዝቡንም አከማቹ:: ማሕበሩንም ቀድሱ:: ሽማግሌዎችንም ሰብስቡ:: ሕጻናቱንና ጡት የሚጠቡትን አከማቹ:: ሙሽራው ከእልፍኙ: ሙሽራይቱም ከጫጉላዋ ይውጡ::"

         †(ኢዩ. 2:15)

† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †

#አቤቱ ህዝብህን አድን ርስትህንም ባርክ ጌታ ሆይ ማራቸው
ከፍ  ከፍ አድርጋቸው/2/

#ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!

#ድምፀ_ተዋህዶ




Репост из: 🎤🌼ድምፀ ተዋህዶ🌼🎤
#ቅዱስ_ቂርቆስና_እናቱ_ቅድስት_ኢየሉጣ (#ሐምሌ_19)

ሐምሌ ዐሥራ ዘጠኝ በዚህች ቀን ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስና እናቱ ኢየሉጣ በሰማዕትነት መከራ ተቀበሉ። ይህም ሕፃን ዕድሜው ሦስት ዓመት ሲሆነው ከሮሜ አገር ወደሌላ ሀገር እናቱ ይዛው ሸሸች በዚያም የሸሸችውን መኰንን አገኘችው። 

ሰዎችም ነገር ሠሩባት ወደርሱ አስቀረባትና ስለ አምልኮ ጠየቃት እርሷም መኰንን ሆይ ዕድሜው ሦስት ዓመት የሆነው ሕፃን አለ አማልክቶችህን ማምለክ መልካም እንደሆነ ወይም እንዳልሆነ ያስረዳን ዘንድ እርሱን ጠይቅ አለችው። 

ሕፃኑም ወደአለበት ጭፍራውን ልኮ ወደርሱ አስመጣው ሕፃኑንም ፊቱ ብሩህና ደስተኛ እንደሆነ አየውና አንተ ደስተኛ ሕፃን ሆይ እንዴት ነህ አለው። ሕፃኑም መልሶ አዎ ለእኔ ደስታ ተጠብቆልኛል ላንተ ግን ኀዘንና ልቅሶ ጥርስ ማፋጨትም ነው መጽሐፍ ለዝንጉዎች ተድላ ደስታ የላቸውም ብሏልና አለው እግዚአብሔር ኃይልና ንግግርን ሰጥቶታልና ብዙ ተናገረ በዚያም ያሉትን እስከ አስደነገጣቸው ድረስ ንጉሡን መኳንንቱንና ጣዖታቱን ረገማቸው ከብርታቱም የተነሣ አደነቁ። 

መኰንኑም በአፈረ ጊዜ በየአይነቱ በሆነ ሥቃይ ታላላቆች የማይችሉትን ታላቅና አስጨናቂ የሆነ ሥቃይን አሠቃየው እናቱንም ከርሱ ጋር እንደ እርሱ አሠቃያት እግዚአብሔርም ያለምንም ጉዳት ያነሣቸው ነበር። ብዙዎች አሕዛብም ይህን አይተው አደነቁ ክብር ይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም አምነው በሰማዕትነት ሞቱ የሰማዕትነትንም አክሊል ተቀበሉ። 

በሕፃኑ ላይም የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ አደረበት። ታላላቅ ድንቆችና ተአምራቶችንም አደረገ ብዙዎች በሽተኞችንም አዳናቸው።

ከዚህም በኋላ መኰንኑ በታላቅ የናስ ጋን ውስጥ ውኃ ጨምረው በእሳት ያፈሉት ዘንድ አዘዘ የፍላቱም ድምጽ እንደ ክረምት ነጐድጓድ ሆነ ያን ጊዜም ፍርሀትና የሃይማኖት ጉድለት በእናቱ ላይ ደረሰባት ሕፃኑም ስለ እናቱ ወደ እግዚአብሔር ጸለየ። 

ያን ጊዜ ጌታችን ልቧን ወደ ሰማይ አሳርጎ ለቅዱሳን ሰማዕታት የተዘጋጁ የብርሃን ማደሪያዎችን አየች ከዚህም በኋላ ጸናች እግዚአብሔርንም አመሰገነችው ልጅዋንም ልጄ ሆይ ከእንግዲህ አንተ አባቴ ነህ እኔም ልጅህ ነኝ አለችው። 

ያቺ ከኔ የተወለድክባትም ቀን የተባረከች ናት አለች ወደዚያ ወደ ጋኑ ውስጥ በገቡ ጊዜም የውኃው ፍልሐት እንደ ንጋት ጊዜ ውርጭ ቀዘቀዘ ከእግዚአብሔር የታዘዘ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል ከሰማይ ወርዶ የእሳቱን ኃይል አቀዝቅዞታልና። 

ከዚህም በኋላ መኰንኑ ሥጋቸው ተቆራርጦ እስከሚወድቅ ድረስ በመቃጥን ውስጥ አድርገው እንዲጐትቷቸው አዘዘ ከእግዚአብሔርም የታዘዘ መልአክ አዳናቸው መኰንኑም በታላቅ ሥቃይ ያሠቃያቸው ዘንድ አስቦ እስኪመክር ድረስ በወህኒ ቤት ዘጋባቸው። 

ያን ጊዜም ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ሕፃኑ ቂርቆስ ወርዶ አጽናናው አረጋጋውም። ስሙን ለሚጠራና መታሰቢያውን ለሚያደርግ ቃል ኪዳን ሰጠው።

ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ሰማዕታት በጸሎታቸው ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

(#ስንክሳር_ዘወርኀ_ሐምሌ ➛ ስንክሳር ዘተዋሕዶ ፌስቡክ ገጽ የተወሰደ)

#ድምፀ_ተዋህዶ


Репост из: 🎤🌼ድምፀ ተዋህዶ🌼🎤
🪙Tonee mining app በዚህ 3 ቀን ውስጥ 10ሰው Invite ካደረጋቹ 1 ቶን እንደሚሰጥ ገልጿል መቼም 10 ሰው Invite ማድረግ አያቅታቹም እንዳትሰንፉ 😊

ያልጀመረ ካለ ይኋው ሊንክ 👇

https://t.me/tonee_app_bot?start=e3f1865b


Репост из: 🎤🌼ድምፀ ተዋህዶ🌼🎤
እንኳን ለቅዱሳን ሐዋርያት ጴጥሮስ ወጳውሎስ ዓመታዊ የሰማዕትነት በዓል እንዲሁም ለሌሎች ቅዱሳን መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሳችኁ፤ አደረሰን።

"ሰላም ለከ ጴጥሮስ ተልሚድ፤ ዘኢያቅበጽከ ተስፋ ነገረ ኑፋቄ ወካህድ፤ እንዘ ትረውጽ ጥቡዐ ለመልእክተ ክርስቶስ ወልድ፤ አመ ለሊከ ወሬዛ ቀነትከ በእድ፤ ወአመ ልህቀ አቅነተከ ባዕድ።"

"ሰላም ለጳውሎስ ሃይማኖተ ክርስቶስ ዘአግሀደ፤ እስከ አቊሰልዎ በሰይፍ ወመተርዎ ክሣደ፤ ከመ ያግብእ ሕዝበ ህየንተ ቀዳሚ ሰደደ፤ በላዕለ አብዳን ተመሰለ አብደ፤ ወለአይሁድኒ ኮኖሙ አይሁደ።"

❖ ሐምሌ ፭ ❖

✞ ቅዱሳን ሐዋርያት ጴጥሮስ ወጳውሎስ [የምስክርነታቸው መታሰቢያ]፤ ቅዱሳት አንስት:- ዴውርስ፣ ቃርያ፣ አቅባማ፣ አቅረባንያ፣ አክስትያና (የቅዱስ ጴጥሮስ ተከታዮች) [መታሰቢያቸው]፤ ቅዱስ መርቄሎስ ሐዋርያ (የቅዱስ ጴጥሮስ ደቀ መዝሙር) [መታሰቢያው] የሚከብርባት ዕለት ናት✞

Показано 20 последних публикаций.