ኦርቶዶክሳዊ ቅዱሳት ሥዕላት: Ethio Icons


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: не указана


በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱሳት ሥዕላት ዙርያ ስለታሪካቸው፣ ሃይማኖታዊ ትርጉማቸው፣
አሣሣል መረጃ የሚያገኙበት ቦታ፡፡ A channel that discusses about icons of ethiopian orthodox tewahido church. Contact for questions @shihaile or ethioicons@gmail.com or www.ethioicons.wordpress.com

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
не указана
Статистика
Фильтр публикаций


+++ሥዕለ አቡነ ተክለሃይማኖት ክፍል 3 +++

በሠዓሊ ኃይለ ማርያም ሽመልስ (በቅዱሳት ሥዕላት ዙርያ አማካሪ፣ ጥናትና ሒስ አድራጊ)

++++++++++===+++++++++++

ከሥር ከዚህ በፊት በተከታታይ ስለቅላችሁ ከነበረው የአቡነ ተክለሃይማኖት ገድል ላይ የሚገኙ ሥዕሎች ተከታዩ ሥዕሎች ተቀምጠዋል።

እነዚህ ሥዕሎች አባታችን ተክለ ሃይማኖት በአንዲት ስፍራ ዛፍ ያመልኩ የነበሩ ሰዎችን እንዴት አድርገው ወደ ክርስትና እንደመለሱ የሚያሳይ ክፍል ነው። በተለይ ዛፉን ከሚያመልኩት ሰዎች መካከል ዛፏ በተአምራት ወደ አባታችን በሔደች ጊዜ በቅርንጫፎቿ የሞቱት እንዴት ከሙታን እንደተነሱ በድንቅ ሁኔታ ተሥሎ እናገኛለን።

እነዚህ ሥዕሎች በብሪቲሽ ሙዝየም የሚገኝ ብራና ገድለ ተክለሃይማኖት ላይ የሚገኙ ሲሆን ከባለፈው የቀጠሉትን ሥዕሎች ቀርቧል።



ከሥዕሎቹ በተጨማሪ ታሪኩን ተሚገልጸው የገድሉን ክፍል  አብሮ ተያይዟል።

ጥንታዊ ቅዱሳት ሥዕላት ለማየት ለማውረድ፣ ለሌሎች ለማጋራት ከፈለጉ @ethioicons ቤተሰብ ይሁኑ።




+++ሥዕለ አቡነ ተክለሃይማኖት +++

በሠዓሊ ኃይለ ማርያም ሽመልስ (በቅዱሳት ሥዕላት ዙርያ አማካሪ፣ ጥናትና ሒስ አድራጊ)

++++++++++===+++++++++++

በዚህች እለት አቡነ ተክለሃይማኖት ቀኝ እግራቸው ከተጋድሎ ብዛት መሰበሯ እና 7 ዓመት በአንድ እግራቸው ቆመው መጸለያቸውን ይታሰባል። እንኳን ለአባታችን መታሰቢያ እለት አደረሳችሁ።

ከሥር ከዚህ በፊት በተከታታይ ስለቅላችሁ ከነበረው የአቡነ ተክለሃይማኖት ገድል ላይ የሚገኙ ሥዕሎች ተቀምጧል። እነዚህ ሥዕሎች በብሪቲሽ ሙዝየም የሚገኝ ብራና ገድለ ተክለሃይማኖት ላይ የሚገኙ ሲሆን ከባለፈው የቀጠሉትን ሥዕሎች ቀርቧል።




ጥንታዊ ቅዱሳት ሥዕላት ለማየት ለማውረድ፣ ለሌሎች ለማጋራት ከፈለጉ @ethioicons ቤተሰብ ይሁኑ።


+++ሥዕለ እረፍታ ለማርያም+++

በሠዓሊ ኃይለ ማርያም ሽመልስ (በቅዱሳት ሥዕላት ዙርያ አማካሪ፣ ጥናትና ሒስ አድራጊ) 0913 05 2824

++++++++++===+++++++++++
እንኳን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የእረፍት በዓል አደረሳችሁ። ከሥር የእመቤታችን የእረፍትና የግንዘት ታሪክን መሠረት በማድረግ ትውፊቱን ጠብቀው የተሣሉ ጥንታዊያን የብራና፣ የእንጨት ገበታ (ኢቆና)፣ እና የግድግዳ ቤተ መቅደስ ሥዕሎች ቀርበዋል።

የእመቤታችን የእረፍት ሥዕል እንደተሣለበት መደብ እና ያለው የቦታ ስፋት የሚጨመሩ ወይም የሚቀነሱ አካላት አሉበት።

በአጠቃላይ ሲሣል የእመቤታችን ቅዱስ ሥጋ በክብር አልጋ ላይ ሆና (ተቀምጣ / ጋደም እንዳለች)፤
ቅዱስ ነፍሷን ጌታችን በእልፍ አእላፍ መላእክት ተከቦ ሲቀበላት፤
ቅዱሳን ሐዋርያት እያዘኑ ከበዋት መብራት አብርተው፣ መጽሐፍ እያነበቡ እና እያጠኑ፣ ቅዱስ ጷጥሮስ በግርጌ ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ በራስጌ ሆነው፣
ቅዱሳን መላእክት እያጠኑ፣
ቅዱሳን ደናግል አዝነው፣
ቅዱስ ዳዊት በገና እየደረደረ፣ ቅዱስ እዝራ በመሰንቆ እያመሰገነ በአጠቃላይ በአስደናቂ መንፈሳዊ ደስታ ይሣላል።

ማስታወሻ፥ የእመቤታችን የእረፍት ሥዕል ላይ ታውፋንያን አስገብቶ መሣል ጸያፍና ተገቢ ያልሆነ ነው። ምክንያቱም ስንክሳር፣ ተአምረ ማርያም ሆነ ሌሎች አዋልድ መጻሕፍት እንደሚነግሩን ታውፋንያ በዚህ በተቀደሰ መንፈሳዊ ስፍራ አስቀድሞ አልነበረም።

የቤተ ክርስቲያን የሆኑት ቅዱሳት ሥዕላት እንወቅ፣ እንመልከት እና እንጸልባቸው። በስጦታ ይሁን  ወይም በስእለት ለቤተ ክርስቲያንም እንስጥ።


ጥንታዊ ቅዱሳት ሥዕላት ለማየት ለማውረድ፣ ለሌሎች ለማጋራት ከፈለጉ @ethioicons ቤተሰብ ይሁኑ።




+++ሥዕለ እረፍታ ለማርያም+++

በሠዓሊ ኃይለ ማርያም ሽመልስ (በቅዱሳት ሥዕላት ዙርያ አማካሪ፣ ጥናትና ሒስ አድራጊ) 0913 05 2824

++++++++++===+++++++++++
እንኳን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የእረፍት በዓል አደረሳችሁ። ከሥር የእመቤታችን የእረፍትና የግንዘት ታሪክን መሠረት በማድረግ ትውፊቱን ጠብቀው የተሣሉ ጥንታዊያን የብራና፣ የእንጨት ገበታ (ኢቆና)፣ እና የግድግዳ ቤተ መቅደስ ሥዕሎች ቀርበዋል።

የእመቤታችን የእረፍት ሥዕል እንደተሣለበት መደብ እና ያለው የቦታ ስፋት የሚጨመሩ ወይም የሚቀነሱ አካላት አሉበት።

በአጠቃላይ ሲሣል የእመቤታችን ቅዱስ ሥጋ በክብር አልጋ ላይ ሆና (ተቀምጣ / ጋደም እንዳለች)፤
ቅዱስ ነፍሷን ጌታችን በእልፍ አእላፍ መላእክት ተከቦ ሲቀበላት፤
ቅዱሳን ሐዋርያት እያዘኑ ከበዋት መብራት አብርተው፣ መጽሐፍ እያነበቡ እና እያጠኑ፣
ቅዱሳን መላእክት እያጠኑ እና አበባ ይዘው፣
ቅዱሳን ደናግል አዝነው፣
ቅዱስ ዳዊት በገና እየደረደረ፣ ቅዱስ እዝራ በመሰንቆ እያመሰገነ በአጠቃላይ በአስደናቂ መንፈሳዊ ደስታ ይሣላል።

ማስታወሻ፥ የእመቤታችን የእረፍት ሥዕል ላይ ታውፋንያን አስገብቶ መሣል ጸያፍና ተገቢ ያልሆነ ነው። ምክንያቱም ስንክሳር፣ ተአምረ ማርያም ሆነ ሌሎች አዋልድ መጻሕፍት እንደሚነግሩን ታውፋንያ በዚህ በተቀደሰ መንፈሳዊ ስፍራ አስቀድሞ አልነበረም።

ይልቁኑም ወደ መቃብር ስፍራ ቅዱስ ሥጋዋን ሐዋርያት ገንዘውና በከብር በአልጋ ላይ አድርገው እየሔዱ ሳለ በመንገድ የተገናኛቸው። ከዚያም ታውፋንያ ጉዳት አደርሳለሁ ሲል ተቀሰፈ። በእመቤታችን አማላጅነት ደግሞ ካገኘው መከራ ዳነ። በመሆኑም ይህ ተአምር ራሱን ችሎ ከእረፍቷ ሥዕል ቀጥሎ የሚሣል ታሪክ እንጂ የእረፍቷ ታሪክ ላይ አይጨመርም።

ይልቁንም ታውፋንያን የሚያስገባ ተጨማሪ ቦታ ካለ በዚያ ስፍራ በቦታ እጦት የማይሳሉት ቅዱሳን/ት ጨምሮ መሣል ይገባል።


የቤተ ክርስቲያን የሆኑት ቅዱሳት ሥዕላት እንወቅ፣ እንመልከት እና እንጸልባቸው። በስጦታ ይሁን  ወይም በስእለት ለቤተ ክርስቲያንም እንስጥ።



ጥንታዊ ቅዱሳት ሥዕላት ለማየት ለማውረድ፣ ለሌሎች ለማጋራት ከፈለጉ @ethioicons ቤተሰብ ይሁኑ።


✍️ጥር 18 - ቅዱስ ጊዮርጊስ
       ዝርዎተ አጽሙ
"ያ ከሃዲ ንጉስ ዱድያኖስ ግንድ አምጥተው ቅዱስ ጊዮርጊስን በግንድ ላይ እንዲቸነክሩት አዘዘ፤ በላዩም ላይ ሰም አፍስሰው እሳት እንዲያነዱበት አደረገ ፤ ከዚህም በኃላ እንደ መጭመቂያ ሆኖ ከተሰራ የስቃይ መሳሪያ ላይ አወጡት ሰውነቱን እንዲሰነጥቁት እንዲጨምቁት አዘዘ፤  አንጀቱ ሁሉ ወጥቶ ከምድር ላይ እስኪዘረገፍ ድረስ እንዲሁ አደረጉበት ነፍሱ ከስጋው ተለየች የሰማዕቱን ሥጋ አቃጠሉት፤ ፈጩት አመድም ሆነ በቀፎ አድርገው ይድራስ ወደሚባል ተራራ ላይ በነፋስ ዘሩት።

ደብረ ይድራስ ማለት ምድረ በዳ ነው ወታደሮቹ የታዘዙትን ፈጽመው ተመለሱ። ያንጊዜም መብረቅ ነጎድጓድ ታላቅ ንውጽውጽታ ሆነ ምድርም ከመሰረቷ እስክትናወጽ ድረስ ከሰማይ ድምጽ ተሰማ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መላእክትን አስከትሎ በብሩህ ደመና ወረደ በተራራውም ላይ ተቀመጠ አራቱን የምድር ነፋሳት የሰማዕቱን ሥጋ እንዲሰበሰቡ አዘዛቸው። ከሞትም አስነሳው ኃይሉን አሳደረበት ባርኮትም ወደ ሰማይ አረገ።

ከዚህ በኋላ ቅዱስ ጊዮርጊስ እየሮጠ ወታደሮቹን ተከተላቸው ወንድሞቼ ቆዩኝ ከናንተ ጋር ልሂድ እያለ ተጣራ የነዚህ የወታደሮች ቁጥር አራት ነው ስማቸው ህልቶን፣ አግሎሲስ፣ ሶሪስና አስፎሪስ ነው፣ ይህንን ታላቅ ተአምራት አይተው አምነዋል፣ በኋላም በሰማዕትነት ሞተዋል፡፡

ይህ የሆነው ጥር 18 በዛሬዋ ቀን ነው ይህንንም ቀን "ዝርዎተ አጽሙ " ስትል ቤተክርስቲያን ሰማዕቱን አዘክራ ትውላለች፤ በስሙ በታነጹለት አብያተ ክርስቲያናት በሙሉ ታቦተ ህጉ ውጥቶ በደማቁ ተከብሮ ይውላል።

(ገድለ ቅዱስ ጊዮርጊስ ምዕራፍ 6 ፤ 15 - 18)

ከሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ረድኤት በረከት ይክፈለን።

ከዲያቆን ዘማርያም ቴሌግራም ገጽ የተወሰደ።



941 0 11 4 11

በሠዓሊ ኃይለ ማርያም ሽመልስ (በቅዱሳት ሥዕላት ዙርያ አማካሪ፣ ጥናትና ሒስ አድራጊ) 0913 05 2824

++++++++++===+++++++++++
የቅዱስ ጊዮርጊስ የሰማዕትነት ሥዕሎች በአንድ ላይ አቀናብሬ የተዘጋጀ ነው። እነዚህ ሥዕሎች የሚገኙት ከአንዱ (በላይኛው በስተ ቀኝ ያለው ደራጎን ድዴድ ሲያደርግ) በስተቀር በዲማ ጊዮርጊስ ቤተ መቅደስ ግድግዳ በወንዶች አንቀጽ የሚገኙ ሥዕሎች ናቸው። እነዚህ በ፪ኛው የጎንደር አሣሣል የተሣሉ ናቸው።

እነዚህን ሥዕሎች አውርዳችሁ እና አሳትማችሁ በነጻ መጠቀም ይችላሉ። ሠዓሊያንም ተመልክታሁና እንደመነሻ ወስዳችሁ የቅዱስ ጊዮርጊስ ሰማዕትን ሥዕል እየሣላችሁ ለቀጣይ ትውልድ ታሪኩ እንዲዘከር አድርጉ።

የቤተ ክርስቲያን የሆኑት ቅዱሳት ሥዕላት እንወቅ፣ እንመልከት እና እንጸልባቸው። በስጦታ ይሁን ወይም በስእለት ለቤተ ክርስቲያንም እንስጥ።


high resolution ሥዕልም ከሥር ለጥፌዋለሁ።


ጥንታዊ ቅዱሳት ሥዕላት ለማየት ለማውረድ፣ ለሌሎች ለማጋራት ከፈለጉ @ethioicons ቤተሰብ ይሁኑ።


ማስታወቂያ
++++++++++++++++++++++++++++++++++++++

የልዩ ልዩ መንፈሳዊ ፕሮጀክቶች ማስፈጸማያ የሆነው የማኅበረ ቅዱሳን አዲስ አበባ ማእከል የትውልድ ማእከል ግንባታ የመጀመሪያው ቤዝመንት ወለል የአርማታ ሙሌት ተከናወነ።

ፕሮጀክቱን ቶሎ ለማጠናቀቅ በአሐዱ በረከት መተግበሪያ ድጋፍ እንዲደረግም ጥሪ ቀረቧል

ማኅበረቅዱሳን አዲስ አበባ ማእከል ከአሐዱ ባንክ ጋር በመተባበር ለአገልግሎት እንዲሁም ለህጻናትና ወጣቶች ሰብዕና መገንቢያ የሚውል ድጋፍ ማሠባሠቢያ አሐዱ በረከት የተሰኘ መተግበሪያ ተግባራዊ ተደርጓል። መተግበሪያው ከቴሌብርና ከሞባይል ባንኪግ ቀጥታ ድጋፍ ማድረግ የሚያስችል መሆኑ ተገልጿል።
በመሆኑም የማኅበረ ቅዱሳን አባላትና የዓላማው ደጋፊ ምእመናን ባሉበት ሆነው ሞባይላቸውን ብቻ በመጠቀም በአሐዱ በረከት መተግበሪያ ድጋፍ እንዲያደርጉና የበረከቱ ተሳታፊ እንዲሆኑ ጥሪ ቀርቧል ።
ከታች የተያያዘውን ሊንክ በመጠቀም ድጋፍ ያድርጉ

https://ahadubereket.com//campaigns/detail/5


እንኳን አደረሳችሁ ለብርሃነ ጥምቀቱ

Показано 11 последних публикаций.