በእድሜ የገፉ ሰዎች፣ የነፍሰ‐ጡር እና አጥቢ ሴቶች ጾም ሸሪዓዊ ብይን
ጥያቄ፡- ጾም መጾም ያቃታቸው ሽማግሌዎችና አሮጊቶች መዳን ያልቻሉ በሽተኞች እርጉዝ ሴቶች እና ጾም ከጾምን ጡታችን ይደርቃል ብለው የሰጉ አጥቢ ሴቶች የረመዷንን ጾም አፍጥረው ለእያንዳንዱ ቀን ምስኪን ማብላት ይችላሉ?
መልስ፡-
1ኛ፡- በእድሜ መግፋት የተነሳ የረመዷንን ጾም መጾም ያልቻሉ ወይም በጣም ተጨናንቀውና ከብዷቸው የሚጾሙ ሽማግሌዎች እና አሮጊቶች እንደዚሁ ጾሙን መጾም ያልቻለ ወይም በግድ የሚጾም መዳኑ ተስፋ የሌለው በሽተኛ የረመዷንን ጾም እንዲያፈጥሩ ተፈቅዶላቸዋል፡፡ ነገር ግን ቤተሰቡን ከሚመግበው እህል ከስንዴ፣ ከተምር፣ ከሩዝ እና ከመሳሰሉት የአንድ ቁና ግማሽ (አንድ ኪሎ ተኩል) ለእያንዳንዱ ያፈጠሩበት ቀን አንዳንድ ሚስኪን ማብላት ይኖርባቸዋል፡፡
አላህ እንዲህ ብሏል፡-
{لاَ يُكَلِّفُ اللّهُ نَفْساً إِلاَّ وُسْعَهَا.. } (البقرة: ٢٨٦)
“አላህ ነፍስን ከችሎታዋ በላይ አያስገድዳትም፡፡” (በቀራህ፡ 286)
{..وَمَا جَعَلَ عَلَيْكُمْ فِي الدِّينِ مِنْ حَرَجٍ.. } (الحج:٧٨)
“በእናንተ ላይ በሃይማኖቱ ውስጥ ምንም ችግር አላደረገባችሁም፡፡” (ሀጅ፡ 78)
{...وَعَلَى الَّذِينَ يُطِيقُونَهُ فِدْيَةٌ طَعَامُ مِسْكِينٍ... } (البقرة :١٨٤)
“በእነዚያም ጾምን በማይችሉት ላይ ቤዛ ድሃን ማብላት አለባቸው፡፡” (በቀራህ፡ 184)
قال ابن عباس : "نزلت رخصة في الكبير والمرأة الكبير وهما لا يطيقان الصيام : أن يفطرا ويطعما عن كل يوم مسكينا" رواه البخاري : ٤٥٠٥)
አብደሏ ብን አባስ እንዲህ ይላሉ፡-
“ይህ የቁርዓን አንቀጽ ጾምን መጾም ለማይችሉ ሽማግሌዎችና አሮጊቶች እንዲያፈጥሩና ለእያንዳንዱ ቀን ምስኪን እንዲያበሉ የወረደ ነው፡፡” ቡኻሪ: 4505)
በሽተኛ ሆኖ ጾም መጾም ያልቻለ ወይም በጣም ከብዶት የሚጾም ሊድን ያልቻለ በሽታ ያለበት ሰው ሸሪኣዊ ብይናቸው ልክ ጾም ያቃታቸው ሽማግሌዎች እና አሮጊቶች አይነት ነው፡፡
2ኛ፡- በነፍሷ ወይም በተጸነሰው ልጅ ላይ ጉዳት ይመጣል ብላ የፈራች ነፍሰ‐ጡር፤ ወይም በነፍሷ ወይም በምታጠባው ህጻን ላይ ችግር ይመጣል ብላ የሰጋች አጥቢ ሴት ልክ ከበሽታው መዳን እንዳልቻለው ሰው ያፈጠሩበትን ቀን ቆጥረው ቀዷእ የማውጣት ግዴታ አለባቸው፡፡
وبالله التوفيق ، وصلى الله على نبينا محمد وآله وصحبه وسلم.
فتاوى اللجنة الدائمة للبحوث العلمية والإفتاء (10/160
@tewihd