𝐇𝐚𝐟𝐮 𝐢𝐬𝐥𝐚𝐦𝐢𝐜 𝐩𝐨𝐬𝐭™


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Другое


亗 ꧁﷽꧂ 亗
🤍𝑤𝑒𝑙𝑐𝑜𝑚𝑒 𝑡𝑜 ᴏᴜʀ 𝑐ℎ𝑎𝑛𝑛𝑒𝑙ᥫᩣ
✔Channel Objective🎊🎊🎊🎊🎊
➻Islamic teachings💛
➻Current information🤗
➻Hadiths and Qurans 🤩
➻በዋናነት #መጅኑኑ_ለይላ🧕 የፍቅር ታሪክ ከመፅሀፉ ምንም ሳይጨመርበት ሳይቀነስበት የሚያገኙበት ብቸኛና እንቁ💎 ቻናል ነው❤❗️
CROSS🔄 @Waver_boy1

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Другое
Статистика
Фильтр публикаций


✋😯ቆይ ከመተኛታችሁ በፊት ሁላችሁም❗️🔰
በተለያዩ ነገሮች ቆሽሾ የዋለውን ቀልባችንን ለማጥራት አጭር ቁርዓን ተጋበዙልኝ😇🤗

✯ ወላሂ ሀቂቃ ማስታወቂያ ነው ተቀላቀሉ ✯


🔖ሱብሒ  እነሳለሁ ብለህ  ነይተህ  ተኛ
ለሱብሂ  ሶላት መነሳትህ  ለአምላክህ ያለህን ውዴታና ታማኝነት  የምትገልፅበት ነው::

 
🌟 የፈጅር_ሶላት  እንደ  ጦርነት ነው ጠንካሮች  ብቻና ብቻ ናቸው ሚገኙበት።

🔖መልካም ለይል🔖😊
 
        


💢እስልምና ላይ የሚሰሩ የተደበቁ #ሴራዎችን ከኢስላሙ ዓለም🌍 መረጃዎች ጋር እየፈለፈለ የሚያደርስ አስደማሚ ቻናል ተቀላቀሉ❗️

🚨ወላሂ ሐቂቃ ማስታወቂያ ነው🚨


╔═══❖•ೋ° °ೋ•❖═══╗
   .......
#መጅኑኑ_ለይላ❤️‍🔥🧕......
   ✎ ፀሐፊ፦ ሷሊህ አስታጥቄ
   ✎አዘጋጅ፦Mukerem
╚═══❖•ೋ° °ೋ•❖═══╝

┎━─━─━─━─━─━─━─━┒
@Hafu_islamic_posts የተዘጋጀ
┖━─━─━─━─━─━─━─━┚

      ╔════•| ✿ |•════╗
               የተዳፈነው ፍቅር
      ╚════•| ✿ |•════╝



ቀናት በተቆጠሩ ለይላ እና ቀይስ ይበልጥ በተቀራረቡ ቁጥር በልባቸው ውሰጥ ተዳፍኖ የነበረው ፍቅር አመዱን ገልጬ ካልወጣሁ እያለ ነው፡፡ በዚያ ፍጥነት ይሆናል ብለው ባልገመቱት መንገድ ተጋጋመ። መተያየታቸው ለኳሽ ሆኖ በሁለቱም ልብ ውስጥ ፍቅር ተያያዘ፡፡ ነገር ግን ሁለቱም ይፋቀሩ እንጂ ፍቅራቸውን አልተነጋገሩም። ሁለቱም ፍቅርን ያህል ነበልባል አዘል ፍም ታቅፈው እየተለበለቡ ነው:: ችላ አይሉት ነገር የዋዛ አይደለም፡፡ ከቃጠሎው ጋር የተጣመረው የመሃባ ስቃይ ደሰታንም አምቋል፡፡ ይዘውት አይቆዩ ደግሞ ፍጅቱ አጥንት ድረስ ዘልቆ የሚጠዘጥዝ ነው፡፡ ግራ የገባ ነገር፡፡
ሁለቱም ተመሳሳይ ስቃይ እየተጋሩ ነው፡፡ ቢሆንም እንዳይታወቅባቸው ይጥራሉ። በተለይ ከጓደኞቻቸው ጋር ሰብሰብ ብለው ሲጨዋወቱ በከፍተኛ ሁኔታ ስሜቶቻቸውን ለመደበቅ ይሞክራሉ፡፡ ሁለቱም ያፈኑት የሚንተከተክ ፍቅር ይፋ ባይታይም እንፋሎቱ ግን በአቅራቢያቸው ላሉት ምልክት እየሰጠ ነው።
በእርግጥ ቀይስ ለአንዳንድ የቅርብ ጓደኞቹ ስለ ስሜቱ አጫውቷቸው ነበር፡፡ ፍቅሩን ለሷ ለማካፈል ያለውን ፍላጎትም አዋይቷቸዋል፡፡ ግን አንዱ ይቅርብህ እጁን ለትዳር መጠየቅ እንጂ ፍቅር ይፋ ማውጣት ትርፉ ውርደት ነው፡፡ ሌላኛው አትሆንህም አባትህና አባቷ ፀበኛ ስለሆኑ ላይድሩህ ነገር አትልፋ፡፡ ይባሱን ስቃይ አትግዛ ደግሞ እሷ ባትወድህና ምላሿ ሚያደማህ ቢሆንስ ምን ሊውጥህ ነው? ደግሞ ቆፍጠን ማለትና ወንድ ወንድ መሽተት፤ ከቻሉ አንዷን አግብቶ መኖር እንጂ ለአንዲት ኮረዳ የምን መብረክረክ ነው? እያሉ ኩም አድርገውታል፡፡ እሱ ግን እሷን እንጂ ሌላማ አይደረግም እያለ የመፍትሄ ሃሳብ ነው ያለውን እየዘረዘረ ይከራከራቸዋል፡፡ እነሱም ይመልሱለታል፡፡ የምታስበው ሁሉ ግራ ነው ይሉታል፡፡ ሲታክታቸው ጥለውት ይሄዳሉ።
ቀይስ አይገባችሁም እያለ ይጮሀል።እነሱንም ፍቅር እንዲደቁሳቸውና እንዲያዩት ይመኛል።
አባት ሙለወሕ በዚያ በኩል ሚስት መፈለጉን አጧጡፎታል፡፡ አንድ ቀን ምሽት ላይ ቀይስ ጠጋ ብሎ ልጄ በል እንግዲህ ወደ ንግዱ ከመሄድህ በፊት ልድርህ ነው አለው።ቀይስ በደሰታ ፊቱ ፈካ፡፡ አባትም በልቡ ለካ ልጄ ባይናገርም ይፈልግ ኖሯል ብሎ ደስ አለው። አስከትሎም ውብና ወላድ የሆነች ቆንጆ ኮረዳ ነው የምድረህ! አንተ ያየሃት ካለች ወዲህ በል! ካልሆነ ግን እኔ ካየኋቸው ላስመርጥህና ቶሎ ሽማግሌ እንላክ አለ። ቀይስ ያኔ አፉ ተሳሰረ፡፡ እንዴት ሽሸጉን ያውጣው? የሱ አባትም ቢሆን የለይላን አባት ይሄ ስም አጥፊ እያለ ሲወቅሰው ደጋግሞ ሰምቷል፡፡ ለይላን ዳርልኝ ሊለው አሰበና፤ አንተ ቅዠታም ብለህ ብለህ ከጠላቴ ጋር ልታዛምደኝ ያምርሃል ብሎ የሚያንባርቅበት መሰለው። አባቱን ደግሞ ይወዳልም ይፈራልም፡፡እናም አንገቱን ደፋ።
አባትሞ ያየው የለም ማለት ነው ብሎ የእገሌን ልጅ አይተሃታል ቁመቷ ብትል ውበቷ በዛ ላይ የነ እገሌ ዝርያ ናት፡፡ እህቶቿም ሆኑ እናቷም ወላዶች ናቸው፡፡ እናቷን አይተህ ልጅቷን አግባ የሚባለውኮ እውነት ነው። እናቷ ወላድ ከሆነች ልጅቷም እንደዛው ነው የምትሆነው ይለዋል። ቀይስ ግን ለይላ ካላለው በስተቀር የመቀበል ፍላጎቱ የለውም፡፡ አይ አትሆንም ደስ አትለኝም አለ ቀይስ ፊቱን ጭፍግግ አድርጎ።ከአባቱ ምርጫ ውስጥ ለይላ ልትኖር ትችላለች የሚል የተስፋ ጭላንጭል ነበረው። ግን አልሆነም፡፡
ምሽቱን አባት የመንደሯን የደረሱ ሴቶች ስምና መረጃ እየዘረዘረ አንዷን እንዲመርጥ ቢለፋም ቀይስ አንዷንም እሷ ትሁን በቃ ብሎ ሊሰማማ አልቻለም፡፡ አባት ጨንቆት የምትወዳት ካለች ንገረኝ አለ። ቀይስ አሁንም ዝም አለ፡፡ ሶሪያ ወይም ዒራቅ ሳለን አንዷ ልብህን ወስዳዋለች መሰል። ከዚያ ነው እንዴ የምትፈልገው? እኔኮ የመንደራችን ሴቶች ይሁኑ ብዬ የማስመርጥህ አኗኗራቸው ከአኗኗርህ ጋር ስለሚጣጣም አትቸገርም ብዬ ነው እያለ ይለፈልፋል።ቀይስ ግን ልቡ አልተገኘም::ይሄኔ አባትየው ታክቶት ጥሎት ሄደ።ሙለወሕ የቀይስን እናት እስኪ አንቺን ከሰማ የሚፈልገውን ጠይቂው ብሎ ላካት። እናትም ወደ ቀይስ ሄዳ ፀጉሩን እየዳበሰች በፍቅር ወግ የማረከችው ሴት እንዳለች ጠየቀችው። ቀይስ ግን አሁንም ሊናገር አልፈለገም፡፡ መጨረሻ ላይ በቃ እራስህ ፈልግና እገሊትን ዳሩኝ በለን፡፡ በመንደሩ ወጣ ወጣ እያልክ ሴቶቹን እያቸው አለችው። ይሄን ጊዜ ቀይስ ተስማማ። ወትሮም ጊዜ መግዣ ምክንያት ነበር የሚፈልገው:: ጉዞህ መራዘም የለበትም ቶሎ አሳውቀን እያለችው እናቱም ሄደች፡፡
ቀይስ አሁንም ከለይላ ጋር ይገናኛል፡፡ በማህበር ከጓደኞቻቸው ጋር ተሰብሰበው በጋራ የሚጨዋውቁበት ጊዜም ይበረክታል። በተለይ ፍቅራቸውን አምቀውታል። ቢሆንም ግን ሁለቱም በራሳቸው መንገድ ነገራቶችን በማስተዋል ለመረዳዳት ይሞክራሉ፡፡ በተለይ ለይላ ከሌሎች ጓደኞቹ ጋር በመቀራረብና እሱን ጣል ጣል በማድረግ በቅናት የሚሆነውን የቆሪጥ እያየች ለሷ ያለውን ፍቅር ለመለካትና ድምዳሜ ላይ ለመድረሰ ትሞክራለች፡፡ ምልክቶችሞ ታያለች፡፡ ሆኖም የልቧ አይደርስላትም።በዚህ አድራጎታቸውና በየልባቸው ያለውን ፍቅር ለመለካት በሚያደርጉት ጥረት በጓደኞቻቸው ይፋቀራሉ በሚል ቢጠረጠሩም ያፈጠጠ ነገር ስለሌለ አፍ አውጥቶ መናገር ከባድ ሆኗል።



🔥Is Continued… … …  …
❤️ℓιкє..ιѕ ιмρσятαит......


#መጅኑኑ_ለይላ ከደቂቃዎች በኋላ ይለቀቃል🤌

መፅሀፉን ያላነበባችሁ ትልቅ እድል ነውና አንብቡት
እላለሁ 🫡


ሰለፎች እንዲህ ይሉ ነበር💙

"ከ እድሜህ 8 ቀን ነዉ የቀረህ ብባል አገባለሁ አላህ ፊት ላጤ ሆኜ መቅረብ አልፈልግም"

ሱብሀነላህ

ፈተዘወጁ ያ አኺ ወያ ኡኽቲ
😁❤️

550 0 0 16 38

ለሰው ልጅ ክብር የሚሰጠው በምንድን ነው ጀማኣ


.

አላህ ሆይ ምንም በማናውቀው ምክንያት የሚቀየርብን ወዳጅ አትስጠን 🤲


የሰው ልጅ ህያው ለመሆን ዝግጁ ሳይሆን ይወለዳል፣
ለወዲያኛው አለም ዝግጁ ሳይሆን ይጓዛል ፣
በሁለቱ ጎራዎች አስከፊው ልዩነት
ድንገተኛው ጉዞ ነው‼️
ኢላሂ መጨረሻችንን አሳምርልን
🤲


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
ቁርዓን የልብ ብርሃን የምሽት ስንቅ📖🩵🎧
.

.

አያተል ኩርሲይ በተቀራበት ቤት ሸይጧን አይገባም።


ንግግራቼዉ እንደ ማር እመጣፍጠዉ ዉዱ ነብያችን 🤍

ከእለታት አንድ ቀን ነቢዩ ሙሐመድ ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም ዘንድ አንድ
ከገጠር የመጣ ኑሮው ያልሰመረለት [ድሃ] ግለሰብ ሰሃን
ሙሉ ወይን ስጦታ ያመጣላቸዋል፡፡ነብዩም ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም ስጦታውን
ተቀብለው ወይኑን መብላት ጀመሩ..የመጀሪያውን ጎርሰው ፈገግ
አሉ..ሁለተኛውንም ጎርሰው ፈገግ አሉ..ግለሰቡም እጅጉን
ተደሰተ..የነብዩ ጓዶች ሰሃቦች ሁሌም ለነብዩ 🤍 ስጦታ
ሲመጣላቸው ስለሚያካፍሏቸው ይህንን ጣፋጭ ወይን እንዲያካፍሏቸው በጉጉት ይጠብቃሉ..የአላህ መልእክተኛ ግን
ሳያካፍሏቸው እያንዳንዱን የወይን ፍሬ እየበሉ እና ፈገግ እያሉ
ሁሉንም በልተው ጨረሱ.. ስጦታ አቅራቢው እጅግ በጣም
ተደሰቶ..ስጦታውንም ስለወደዱለት አመስግኖ ሄደ..አንዱ ሶሃባ ጠጋ ብሎ ነብዩን ጠየቃቸው

‹‹የአላህ መልእከተኛ ሆይ..ምነው ሳያካፍሉን?›› እሳቸውም 🤍
ፈገግ ብለው መለሱ ‹‹ሰወዬው መደሱቱን አይታችኋል አይደል?!..
ወይኑን ስቀምሰው በጣም ይመር ነበር..ባካፍላችሁ አንዳችሁ
ግለሰቡን የሚያስከፋ እና ደስታውን የሚያደፈርስበትን ነገር
እንዳታሳዩት ብየ ስለሰጋሁ ነው ብለው መለሱላቸው! የኛ ዉድ መሪ🤍❤️

ሰሉ አለ ነቢ💙


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
Tnsh feta belu


እዴት አመሻቹ የኔ ውዶች❤️❤️❤️

862 0 0 11 26

╔═══❖•ೋ° °ೋ•❖═══╗
   .......
#መጅኑኑ_ለይላ❤️‍🔥🧕......
   ✎ ፀሐፊ፦ ሷሊህ አስታጥቄ
   ✎አዘጋጅ፦Mukerem
╚═══❖•ೋ° °ೋ•❖═══╝

┎━─━─━─━─━─━─━─━┒
@Hafu_islamic_posts የተዘጋጀ
┖━─━─━─━─━─━─━─━┚

      ╔════•| ✿ |•════╗
           የጥርጊያው ዱብዳ
      ╚════•| ✿ |•════╝




ቀይስ ከአብሮ አደጉ ጋር በመንደሩ እየተንቀሳቀሰ አንድ ጥርጊያ ላይ ሲደርሱ ድንገት ውዝ ሆነ። ወሬውን አቆመ:: ጓደኛው ድንገት ዝም ማለቱ ገርሞት ወደሱ ሲዞር ልጁ እይታውን ወደ አንድ አቅጣጫ አፍጥጦ ሃውልት ሆኗል። ወደሚመለከትበት አቅጣጫ ሲዞር ለይላን ከሩቅ አያት። ቀይስ ዓይኑን ባለበት እንደተከለ ከአገጩ ብቻ ወደ ጓደኛው ዘምበል ብሎ ለይላ ናት አለ በለሆሳስ፡፡ አዎ አለ ጓደኛው ለይላ ጉፍታዋን እነ ቀይሰ መንደር ስትደርሰ ፊቷን እንደምትሸፍንበት ታውቅ ነበር። ግን ድንገት ተቀደመች፡፡ እሷም በጥርጊያው በዚያኛው ገጥ ቀጥ ብላ ቆማለች። የደነገጠችው ቀይስን ሰላየችው ሳይሆን ቀይስ ስላያት ነበር። ቀድሞውኑ እንዲያገ አልፈለገችም። ስለ ሰሜቱ አታውቅም፡፡ ፊት ቢነሳኝሰ የሚል ሃሳብ ገብቷታል። የከተማዎቹን ኮረዶች ውበት ታውቃለች፡፡ የትዳር ጥያቄ ሲመጣላት እንኳን ቶሎ ትዝ የሚላት ቀይስ ቢሆነሰም ትዳር ድረስ እንደማትደርስ ታስባለች። አባቷ ለአባቱ ያለውን ጥላቻ ማወቋና ቀይስ በከተማ ሴት ሊጠለፍ መቻሉን አብዝታ ማሰቧ ያመጣባት ፍርሃት ቀመስ እምነት ነበር።
ቁመቷ አጠር ቢልም ሁለመናዋ ጎምርቷል። ፊቷ ድምቀትን ከጨረቃ የምትዋስ እንቡጥ ፅጌሬዳ መሰሏል፡፡እጅጉን አምሮባት፣ የልጅነት ወዟ ሳይጠፋ ወጣትነት እየተዋሃዳት ነው፡፡ ትንሿን ለይላም አላጣባትም፡፡ ግን አዲስና ሌላ የቁንጅና ሰገነት ላይ የምትንጎራደድ ለይላም ጨምሮ አጊንቶባታል። ልዩ መስህብ የማይጠገብ እይታ፡፡
የትዝታ ሞገድ ቀድሞ የነበረውን የተቀበረ ፍቅር ወጀቡን አክሎ መላ ሰውነቱን ለይላ ባህር ውስጥ ሲዘፍቀው ታወቀው᎓᎓ ከልጅነት እስከ እውቀት ያለውን የሷና የሱ የወዳጅነትና የአብሮ አደግነት ትውስታ ከምናቡ ቋት ጨልፎ አዲስ ፍቅር ከሚሉት ጦስ ጋር ኣዋህዶ ልቡ ውሰጥ ሲሸቀሸቅ ተሰማው፡፡ ለይላ አላት፡፡ ቀይስ አለችው:: ተቀራረቡ ዝም ብለው ተያዩ። መተቃቀፍሞ መነካካትም አይታሰብም የሁለቱም ጓደኞች ታዛቢ ሆነው ተሰይመዋል። በጣም አድገሻል ውብ ሆነሻል አላት፡፡ አንገቷን ደፍታ እና ብቻህን እንዲያምርብህ ነበር ፍላጎትህ ብላ ተሸኮረመመች፡፡ በጥቂቱም ቢሆን አፍ የፈቱ ያህል ተሰምቷቸው እፎይ አሉ፡፡ ያን ቀን ጥቂትም ቢሆን አውርተው
ተለያዩ።
ቀይስና ለይላ ከቀናት በኋላ ወደ ድሮው ቀረቤታቸው ተመለሱ፡፡ ሁለቱም አድገዋል። ነገራቶችም ጠጠር እያሉ ነው፡፡ የልጅነት የነበረው ፍቅር አዳዲስ ስሜቶችን እያስተናገደ ከበፊቱ እየባሰ ነው። በራሳቸው ላይ አዳዲስ ነገሮችን ያስተውሉ ይዘዋል። መለያየት እየከበዳቸው ናፍቆትም እየታወቃቸው ሄዷል። ሁለቱም በየፊናቸው የሚሰማቸውን ስሜት አዳፍነው እንደ ልጅነታቸው ይጨዋወታሉ፡፡ ባይሆን አሁን ነፍስ አውቀዋልና መገናኘታቸው የቤተሰብ ፀብ እደሚያጋግም ተገንዝበዋል። እናም የሚገናኙት በከፍተኛ ጥንቃቄ ነው ::
የቀይስ አባት ቀይስን ለመዳርና ትመጥነዋለች የሚላትንም ሴት ለመምረጥ እየተንጎዳጎደ ነው። ምንም የንግድ ጉዞው ቢራዘም ሳያገባ ላይልከው ለራሱ ቃል ገብቷል። ቢሆንም ለቀይስ አልነገረውም። ቀይስ እየወጣ ውሎ ይገባል፡፡ ለይላም ተደብቃ እየወጣች ከቀይስ ጋር ትንሽ ቆይታ ትመለሳለች። የቀረውን ቀን ቀይስ ከጓደኞቹ ጋር ይውላል፡፡ ሰለ ለይላ ይጠይቃቸዋል፡፡ ያወራቸዋል። በጀርባው ተንጋሎ ስለሷ ያስባል፡፡ ያሁኑ ውዴታ ከልጅነታቸው ልቋል። ሁለቱንም ብቻቸውን ያስቃቸዋል። በህልማቸው ያቀራርባቸዋል። ስንኝ ያስቋጥራቸዋል ወደፊትን ያሳስባቸዋል። ሁሉንም እያስረሳቸው መጥቷል። በተለይ ቀይስ ነጋዴ መሆኑን እንኳ ማስታወስ  አይፈልግም፡፡ አሁን ላይ እንደ ቀደሙ ለይላ እያለች የበኑ ዓሚርን ጎሳ ጥሎ መውጣት አይታሰብም ። የእስከዛሬው ያለሷ ያሳለፈው ያ ሁሉ ጊዜ ከንቱ መሰለው። አሁን ላይ እሷን በማየት ጥሙን ይቆርጣል፡፡ ይጠግባል። ይደሰታል፡፡ አዲሱ የገነፈለ ፍቅር ድንቅ ገጣሚነቱን ሊያፈነዳው ቀጠሮ ይዟል፡፡


🔥Is Continued… … …  …
❤️ℓιкє..ιѕ ιмρσятαит......


#መጅኑኑ_ለይላ ከደቂቃዎች በኋላ ይለቀቃል🤌

መፅሀፉን ያላነበባችሁ ትልቅ እድል ነውና አንብቡት
እላለሁ 🫡


ሀቅ ነው


ስምህ ነስሩ ሆኖ ከሚስትህ ጋር በፍቅር እየኖራችሁ ስሜን ተርጉሚልኝ ስትላት፦

ነ....ነብዩ ሙሀመድ 🤍 የሚወድ💙
ስ.....ስስት የማያቅ👍
ሩ..... ሩህሩህ የሆነ🥺
ነስሩ😊

ልክ ደሞ ሚስትህን አስቀይመሀት ስሜን ተርጉሚሊኝ ስትላት ደሞ😁
     ነ.....ነገረኛ የሆነ
    ስ.....ስራፈት ስስታም
    ሩ......ሩቅ ለፍቅር
     ነስሩ😠😁❤

1k 0 0 49 56



يا الله 🥹
ልነሳ ነው መሰል መውደቅ አብዝቻለው...🤲


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
🌙 የምሽት ስንቅ🎧

📖ቁርዓን

Показано 20 последних публикаций.