👑 አዳም ረታ 👑


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha
Toifa: ko‘rsatilmagan


ቀንዎን ያሳምሩ
👉የአዳም ረታ እና ሌሎችም እውቅ ደራሲያን ስራዎች
👉ግጥሞች
👉የአማርኛ መፅሀፍት በ pdf
👉 አዝናኝ እና ቁምነገር አዘል ፅሁፎች
👉ሙዚቃዎች እና ሌሎችም የምትፈልጓቸውን አንድ ላይ በ አዳም ረታ ያግኙ።
👉 የመፃህፍት ጥቆማ
@AdamuReta
@AdamuReta
@AdamuReta
For cross promotion contact
@isrik
@isrik

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Toifa
ko‘rsatilmagan
Statistika
Postlar filtri


   ከላይ አርነት ስር የተዳሰሰዉ እቴሜቴ ሎሚ ሽታ የተሰኘዉ የአዳም የአጫጭር ልብ ወለዶች መድበል ከአለንጋና ምስር እና ይወስዳል መንገድ ያመጣል መንገድ በተጨማሪ ሽግግር ሽሽት ተብሎ የሚጠራዉ የግብዝነት አይነት የተፈከረበት ሥራ ነዉ፡፡ ፍልስፍናዊ ሴማው የተዳሰሰው የስብሐት ጢም በተሰኘዉ አጭር ልብ ወለድ ውስጥ ነዉ፡፡ በእዚህ አጭር ልብ ወለድ ዉስጥ የተሳለችዉ ዋና ገጸባሕርይ ፋኖስ ደራሲ ባሏን ስብሐትን በመክዳት ለበን ወደተባለ የቀድሞ ወዳጇ ስትኮበልል የምናገኛት ገጸባሕርይ ናት፡፡ አዳም እንደሚነግረን፣ ይች ገጸባሕርይ ስብሐትን ከድታ ከለበን ጋር የማገጠችዉ በሁለት ምክንያቶች ነዉ፡፡ የመጀመሪያዉ ምክንያት፣ ስብሐት የምትፈልገዉን ወሲባዊ ደስታ ሊያሟላላት ባለመቻሉ ነዉ፡፡ አዳም በእዚህ ትረካ እንደሚነግርን፣ ስብሐት በጠራራ ሌሊት በፍትወት የምትቀጣጠል እጅግ ዉብ ሚስቱን ለቆ ለብቻዉ ጠረጴዛ ላይ ተደፍቶ ድርሰት ሲቸከችክ የሚያድር ሰዉ ነዉ፡፡ ሁለተኛዉ ምክንያት፣ ስብሐት በቁስ ያልደረጀ ነጭ ደሃ ደራሲ በመሆኑ ነዉ (አዳም፣ 2001)፡፡  
   ፋኖስ ለበን ወደተባለዉ የቀድሞ ወዳጇ ኮብልላ መማገጧ የፈጠረባትን የኅሊና ፀፀት ስትለቃለቅ የምናገኛት ወሲባዊ ደስታ የነፈጋት ባሏ ስብሐት ለዉስልትና እንደዳረጋት ለራሷ በመንገር ጣቷን እሱ ላይ በመቀሰር ነዉ፡፡ አዳም ከላይ በተጠቀሰዉ ትረካ ዉስጥ የሚከተለዉን ጽፏል፦ “ወረቀት ላይ ጎብጠህ የሌለ ነገር ስትፈጥርና ስትጠነቁል እኔ በቁም ያለሁትን ስትረሳ ልጅት ምን ላድርግ … ላይፍ ኢዝ ሾርት” (አዳም፣ 2001፡ገጽ 35)፡፡ ይህ የፋኖስ ጠባይ ከላይ እንዳየነዉ በግብዝነት ዉስጥ የመዉደቅ ምልክት ነዉ፡፡

ክፍል ሁለት ይቀጥላል...

@AdamuReta
@isrik


   ሎሚ ሽታ ከላይ በነገረችን ምክንያት ባሏን ከድታ አስናቀ የተባለ ወሲባዊ አምሮቷን ያረካላት ሰዉ ቤት መግባትን መርጣለች (አዳም፣ 2001)፡፡ ሎሚ ሽታ ለራሷ ብቻ የተተወ ሁለት ምርጫ ነበራት፡ አንድ በድብርት ተከባ ከሰማንያ ባሏ ታደሰ ጋር ዘመኗን መዝለቅ፡፡ ሁለት “የስጋዋም የመንፈሷም ምግብ” የሆነዉን አስናቀን መርጣ መኮብለል፡፡ የሎሚ ሽታ ምርጫ ሁለተኛዉ ነዉ፡፡  
              ፪. ግብዝነት 
   ግብዝነት ግብዝ  faith)obert Wicks.በሳትረ ፍልስፍና ዉስጥ ከሚገኙ ዐቢይ ጭብጦች መካከል አንዱ ነዉ፡፡ ግብዝነት ራስን በመሸንገል ገሀድ እና ሽግግር ብለን የምንጠራቸዉን ሁለቱን የሰዉ ልጅ ደረቅ ሐቆች የመካድ ወይም የመሸሽ ተግባር ነዉ፡፡ የሰዉ ልጅ ፍፁማዊ እርነትን የተጎናፀፈ ፍጡር መሆኑን ኅሊናዉ እያወቀ ራሱን የሚያታልለዉ ብቸኛዉ የሕይወቱ ፈጣሪ እሱ መሆኑን በመገንዘቡ ሳቢያ ከሚፈጠርበት ጭንቀት እፎይ ለማለት ነዉ፡፡ ከእዚህ ጭንቀት እፎይ ለማለት የሚሞክረዉ ደግሞ ራሱን ኅሊና ያለዉ ፍጡር (conscious being) በመሆኑ ምክንያት የተቀዳጀዉን አርነቱን ተጠቅሞ ልክ እንደ ጠረጴዛ ወይም ወንበር ማንነቱን መለወጥ የማይችል ቁስ አድርጎ በመቁጠር ነዉ፡፡ ይህ አይነቱ ግብዝነት ሽግግር ሽሽት ተብሎ ይጠራል፡፡ በተጨባጭ ግን፣ የሰዉ ልጅ የተጎናፀፈዉን አርነት ተጠቅሞ የታሪካዊ ሁኔታዉን (historical milieu) እግረ ሙቅ በጥሶ አዲስ ሕይወት የመፍጠር ኃይል አለዉ፡፡ ሳትረ ሽግግር ብሎ የሚጠራዉ ይህን ሐቅ ነዉ፡፡ ስቴፈን ፕሪስት (2001) እንደ ጻፈዉ፣ የሌሎችን ፍረጃ አሜን ብሎ መቀበል (being-for-others) ሌላኛዉ ሽግግር ሽሽት ተብሎ በሚጠራዉ የግብዝነት አይነት የመዉደቅ መገለጫ ጠባይ ነዉ፡፡
   እኛ የሰዉ ልጆች ያለንበትን ነባራዊ ሁኔታ የሚገልፁ ቋሚ ደረቅ ሐቆችን (fixed facts) ሳትረ ገሀድ ብሎ ይጠራዋል፡፡ እነዚህም ደረቅ ሐቆች ቁመታችን፣ ብሔራችን፣ የቆዳችን ቀለም፣ ፆታችን፣ ዘራችን፣ ነፃ ፍጡር መሆናችን፣ ማኅበራዊ መደባችን፣ ዜግነታችን… ወዘተ ናቸዉ፡፡ የሰዉ ልጅ በእርግጥ የሆነዉን ማንነቱን የሚክድ ወይም የሚሸሽ ከሆነ ገሀድ ሽሽት ተብሎ በሚጠራዉ የግብዝነት አይነት ወድቋል፡፡ ገሀድን የሚሸሽ ግለሰብ ደካማ ባሕርዩን ለመቀበል ፈቃደኛ አይደለም፡፡ በሳትረ ቢንግ ኤንድ ነቲንግነስ ዉስጥ የተጠቀሰዉ ግብረ ሰዶም ሰዉ ገሀድ ሽሽት ብለን የምንጠራዉ የግብዝነት አይነት ምሳሌ የሚሆን ግለሰብ ነዉ፡፡
   ከላይ ፍፁማዊ አርነት ዉስጥ በጠቀስኩት ኦቾሎኒ በተሰኘዉ የአዳም አጭር ትረካ ዉስጥ የሚገኘዉ ዋና ገጸባሕርይ ስምዖን ሽግግር ሽሽት ብለን በምንጠራዉ የግብዝነት አይነት የወደቀ ሰዉ ነዉ፡፡ ስምዖን ሌሎች የሰጡትን የማንነት ፍረጃ አሜን ብሎ ተቀብሎ የሚኖር ግለሰብ ነዉ (አዳም፣ 2001)፡፡ ስምዖን ሌሎች የሰጡትን “መልከ ጥፉ” የሚል ስያሜ አሜን ብሎ መቀበሉ ለከባድ የበታችነት ስሜት ህመም ዳርጎታል፡፡ አዳም ኦቾሎኒ በተሰኘዉ አጭር ትረካ ዉስጥ የሚከተለዉን ጽፏል፦
ዕድሜዬ አሥራ አራት እስኪደርስ በመልኬ እሰደብ ነበር (በኋላም ቀረልኝ ማለት ሳይሆን)፡፡ እኔም ተጨባጭ መረጃ ይዤ ከመከራከር ይልቅ የተባልኩትን በመስማት፣ ሰምቼም በማመን ዝቅተኛነት የወረረኝ፣ ‘አስቀያሚ’ የተባለ ፊቴን ሰዉ ፊት በኩራትና በራስ መተማመን ማሳየት የሚከብደኝ ነበርኩ)፡፡ የስነ ልቡና በሽታ በሉት ብትፈልጉ… ‘አስቀያሚ’ ተብዬ መሰየሜ የፈጠረብኝን አጥንቴ ድረስ የተጠለለዉን የዉርደት ስሜት፡፡ ፕሮፓጋንዳ የትኛዉ ጎረቤቴ ወይም የቤተሰቤ አባል አዉጥቶልኝ አምኜ ተከትዬዉ እኔን የወጣትነት ጨለማ ዉስጥ እንደከተተኝ አላዉቅም፡፡ የማዉቀዉ ማፈሬን ነዉ፡፡ አጨራረሱን ነዉ፡፡ ትዝ የሚለኝ ማፈሬ ነዉ፡፡ ዕድሜዬ ከፍ እያለ እንኳን ሲሔድ … በዚህም ወጣት ሴቶች ዐይን ስገባና ሲያተኩሩብኝ … አስቀየሚነቴ የሚያስገርማቸዉ … አስገርሟቸዉ የሚያፈጡብኝ ይመሰስለኝ ነበር (አዳም፣ 2001:ገጽ 261)፡፡ 
… መልክ፣ ቁመና ቀላል ነገር ተብሎ ይሰየማል እንጂ የሰዉ ሕሊና ላይ… ተስፈኛ መሆኑንና ተስፋ-አልባ መሆኑን እንደሚመጥን በእኔ በደረሰበት ሰዉ አዉቀዋለሁ፡፡ 
ግብዞች ግን ይላሉ፡
‘መልክ ታጥቦ አይጠጣ’
እኔም እመልሳለሁ፡
‘ይጨለጥ፣ እልም አድርጎ ይጨለጥ’
ግብዞች እንዲህ ይላሉ፡
‘ዋናዉ ቁም ነገር ነዉ’
‘ተባለ እንዴ? እዛ አገር ነበርኩ … ያልታደለ ዜጋ ሆኜ’ እላለሁ፡፡ የጎደለብኝ ሌላ ነገር አልነበረም፡፡ የጎደለኝ… ‘የጎደለህ…’ ተብዬ ያመንኩት… አምኜም በደም ሥሬ ያስገባሁት መልከ-ጥፉ መባሌ ያሳደረብኝ ገጣባ ስሜት ብቻ ነበረ (አዳም፣ 2001፡ገጽ 261-262)፡፡ 
   የሌሎችን ፍረጃ በይሁንታ መቀበል ራስን እንደ ቁስ አሳንሶ መመልከት ነዉ፡፡ በተጨባጭ ግን፣ የሰዉ ልጅ ማመን እስኪደንቅ ነገሮችን የመቀየር ሥልጣንን የተቀዳጄ አስደናቂ ፍጡር ነዉ፡፡
   የአዳም አንዱ ልኂቅ ሥራ (masterpiece) (የአማርኛ አቻዉ የአቶ ቴዎድሮስ ገብሬ ነዉ) መካከል አንዱ የሆነዉ ይወስዳል መንገድ ያመጣል መንገድ የአጫጭር ልብ ወለዶች መድብል ከላይ የዳሰስነዉ ሽግግር ሽሽት ተብሎ የሚጠራዉ የግብዝነት አይነት የተፈከረበት ሌላኛዉ ሥራ ነዉ፡፡ ፍልስፍናዉ የተዳሰሰዉ ቀዳዳ በተሰኘዉ አጭር ልብ ወለድ ዉስጥ ነዉ፡፡ ይህ ትረካ በአንደኛ መደብ የትረካ አኳያ የተተረከ ነዉ፡፡ እዚህ ትረካ ዉስጥ የተሳለችዉ ገጸባሕርይ ማርታ ተክለማርያም ንቃተ ኅሊናን የተጎናፀናፈች ነፃ ፍጡር መሆኗን በመካድ ራሷን ንቃተ ኅሊና እንደ ጎደላቸዉና ንጥረ ባሕርያቸዉ በወሳኛዊነት ሕግ እንደ ተደነገገ ግዑዝ ፍጡራን ቆጥራ ኃላፊነቷን ስትሸሽ እናገኛታለን (አዳም፣ 2003)፡፡ ይህ ጠባይ በግብዝነት ዉስጥ የመዉደቅ ምልክት ነዉ፡፡
   ማርታ አስመሮም ከተባለዉ የሕግ ባሏ ተሸሽጋ ደበበ ከተባለ የልጅነት ወዳጇ ጋር የምትማግጥ ገጸባሕርይ ናት (አዳም፣ 2003)፡፡ ማርታን ቤተሰቦቿ ለአስመሮም የዳሯትም ገና በኮረዳነት እድሜዋ ነበር፡ የማርታ ተድሮ መሄድ የእሷምን የደበበንም ልብ በሐዘን ሰብሯል፡፡
   ምንም እንኳ ማርታ በግብዝነት አማካኝነት የተጎናፀፈችዉን አርነት ለመሸሽ እንደ ስትራቴጂ ብትጠቀምበትም፣ ንቃተ ኅሊናን የተቸረች ፍጡር በመሆኗ ቤተሰቦቿም ሆነ ባሏ አስመሮም ያቀረበላትን የጋብቻ ጥያቄ ዉድቅ የማድረግም ሆነ የመቀበል ምርጫ ለእሷ ብቻ የተተወ ነበር፡፡ ደበበን ወይ አስመሮምን የመምረጥ ኃላፊነቱ የእሷ ብቻ ነበር፡፡ ከታሪኩ እንደምናነበዉ፣ እሷ ግን የትዳር ሕይወቷን በተመለከተ ‘ከደሙ ንፁህ ነኝ’ ብላ ራሷን በመሸንገል እንድታገባ የገፋፏትን ሰዎች ስትወነጅል እናገኛታለን (አዳም፣ 2003)፡፡ በተጨባጭ ግን፣ ማርታ የዉሳኔዎቿ ብቸኛ ባለ ዕዳ ናት፡፡

   ለሳትረ ግብዝነት ግድፈት (error) በመሆኑ ፈፅሞ ተቀባይነት የለዉም፡፡ ሳትረ እንደሚነግረን፣ ማርታ ወደ ህልዉና ስትመጣ የተጎናፀፈችዉንና በየትኛዉም መንገድ ልትሸሸዉ የማትችለዉን አርነት እና ኃላፊነት ለመሸሽ እቅድ በመንደፍ ፈንታ በሕይወቷ ለተከወኑ ነገሮች ሁሉ ሙሉ ኃላፊነቱን የምትወስድ ሐቀኛ ሴት ልትሆን ይገባል፡፡ ሐቀኝነት ፈፅሞ መሸሽ የማንችለዉን ነፃነታችንን እና ኃላፊነታችንን ሙሉ በሙሉ በመቀበል የሚገለፅ ጠባይ ነዉ፡፡ ይኸ አይነት ጠባይ ያለዉ ግለሰብ ለሁሉም ድርጊያዎቹ ዳፋ ሌሎች አካላት (ፈጣሪ፣ ማኅበረሰብ፣ ጂን … ወዘተ) ላይ ጣቱን ከመቀሰር ተቆጥቦ የእያንዳንዱ ዉሳኔዉ ባለ ዕዳ ራሱ ብቻ መሆኑን አምኖ ይቀበላል፡፡ 


   የሳትረ ሥነ ኑባሬ እንደሚያትተዉ፣ የሰዉ ልጅ ህልዉናዉ ከማንነቱ ወይም ተፈጥሮዉ ቀዳሚ በመሆኑ ዕጣ ፈንታዉን በራሱ እጅ የመጻፍ ሥልጣን አለዉ፡፡ በሌላ አነጋገር፣ የሰዉ ልጅ ያለ ረዳት የሚኖር ባይተዋር ፍጡር (abandoned) በመሆኑ አርነቱን ተጠቅሞ ራሱን የመፍጠር ሙሉ ኃላፊነቱ ጫንቃዉ ላይ የወደቀ ነዉ (ሳርተር፣ 2018)፡፡ በሳትረ ኤግዚስቴንሻሊዝም ዉስጥ አርነት እና ኃላፊነት የአንድ ሳንቲም ሁለት ገፅታዎች ናቸዉ፡፡ ባይተዋርነት በሳትረ ግብረ ገብ ዉስጥ የሚገኝ ዐቢይ ሴማም ነዉ፡፡ ይህ ሴማ የሳትረን ኢ-አማኝነት (atheism) የሚሰብክ ነዉ፡፡ ሳትረ ፈጣሪ (God) በህልዉና አለ ብሎ አያምንም፡፡ ፈጣሪ በህልዉና ባለመኖሩ ምክንያትም የሰዉ ልጅ እንዴት መኖር እንደሚገባዉ ፍፁማዊ (a priori) የግብረ ገብ ሕግጋትን የደነገገለት አካል የለም፡፡ በእዚህም የተነሳ፣ እያንዳንዱ ግለሰብ የራሱን የግብረ ገብ እሴት ፈጥሮ ሕይወቱን የመምራት ኃላፊነት አለበት፡፡ ሳትረ የፊዮዶር ዶስቶቭስኪን ንግግር ጠቅሶ እንደሚነግረን፣ ፈጣሪ በህልዉና ከሌለ ሁሉም ነገር የተፈቀደ ነዉ (ሳትረ፣ 2007)፡፡   
     እንደ ሳትረ (2018) እሳቤ፣ ቁሶች (being-in-itself) ተሟልተዉ የተፈጠሩ አካላት በመሆናቸዉ ዕድል ፈንታቸዉን በምርጫቸው የመቀየስ ኃይል የላቸውም፡፡ ጠረጴዛ ተሟልቶ የተፈጠረ ቁስ በመሆኑ ባለበት ፀንቶ ኗሪ ነው፡፡ ፈፅሞ በሥልጣኑ ራሱን መለወጥ አይችልም፡፡ የቁስ ተፈጥሮ ከህልዉናዉ ቀዳሚ ነዉ፡፡ በመሆኑም፣ ቁስ የሳቢያ እና ዉጤት ሕጎች (causal laws) ይተገበርበታል (ገቲንግ፣ 2001)፡፡ በተቃራኒዉ፣ የሰዉ ልጅ ከሳቢያ እና ዉጤት ሕግ እግር ብረት (causal determination) ነፃ ነዉ፡፡ ሰዉ ዕድል ፈንታዉን በተለመው መንገድ የመቀየስ ኃይል ያገኘዉ ልክ እንደ ቁስ ሙሉ ፍጡር ባለመሆኑ ነዉ (ዳግል፣ 2011፤ ፍሮንዲዚ፣ 1981)፡፡ 
   አለንጋና ምስር እና ሌሎች አጫጭር ታሪኮች በተሰኘዉ የአዳም የአጫጭር ልብ ወለዶች መድብል ዉስጥ የቀረበዉ ኦቾሎኒ የተሰኘዉ አጭር ትረካ ከላይ የተመለከትነዉ ፍልስፍናዊ ዐሳብ በጥልቀት የተዳሰሰበት ሥራ ነዉ፡፡ ኦቾሎኒ ዉስጥ የተሳለዉ ዋና ገጸባሕርይ ስምዖን የእኛ የሰዉ ልጆች ባሕርይ (our character traits) በሥልጣናችን እንድንሆን ከመሰነዉ ዉሳኔ ዉጭ አለመሆኑን ተገንዝቦ የቀደመ ማንነቱን በራሱ ኃይል ሲለዉጥ እናገኘዋለን፡፡ ስምዖን ሰዉ በመሆኑ የተጎናፀፈዉን ፍፁማዊ አርነቱን ተጠቅሞ ማንነቱን በአዲስ መልክ ከመፍጠሩ በፊት በልጅነቱ ዘመን ሰዎች መልከ ጥፉነቱን እየጠቀሱ መስደባቸዉ ከባድ የበታችነት ስሜት ፈጥሮበት ሕይወቱ ሐዘን ያጠለበት ነበር (አዳም፣ 2001)፡፡ 
   ስምዖን ኋላ ላይ ከላይ የነገረንን ተጣብቶት የኖረዉን የዝቅተኝነት ስሜት ሲኒማ ሊመለከት ከባልንጀሮቹ ጋር ፒያሳ ሲኒማ ኢትዮጵያ አቅንቶ ሳለ ሲኒማ ቤት ዉስጥ የተዋወቃት ልጃገረድ ሲታይ በነበረዉ ሲኒማ ዉስጥ የሚተዉነዉ ፈረንጅ ተዋናይ መልክ ከእሱ መልክ ጋር እንደሚመሳሰል ለእሱ እና ለወዳጆቹ በመጥቀሷ ምክንያት አሸንፎ ተቀባይነቱን ያረጋገጠባትን ‘ኦቾሎኒ’ ብሎ የሚጠራትን ሴት ለመጀመሪያ ጊዜ ለመተዋወቅ (ለመጥበስ) የቻለዉ በራሱ ሥልጣን ነዉ፡፡ ይህ ገጸባሕርይ ኋላ ላይ ከኦቾሎኒ በተጨማሪ ሌሎች ሴቶችን የሚያማግጥ ሴት አዉል (womanizer) ወደ መሆን እንደተሸጋገረም ከላይ በተጠቀሰዉ ትረካ ዉስጥ ይነግረናል፡፡ አዳም የሚከተለዉን ጽፏል፦ 
እና ግን እየቆየ በራስ መተማመኔ እያደገ ሌላ ሴት እንደሚፈልገኝ፣ እንደሚያየኝ ስረዳ ትሰለቸኝ ጀመር፡፡ በቀን በቀን ካላገኘሁሽ የምላት በመጀመሪያ ሁለት ቀን፣ በሚቀጥለዉ ጊዜ ሦስት ቀን እያለ ለሳምንትና ለወር የቀጠሮአችን ጊዜ መስፋት ጀመረ፡፡ የገባትም መሰለኝ፡፡ እኔ በተገኘዉ ክፍት ቦታ ሌሎች ሴቶችን ማማለል ወጣሁ፡፡ ብዙ ቀላቀልኩ፡፡ ቀድሞ ችላ የሚሉኝ የሚመስለኝን ደፈርኩ (አዳም፣ 2001፡ገጽ 270)፡፡  
… እዚያዉ አጠገብዋ ዉለታ-ቢስ ነዉ የሆንኩት፡፡ ብዙ አልተጓዝኩም፡፡ ጐንዋ ቆሜ እየዳበስኳት ነዉ የከዳኋት፡፡ ክፉ አልተናገረችኝም፡፡ አልተናገረችኝም ማለት አልገባትም ማለት አይደለም፡፡ እኔ ግን የገመትኩት እንደዚያ ነበር፡፡ ምን እንደነካኝ አላዉቅም፡፡ ሲያጋጥመዉ አፌ ደ’ሞ ሊያታልላት ይፈልጋል …
“ትወደኛለህ?” ስትለኝ፡፡
“ኦቾሎኒዬ አይደለሽ” እላታለሁ፡፡
እህቴ ባል አግብታ አሜሪካ ስትሄድ መሸኛ ፓርቲ ተደርጎ አልጠራኋትም፡፡ ያን ማታ የመጣችዉ ሌላ ከእስዋ የተሻለች የምትመስል ‘አራዳ’ ቢጤ ናት፡፡ (‘አንቺ ሰዉዬ ትለዋዉጪያለሽ’ ሲሉኝ እኮራ ነበር ሀሀሀሀ!!!) (አዳም፣ 2001፡ገጽ 271-272)፡፡
   እቴሜቴ ሎሚ ሽታ የተሰኘዉ የአዳም የአጫጭር ልብ ወለዶች መድበል ከላይ የዳሰስነዉ ፍፁማዊ አርነት ብለን የምንጠራዉ ፍልስፍናዊ ጽንሰ ዐሳብ የተፈከረበት ሌላኛዉ ሥራ ነዉ፡፡ እቴሜቴ ሎሚ ሽታ የተሰኘዉ አጭር ልብ ወለድ ይህ ፍልስፍናዊ ጭብጥ በጥልቀት የተዳሰሰበት የመድበሉ መጠሪያ ነዉ፡፡ እቴሜቴ ሎሚ ሽታ አጭር ልብ ወለድ ዉስጥ የተሳለችዉ ዋና ገጸባሕርይ ሎሚ ሽታ ግላዊ ምርጫዋን ተጠቅማ ሕይወቷን በአዲስ ጎደና የቀየሰች ሴት ናት፡፡ ደራሲዉ እዚህ ታሪክ ዉስጥ እንደሚነግረን፣ ይቺ ሴት ከሕግ ባሏ ታደሰ ጋር ትመራዉ የነበረዉ ሕይወት ድባቴ ያጠላበትና ሙሉ ደስታ ያልነበረዉ ሕይወት ነበር፡፡ ይህ የሆነዉ ደግሞ ባሏ ታደሰ ወሲባዊ አምሮቷን በምትፈልገዉ ልክ ሊያረካላት የሚችል ወንድ አለመሆኑ ነበር፡፡ አዳም የሚከተለዉን ጽፏል፦
ከላይ አያለሁ፡፡ በምሽት ሞተሩን አስነስቶ ሲከንፍ፡፡ ሦስተኛ ቀኑ ነዉ፡፡ እያስጮኸ ሞተር ሲያስነሳ፡፡ ለካስ የእኔ ሱስ ነበረበት፡፡ ደስ ይላል፡፡ የወደደን ራቅ አድርጎ ወደ ሌላ ወደ ወደደ መሸጋገር፡፡ እንዴት ነዉ ብልግና አይሆንም፡፡ ባል መለወጥ ይባላል፡፡ ለአፍታ እኔ ወደነበርኩበት ቀና ብሎ ያየ መሰለኝ፡፡ ያቺ ቀልቃላ ልጅ የት እንዳለሁ ነግራዉ ይሆናል፡፡ ደስ የሚሉ ዐይኖች ነበሩት፡፡ ታደሰ መልካም ዓይኖች ነበሩት፡፡ ልንተኛ ወይ ሊተኛ ሲል ሶፋዉ ዙሪያ እየተሽከረከረ ስራ ፈቶች የተበተቡትን ግጥም የሚባል ነገር ያነብልኝ ነበር፡፡ የሚያስፈራ፡፡ ገላልጦ እያሳየ የሚያስፈራ፡ ሴት ሳይሆኑ የሴትን ልብ እናዉቃለን የሚሉ ገጣሚዎች፡፡ አፍቃሪ መስዬ አሰቃይቼዋለሁ፡፡ ግን ደ’ሞ እኔ እንደ አንድ ግለሰብ የፈለግሁትን መምረጥ የመቻል መብት እንዳለኝ መዘንጋት የለበትም፡፡ ምን አንቀለቀለዉ ግን? ቢጋጭ ከሆነ ግንብ ጋር? ወይም አህያ ገጭቶ እንደ አህያ ቢሞትስ? ምን ሆንኩ ነዉ? መጀመሪያ አጠገቡ እያለሁ ወንድ መሆን ነበር፡፡ በሚያስፈልግበት ጊዜ ወንድ አይሆኑም፡፡ በእሷ ምክንያት ሞተ ለመባል ነዉ? ጤነኛዉን ሰዉዬ አሳበደችዉ እንዲባልለት ነዉ? በእኔ ላይ ሊያስፈርድ ነዉ? እሷ እንዲህ አድርጋዉ እንዲህ ሆነ ሊያሰኝ? የጠበቃ ተንኮል፡፡ ወይስ ገና ለገና ከዚህ ጉብታ ላይ አይቼዉ ‘እኔን! እኔን! እኔን!’ ብዬ ተንደርድሬ እንድመለስለት ነዉ? ልጅ አደረገኝ? አጠገባቸዉ ተጋድሞ ያልመተሩት ስጋ በጮሌ ድመት ሲወስድባቸዉ የሚነጫነጩ ስንት ዉሾች አሉ (አዳም፣ 2001፡ገጽ104)፡፡ 


አዳም ረታ : ኤግዚስቴንሻሊዝም እና አብዘርዲዝም
  ክፍል አንድ          



   ይህ ኂሳዊ መጣጥፍ ኤግዚስቴንሻሊዝም ተብሎ በሚጠራው በዠን-ፖል ሳትረ እና አብዘርዲዝም ተብሎ በሚጠራው በአልበርት ካሙ ፍልስፍና መነፅር የአዳም ረታ የልብ ወለድ ድርሰቶችን የሚፈክር ነው፡፡ የአዳም ረታ የድርሰት ሥራዎችን ከኤግዚስቴንሻሊዝም ፍልስፍና አንጻር በመፈከር ረገድ ይህ የእኔ ሥራ የመጀመሪያ አይደለም፤ ሌሎች ሰዎችም በዉጭ ሀገር ቋንቋ ተመሳሳይ ሥራ ሠርተዋል፡፡ ስማቸዉን ለመጥቀስ፡ ፀደይ ወንድሙ ዘ ኬዝ ኦፍ ኤግዚስተንስ ኢን ፍቅር እስከ መቃብር፣ ከአድማስ ባሻገር ኤንድ ግራጫ ቃጭሎች፡ ፍሮም ኤግዚስቴንሻሊስት ፐርስፔክቲቭ በሚል ርዕስ እ.አ.አ. 2007 ዓ.ም፣ አክሊሉ ደሳለኝ ኤግዚስቴንሻሊዝም ኢን ዘ ሴሌክትድ ክሬቲቭ ወርክስ ኦፍ አዳም ረታ በሚል ርዕስ እ.አ.አ. 2010 እና አዳም ረታ አዝ ኤ ሊትረሪ ኤግዚስቴንሻሊስት፡ ቴክስችዋል ኤንድ ዲስክሪፕቲቭ ክሪቲሲዝም በሚል ርዕስ እ.አ.አ. 2010 ዓ.ም፣ አረጋዊ ገ/ሚካኤል አን ኤግዚስቴንሻሊስት ሪዲንግ ኦፍ አዳም ረታስ ኖቭል መረቅ በሚል ርዕስ እ.አ.አ. 2017፡፡ ይህ ኂሳዊ መጣጥፍ ሙሉ በሙሉ ከላይ በጠቀስኳቸው አጥኝዎች ባልተዳሰሱ የአዳም ሥራዎች ላይ አትኩሮቱን ያደረገ ነዉ፡፡  
   አዳም ረታ ከሌሎች የሀገራችን ልብ ወለድ ደራሲያን በተለየ መልኩ የኤግዚስቴንሻሊዝም እና አብዘርዲዝም ፍልስፍና መሠረታዊ ሴማዎችን (themes) በጥልቀት የዳሰሰ ልብ ወለድ ደራሲ ነዉ፡፡ በመሆኑም፣ ደራሲዉን በልበ ሙሉነት ከኤግዚስቴንሻሊስት እና አብዘርዲሰት ልብ ወለድ ደራሲያን ጎራ መፈረጅ ይቻላል፡፡ 
  አዳም ረታ በኢትዮጵያ ሥነጽሑፍ ላይ ጉልህ ተፅዕኖ የፈጠረ፣ በሕይወት ከሚገኙ የዓለማችን ታላላቅ ልብ ወለድ ደራሲያን መካከል አንዱ ሆኖ መጠራት የሚችል ደራሲ ነዉ፡፡ ደራሲዉ ለአራት አሥርት ዓመታት በዘለቀ የሥራ ዘመኑ በግሉ አራት ረጅም ልብ ወለዶችን ግራጫ ቃጭሎች (1997)፣ መረቅ (2007)፣ የስንብት ቀለማት (2008) እና አፍ (2010) እና ስድስት የአጫጭር ልብ ወለድ መድበሎችን ማሕሌት (1981)፣ አለንጋና ምስር እና ሌሎች አጫጭር ታሪኮች (2001)፣ እቴሜቴ ሎሚ ሽታ (2001)፣ ከሰማይ የወረደ ፍርፍር እና ሌሎች አጫጭር ልብወለዶች (2002)፣ ይወስዳል መንገድ ያመጣል መንገድ (2003)፣ ሕማማትና በገና እና ሌሎች አጫጭር ታሪኮች (2004) ለህትመት አብቅቷል፡፡ ከሌሎች እዉቅ ልብ ወለድ ጸሐፍት ጋር ደግሞ አባ ደፋር እና ሌሎች አጫጭር ታሪኮች (1977)፣ ጭጋግና ጠል እና ሌሎች (1990)፣ አማሌሌ እና ሌሎችም (2009) እና አዲስ አበባ ኖይር (2012) የተሰኙ የአጫጭር ልብ ወለድ መድበሎችን ለህትመት አብቅቷል፡፡
   አዳም ረታ በእኛ ሀገረ ልብ ወለድ ጠጠር ያለ ቁም ነገርና ፍልስፍናዊ ሐቲት በኪን ተኩሎ የሚቀርብበት ኪናዊ ድርሳን መሆኑን በገሀድ ካሳዩ የዘመናችን ጎምቱ ልብ ወለድ ደራሲያን መካከል አንዱ ነዉ፡፡ ደራሲዉ በሀገሪቱ ሥነጽሑፍ እድገትም የአንበሳዉን ሚና ተጫዉቷል፡፡
   ከላይ በመግቢያዬ እንደ ጠቀስኩት አዳም ረታ በፈጠራ ሥራዎቹ ዉስጥ በርካታ የኤግዚስቴንሻሊዝም እና አብዘርዲዝም ፍልስፍና ጽንሰ ዐሳቦችን በጥልቀት ዳስሷል፡፡ ደራሲዉ የኤግዚስቴንሻሊዝም እና የአብርዲዝም ፍልስፍና ዐቢይ ሴማዎችን የዳሰሰባቸዉ የልብ ወለድ ድርሰቶቹ አለንጋና ምስር እና ሌሎች አጫጭር ታሪኮች፣ ይወስዳል መንገድ ያመጣል መንገድ፣ እቴሜቴ ሎሚ ሽታ እና ከሰማይ የወረደ ፍርፍር እና ሌሎች አጫጭር ልብወለዶች ሲሆኑ በእነዚህ ሥራዎች ዉስጥ የተዳሰሱት ሴማዎች ደግሞ ፍፁማዊ አርነት (radical freedom)፣ ኃላፊነት (responsibility)፣ ጭንቀት (anguish)፣ ግብዝነት (bad faith)፣ ሐቀኝነት (authenticity)፣ ባይተዋርነት (abandonment) እና ወለፈንድ (absurdity) ናቸዉ፡፡ እነዚህ ሴማዎች በጥብቅ የተዛነቁ ናቸዉ፡፡ 
የኤግዚስቴንሻሊዝም እና የአብዘርዲዝም ሴማዎች በአዳም ረታ ድርሰቶች ዉስጥ
              ፩. ፍፁማዊ አርነት
   ፍፁማዊ አርነት በሳትረ ኤግዚስቴንሻሊዝም ዉስጥ ትልቅ ሥፋራ የሚሰጠዉ ጽንሰ ዐሳብ ነዉ፡፡ ከሃያኛዉ ክፍለ ዘመን ታላላቅ የምዕራቡ ዓለም ፈላስፎች መካከል አንዱ የሆነዉ ሳትረም ከሁሉም የዓለማችን ፈላስፎች በላቀ ስለ ሰዉ ልጅ አርነት የተፈላሰፈ ፈላስፋ ነዉ፡፡ ለእሱ በሰዉ ልጅ ሕይወት ዉስጥ እጅግ የላቀ ዋጋ ያለዉ ነገር አርነት ነዉ (ሄርስችፊልድ፣ 1968)፡፡ በሳትረ ፍልስፍና ዉስጥ አፅንዖት የሚሰጠዉ የአርነት አይነት ተጨባጭ አርነት (practical freedom) ነዉ፡፡ ይህ አይነቱ አርነት ከሥነ ኑባሬያዊ አርነት (ontological freedom) የተለየና ገደብ (limit) ያለዉ ነዉ፡፡
   አርነት የሳትረ የሥነ ኑባሬ ነባቢ አእምሮ (ontological theory) የማዕዘን ድንጋይ ነዉ፡፡ ይህ አርነት ፈፅሞ ሊሸሹት የማይችሉት የሰዉ ልጅ መገለጫ ባሕርይ (unescapable characteristics) ነዉ፡፡ ለሳትረ፣ ሰዉ መሆን ማለት ነፃ መሆን ማለት ነዉ፡፡ እንደ ሳትረ እሳቤ፣ አርነት የሚገደበዉ በራሱ በአርነት ብቻ ነዉ፡፡ በመሆኑም፣ የሰዉ ልጅ ከአርነት ቀንበር ነፃ መዉጣት አይችልም – ነፃ እንዲሆን ተረግሟልና፡፡  
   የሳትረ ሥነ ኑባሬ ነባቢ አእምሮ መነሻ ህልዉና (existence) የንጥረ ባሕርይ (essence) ወይም ማንነት ቀዳሚ ነዉ (existence precedes essence) የሚለዉ መፈክር ነዉ፡፡ ሳትረ የሰዉ ልጅ ህልዉና ከማንነቱ ቀዳሚ ነዉ የሚለዉን የሥነ ኑባሬ አስተምህሮቱን የገነባዉ ፈጣሪ በህልዉና የለም ብሎ ስለሚያምን ነዉ፡፡ እንደ እሱ እሳቤ፣ ፈጣሪ በህልዉና ባለመኖሩ ምክንያት፣ የሰዉ ልጅ እንደ ግዑዛን ፍጥረታት ቀድሞ የተሠራ ንጥረ ባሕርይ ወይም ተፈጥሮ የለዉም፡፡ የሰዉ ተፈጥሮ የሰዉ ልጅ ወደ መኖር ከመጣ በኋላ በራሱ ትልም መሠረት የሚሠራ ነዉ (ሳትረ፣ 2007)፡፡
   እንደ ሳትረ (2007) እሳቤ፣ የሰዉ ልጅ ንጥረ ባሕርይ ወይም ማንነት ከህልዉናዉ ቀዳሚ ነዉ (essence precedes existence) የሚለዉ የኢማኑኤል ካንት እሳቤ የተሳሳተ አተያይ ነዉ፡፡ በመሆኑም፣ ይህን አተያይ አበክሮ ይቃረናል፡፡ የካንት እሳቤ የንጥረ ባሕርይን (essentialism) ዲበአካላዊ አስተምህሮ የሚሰብክ ነዉ፡፡ የንጥረ ባሕርይ አስተምህሮ ወሳኛዊነትን የሚሰብክ በመሆኑ ለአርነት ቦታ የለዉም፡፡ ሳትረ ከካንት በተቃራኒ፣ የሰዉ ልጅ ወደ ህልዉና ከተወረወረ በኋላ ማንነቱን እንደ አናጺ በትልሙ (projection) መሠረት የሚያንጽ ነፃ ፍጡር (subjectivity) እንጅ ልክ እንደ ዕደ ጥበባት እንደ ቢለዋ፣ ብዕር ወይም የእጅ ሰዓት ቋሚ ተፈጥሮን ይዞ ወደ ህልዉና የመጣ ፍጡር አይደለም ይለናል፡፡ ለሳትረ፣ የሰዉ ልጅ ወደ መኖር መጥቶ ማንነቱን ከመፍጠሩ በፊት ምንም (nothing/empity) ነበር፡፡  




ገላጋይ መስሎ አጥቂ
( ሰሎሞን ደሬሳ )


የተነጠፈልሽ እንድትረጋግጪው
አንች ልጅነቱን ጨክነሽ የቀጨሽው፤
በጨረቃ ብርሃን ጥርሶችሽን ሲቆጥር
በትምህርት ጊዜው አንቺን ሲያሰላስል
እየታየው የከንፈሮችሽ ውበት
ተቃጥሎ በጥርሶችሽ ንጣት
እያጥወለወለው ያይኖችሽ ጥራት ጥልቀት።
ታገኝዋለሽ ዘመን ሲገልጥለት
ዞር ብሎ ሲያይሽ አምስት አመት አልፎ
ያላዋቂ ፍቅሩ በማወቅ ተገፎ
ትዝታ ለውጦት መልክሽን ሲረሳው።


"ኢሾ ኢሾ ያአቦኮ
ቶርቶራዳ? ለፋ ፉቴ
ኢሾ ኢሾ
"


1962 ዓ.ም
📚 ልጅነት (መድብል)📚


@AdamuReta
@isrik


ቀንዳም ኑሮን በቀልድ ቀንበር
  ━━━━ ✦ ━━━━
✍ ዓለማየሁ ገላጋይ
'
ጎረቤቶቼ አብዛኛው እድሜያቸውን በትዳር ያሳለፉ አዛውንቶች ናቸው። ሰውየው 71፣ ሴቲቱ 68 ዓመታቸው ነው። እንደሚባለው ከሆነ አርባ ሁለት ዓመታት ያስቆጠረ የፍቅር አብሮነት አላቸው።

ሰሞኑን ከእነርሱ የትዳር ዘመን ጋር እኩል እድሜ የነበረው መኖሪያ ቤታቸው እንደሚፈርስ ተነገራቸው። በልዋጩም ኮንደሚኒየም ይሰጣችኋል ተባሉና 'ፕሮሰስ' ጀመሩ። ከ'ፕሮሰሱ' አንዱ ህጋዊ የጋብቻ ወረቀት ማውጣት ነው።

መንግሥት የካደባቸውን አርባ ሁለት ዓመት በልቦናቸው ይዘው በአጃቢ ወደ ጋብቻ አስፈፃሚ ድርጅት ሄዱ።

ሴትየዋ ፀጉራቸውን ተተኩሰዋል። በሀበሻ ልብስ ተሽሞንሙነው ከየጎረቤቱ በተጠረቃቀመ ጌጣ-ጌጥ ተንቆጥቁጠዋል። ሰውየውም ከወትሮው ለየት ያለ ሙሉ ልብስ ከነቄንጠኛ ባርኔጣው አድርገዋል።

ጋብቻ አስፈፃሚው ሹም ፊት ቀርበው ተፈራረሙ። ወደ ፎቶ መነሻው ክፍል ሲያመሩ ሞቅ ባለ የሙሽራ ዘፈን አጀብናቸው፦
"አይዞሽ ሙሽሪት አይበልሽ ከፋ
ሁሉም ያገባል በየወረፋ"

በዚህ መካከል አንድ ጓደኛዬ ወደ እኔ ጠጋ ብሎ፦

"ኧረ እኚህን ሴትዮ አንድ በላቸው" አለኝ።

"ማንን?" አልኩት

"ሙሽሪቷን"

"ምን አደረጉ?"

"እያለቀሱ ነው"

"ምን ሆነው?"

"ይህንን ወጌን እናቴ ሳታይ ሞተች እያሉ"

'ወግ ነው ለኮንዶሚኒየም ሲዳሩ ማልቀስ' እንበል ይሆን?
😂 😂 😂
━━━━━━━━━
📔 ኢህአዴግን እከሳለሁ!
🗓 ነሐሴ 2004 ዓ.ም.
📄 79 - 80
📖 📖 📖 📖 📖


@AdamuReta
@isrik


የፍቅር ቀን ወይም የአደይ ቀን

Reposted


"…እያንዳንዱን ኢትዮጵያዊ የፍቅር ጀግና ለማድረግ በአገራችን ቫለንታይንስ ደይ እየተባለ የሚከበረውን የፈረንጆች በዓል ተውሰን እንደ አገራችን ፀባይ ለማክበር እቅድ አውጥተን ነበር፡፡

የጦር ጀግኖች ብቻ ሳይሆን የፍቅር ጀግኖች ያስፈልጉናል፡፡

ቫለንታይን ጥሩ ሃሳብ ነው፡፡ ክፋት የለበትም፡፡ ተቃቅፈው የሚሄዱ ፍቅረኞች ማየት ደስ ይላል፡፡ እጅ ለእጅ ተያይዘው በመንገድ የሚሄዱ ወጣቶች ትዕይንት የሚናፍቅ ነው፡፡ እኔ ወጣት በነበርኩበት ዘመን እንዲህ ማድረግ ያሳፍረን ነበር፡፡ ልጆቻችን በፍቅር እንዲያፍሩ አልፈልግም፡፡ ፍቅርን ከብልግና አምታተናል፡፡

ይሄን ቫለንታይን ቀን በዓል ኢትዮጵያዊ ለማድረግ ሦስት ነገሮች ማሟላት አስበን ነበር፡፡

አንደኛ ከየትኛውም የአገራችን ክፍል አስገራሚ የፍቅር ታሪኮችን መሰብሰብና ለብሔራዊ በዓል የሚያገለግለንን ነቅሰን ማውጣት፤

ሁለተኛ ምሳሌ የሚሆኑንን የአበባ አይነትና የአበባ ቀለም መምረጥ፤

ሦስተኛ በታዋቂ ገጣሚ፤ ሙዚቀኛና ኮርዮግራፈር በአሉን የሚዘክር በቀላሉ አድማጭ ሊያንጎራጉረው የሚችል ዜማ መስራት ነበሩ፡፡

ከነዚህ ውስጥ ኮሚቴው ለብቻው የሚወስናቸው የበዓሉን ቀን፣ የአበባው ዓይነትና የአበባ ቀለም ሲሆኑ፣ የተቀሩት ዐላማዎች ግን በጥናትና በህብረት ውሳኔ ይፀድቃሉ፡፡

አገራችንን ከአደይ የበለጠ ምን አይነት አበባ ሊወክላት ይችላል?

ከመስከረም ወር የበለጠ ምን የሚያምር ወር አለ?

ቢጫ ቀለምስ ውብ አይደለም?

የአገራችን ስም ከተሰራባቸው ቀለማት አንዱ ዮጵ ትርጓሜው ቢጫ ወርቅ ማለት ነው፡፡

ቢጫ የፀሐይ ብርሃን ነው፡፡ ፀሐይ ከሌለ ሕይወት የለም፡፡ እንደ ፍቅረኞች ፊት የምታበራው ፀሐይ አይደለችም? የተፋቀሩ ሁሉ እየተንቦገቦጉ አይደለ የሚውሉትና የሚያድሩት?

በዚህ ዕለት በአገራችን ያልተለመደ ስርዓት ለማምጣት ሀሳብ አለን፡፡

በዛን በፍቅር ቀን ወይም በአደይ ቀን (ስሙንም በሕብረት እንወስናለን ብለን ነበር) መሳሳም እንዲፈቀድ ከሃይማኖት መሪዎች ከሕግ አዋቂዎች ከወጣቶች ጋር የመነጋገር ሃሳብ ነበረን፡፡ ፍቅረኞች በመንገድ ላይ እዚህ አገር ሲሳሳሙ ታይተዋል? በዛን ቀን መሳሳም አሳፋሪ አይሆንም፡፡

ዓላማችን ወሩ መስከረም ሲሆን ቀኑ በመስከረም አንድ እና በመስከረም ሰባት መሃል ይሆናል፡፡ በዚያን ቀን ቢጫ ቀለም ያለው ልብስ መልበስና ቢጫ አበባ መያዝ ደንብ እናስደርጋለን፡፡ ቢጫው የተለያየ ቢጫ ሊሆን ይችላል፡፡ በበዓሉ ምሽት ቢጫ ርችቶች በሰፈሮቻችን የምሽት ሰማይ ላይ ይፈካሉ፡፡

ፍቅርን ማክበር ብልግና የለውም፡፡ ፍቅረኞች ቢሳሳሙ ብልግና የለውም፡፡ እየሆነና እየተደረገ መደባበቅ ጨዋ አያደርግም፡፡

በአደባባይ ሰዎች የተጋደሉባቸው ከተሞቻችን መፋቀርን የሚያሳዩ ምልክቶችን ለምን አሳፋሪ እንዳደረጉት አይገባኝም፡፡

ቦንብ ይዘው በሚንጎራደዱበት ከተማ ምናለ አደይ ይዘው ቢተቃቀፉ?

ለምን የፍቅር ዘፈን ሌላ ሰው ሲዘፍንልን ብቻ እንሰማለን? ለምን እኛ ድርጊቱ ውስጥ በአደባባይ አናወጣውም? ላፈቀረን ለፍቅረኛችን ዘፈን ከምንመርጥለት ለምን ባንችልበትም ራሳችን አናንጎራጉርለትም? ያፈቀርነውንስ ይዘን በአደባባይ ለምን ይሄው እዩን አንልም?

ጥላቻን ሳናፍር ያሳየን መውደድ ለምን ያሳፍረናል?"



📖 የስንብት ቀለማት፤ ገፅ 812

@AdamuReta
@isrik




ልቡ የለመለመ ሰው ለምለም ይወጣለታል::

ልቡ የደረቀ አገር ላይ ግራሩ ይደርቃል::

ቅንነት ካለህ ደረቅ እንጨት መሬት ብትከት ውሀ ባታጠጣውም ይፀድቃል::

🍃🍂 አዳም ረታ




"ማዳን ባልችል እንኳ ልሰውራቸው" (የአለማየሁ ገላጋይ ጣልቃ ገብነት)

* አንድ ደራሲ ለፈጠራቸው ገፀባሕርያት ታማኝ መሆን አለበት። የእሱ ድርሻ መሆን ያለበት ገፀባህርያቱን እና አለማቸውን መፍጠር ብቻ ነው።
ከዛም በፈጠረላቸው አለም ውስጥ እንደፍጥርጥራቸው እንዲኖሩ መልቀቅ።
የስነመለኮት ሊቃውንት "deistic theory" (deism) እንደሚሉት። ወይም ሰዓት ሰሪው እግዚአብሔር እንደሚሉት። ይህ "ism" በአጭሩ ሲብራራ እንዲህ ነው፦ (አንድ ሰአት ሰሪ ሰአቱን ሰርቶ ሲያበቃ ሰአቱ ካለሰሪው ጣልቃ ገብነት እንደሚሰራ፤ እግዚአብሄርም አለምን ፈጥሮ ጣልቃ ላለመግባት ወደ ሩቅ ቦታ ሄዷል ይላሉ።)
እንደ አማኝ በዚህ theory ባንስማማም፥ ደራሲ ግን እንዲህ ቢሆን ይመረጣል። ገፀባህርያቱንና አለማቸውን ከፈጠረ በኋላ ህይወታቸውን እንዲኖሩ ሊለቃቸው ይገባል።

* ካልተሳሳትኩ ብርሃኑ ዘርይሁን ይመስለኛል፦ "እከሌ የተባለው ገፀባህርይ ያሳዝነኛል ግን ምን ማድረግ ይቻላል የሱ ነገር... " እንዳለው። በቃ ማዘን ካለበት ይዘን! መሞት ካለበት ይሙት! ቁርጡን አውቆ እውነትን መጋፈጥ ካለበት ይጋፈጥ....

*አለማየሁ ገላጋይ ግን ከቃለመጠይቆቹ እንደተረዳሁት ለሰው ልጆች የሆነ አንዳች ተቆርቋሪነት እና ርህራሄ ያለው ሰው ነው። ጥሩ ነው! በገፀባህርያቱ ህይወት ጣልቃ እስካልገባ ድረስ ጥሩ ነው። አሌክስ ግን ይህን ማድረግ ያቃተው ይመስለኛል። በጣም በተደጋጋሚ ጣልቃ ሲገባ አስተውያለሁ።

* ገፀባሕርያቱ የሚያልፉበትን መከራ ለመመልከት ልቡ አልችል ሲለው "ባላድናቸው እንኳን ራቅ ወዳለ ቦታ ወስጄ ልሰውራቸው" የሚል ይመስላል። ይሄን ጣልቃ ገብነቱን እስቲ በወፍ በረር እንመልከት።
- የንፁህ እናት
- የመክብብ አባት (ባለ ፕሪስሊው)
- ረቂቅ
- ሻምበል ጠናጋሻው
- ማናሉ (የጋንጩር እህት)
- ናፍቆት
- ኩንዬ
- ሲፈን
- ጅምር ደራሲው ፋሲል.....
እነዚህ ሰዎች አረረም መረረም ኑሯቸውን እየኖሩ ነው። ህይወት ፊቷን ብታዞርባቸውም! ቢያዝኑም! ቢከፉም! ከመከራ ሊታደጋቸው ያልቻለው አለማየሁ ገላጋይ ምን አደረገ? አጠፋቸው(ሰወራቸው) ሃዘናቸው መቋቋም ሲያቅተው በሰበብ ባስባቡ እያመሃኘ ሰወራቸው።

1ኛ- ፕሪስሊው(የመክብብ አባት)፦ ከሚስቱ ጋር ያለውን ግንኙነት ስናይ " የወንድ አልጫ" ነው ማለታችን አይቀርም። ቀና ብሎ በሙሉ አይኑ እንኳ እሷን ማየት አይችልም! ይሽቆጠቆጣል! ከአይኗ ግርፊያ ለማምለጥ የሚገባበት ያጣል! የገዛ ልጁ እንኳ ታዝቦት " ከጫካ አጥምዳ ያላመደችው የዱር እንስሳ ይመስለኛል" ይላል። ግን ለምን አልጫ ሆነ? ጀግና የወንድ ቁንጮ እንደሆነ እርግጥ ነው። የሰፈሩን ወንድ ሁሉ አንዱን በቴስታ አንዱን በቡጢ ዘርሮ ቤቱን ያስከበረ ወንድ ነው። እሷጋ ሲደርስ ግን ልፍስፍስ ብሎ ቁጭ። ለምን? ሊያጣት አይሻም! ከሚያጣት በሷ ተጨቁኖ መኖርን መርጧል። የሚወደውን ጊታሩን እንኳን ስለሷ መስዋእት አድርጓል። በዚህ ስቃይ ውስጥ ሊተወው ያልወደደው አለማየሁ ሰወረው። በቃ እንደወጣ ቀረ።

2ኛ- ናፍቆት፦ ያቺ ወንዳወንድ ጎረመሰች። ጡቶቿ ጉች ጉች! ከወንዶች ጋር ቡጢ መቃመሱን ትታ ከንፈር መቃመስ ለመደች😁 ጉርምስና ክፉ ነው። ልቧን አሸፈተው እልም ብላ ጠፋች።

3ኛ- ኩንዬ፦ የቤቱ ድባብ አስጨናቂ ነው። በለጋ እድሜዋ የወደቀባት በሽተኛ የማስታመም ሃላፊነት መጨረሻ አልባ ሆነባት። ከዚህ ስቃይ መገላገል የምትችለው ስትሞት ወይ ስትጠፋ ነው። አሌክስ እንድትጠፋ አደረገ ። እሱ መጨከን አይችልማ!

4ኛ- ሲፈን፦ የታለ ብዜን ሚስት መሆን ነው ህልሟ። የታለ ብዜን ውቃቢ ካዳሚ መሆን ነው የህይወት ግቧና ክብሯ። ምን ዋጋ አለው አልተሳካም። እሷ ግን የታለን ግዴለሽነትና ቸልተኝነት ተቀብሎ እየታመሙ መኖሩ ተስማምቷት ነበር። ዳር ሆኖ የተመለከተው አለማየሁ ግን አዘነላት። እሷም ጠፋች።

5ኛ- የንፁህ እናት፦ ባልን በሞት ማጣት ስብራት ነው። አማት ቤት ለመኖር መገደድ ደሞ ይብሳል። የእለት ጉርስን ከአማቶች በድርጎ መልክ መቀበል ከሞት ይከፋል። ስሜትን የሚያጋሩት የራስ ሰው ማጣት ስቃይ ነው። ምን ታድርግ? እየታመመች ትኑር? አዎ ትችላለች መታመሙን ብቻ ሳይሆን እንባዋንም መሰወርም ለምዳለች። አሌክስ ግን አልቻለም። ሰወራት። ጠፋች።

6ኛ- ማናሉ፦ ድምፀ መልካሟ! ብርቱ ሃዘን ባይደርስባትም ፕሪስሊው ከሌለ የሸካራ ፀጉሯን ድምፅ እንጂ ውብ ቅላፄዋን ከማን ጋር ትቀልፃለች። በዛላይ እሱ የታመመው ህመም ጎድቷታል። እልም ብላ ጠፋች።

7ኛ- ጅምር ደራሲው ፋሲል፦ መንክርን መጋፈጥ ይቻላል? አይቻልም! በአንዲት ቁራጭ ደብዳቤ ተሰናብቶ ጥፍት!

8ኛ ሻምበል ጠናጋሻው፦ ህመሙን መዘርዘርም አይቻል። ተሰቃየ። መሄጃ ቢያጣ "ለሃገሩ ሊዋጋ" ዘመተ!

9ኛ- ረቂቅ፦ ረቂቅስ ትሙትና ትገላገል? በምን በደሏ? በናፍቆት ትታመም? ምንቦጣት? አዛኙ አለማየሁ ጣልቃ ገባ። ደራሲ ባለስልጣን አይደል? እንደ አማልክቱ ያሻውን ማድረግ ይችል የለ? እንደ ስሟ ወደ ረቂቅነት ለወጣት። ከእግሯ ጀምራ እየተሰወረች እየተሰወረች.....በቃ ስውር።

kal ©Bekalu Girma


ዘመዴን ስስመው
( ደበበ ሰይፉ )


ዘመዴን ስስመው
ጉንጬ ቢሻክረው
እኔንም ሻከረኝ
ዕድሜ መለስለሱ ፥ ማብቃቱ ታወቀኝ።


1966

@AdamuReta
@isrik




ለመሆኑ የአዳም ልጨኛ ስራው የቱ ነው?

በሙዚቃና በፊልም ምሳሌ ልጥቀስ፦ የማይክል ጃክሰን ሙዚቃዎች ከነቪዲዮ ክሊፓቸው ሁሉም ምርጥ ናቸው—አንዱን ከአንዱ ማበላለጥ አይቻልም፦ thriller, beat it, dangerous, black or white, earth song, you rock my world, bad ወዘተ

የክሪስቶፈር ኖላን ፊልሞችም ሁሉም እኩል ተወዳጆች ናቸው—Memento, The Prestige, Insomnia, Interstellar, Inception, Dunkirk, Oppenheimer. በእርግጥ TENET የተሰኘ ፊልሙ ምንም ነው ያልገባኝ።🤣🤣

የአዳም ረታ ብርቱ አንባቢዎች ዘንድ አራት የተለያዩ ስራዎቹን እንደየ አንባቢው ዝንባሌ የደራሲው ታላቁ ስራ ተደርገው ይቆጠራሉ። እነሱም

ግራጫ ቃጭሎች
ይወስዳል መንገድ፣ ያመጣል መንገድ
መረቅ እና
የስንብት ቀለማት ናቸው።

እኔ መረቅንና የስንብት ቀለማትን ስላላነበብኳቸው፣ ለእኔ የአዳም ማስተርፒስ ግራጫ ቃጭሎች ነው። በነገራችችን ላይ ይሄ ድምጽ መደብሰቢያ poll አይደለም። የትኛው ልብወለድ በድምጽ ብልጫ አሸናፊ መሆኑን ማወቅ ጥቅም የለውም። ጥቅም ያለው ከነዚህ አራት መጻሕፍት/ከአስሩም ሊሆን ይችላል አንዱን የመረጣችሁበት ምክንያት ነው።

እኔ ልጀምር



በመጀመሪያ ግራጫ ቃጭሎችን የሚመስል ልብወለድ ከአሁን በፊት አልተጻፈም ወደፊትም አይጻፍም። አዳም የራሱ የሆነ ወጥ/ኦሪጅናል ስልት አለው።

❷❷

አዳም ጋር ሌላው ሁሌም የምደነቅነት ኳሊቲው፣ ማንም ንቆ የሚተዋቸውን ጥቃቅን ጉዳዮች በሰነጽሁፍ መነጽር አጉልቶ፣ በስነጽሁፍ ለዛ አስውቦ የሚያቀርብበት ጥበቡ ነው።

Small things matter.
Actually, they are the only size that matters.
ትለናለች አሩንዳቲ ሮይ።

ይህንን መንገድ መከተል የጀመረው ደግሞ በግራጫ ቃጭሎች ነው። በዚህ ልብወለድ አዳም ለአማርኛ ስነጽሁፍ ትልቅ ልጅ ነው ከምናቡ አፍልቆ ያዋለደው።

❸❸❸

ቋንቋ ለደራሲ መሳሪያው ነው ካልን አዳም የቋንቋ ኒውክሌር የታጠቀ ደራሲ ነው።

በነዚህ ምክንያቶች ግራጫ ቃጭሎች ልጨኛ የአዳም ልብወለዴ ነው። እስኪ የእናንተንም ንገሩነ፦ የመጽሀፍ ዝርዝር ሳይሆን ከምርጫችሁ ጀርባ ያለውን ስነጽሁፋዊ ምክንያት። እንደዚህ ስንወያይ ነው እርስሸእርስ የምንማማረው!!

ደግሞም ከእኛ ከአንባቢዎቹ ባሻገር አዳም ረታ ራሱ ትልቁ ስራዬ ይሄ ነው ብሎ የሚጠቅሰው የትኛውን የልብወለድ መጽሐፉን ነው? ለምን? ምርጫውንና ምክንያቱን ሊነግረን ፈቃደኛ ከሆነ ይኸው እዚህ Adam Retaን ታግ አድርጌዋለሁ።

© Te Di




DAILY THOUGHTS (የዕለተ ዕለት ሀሳቦች) dan repost
በመንፈስም በስጋም ግባችን መሰናበት ነው ። ሞትን ነው የምንኖረው ወይም እየኖርን ነው የምንሞተው ። ግን ሁልጊዜ አለን ። ብንሞትም እንኩዋን አለን ። እያለን ደሞ ስለምንለወጥ የለንም ። በዚህ ምክንያት ደስታችንና ሃዘናችን ጊዜያዊ ነው ።

(የስንብት ቀለማት )






Alex Olompia - Zelalem Zelalem

አሌክስ ኦሎምፒያ
ዘላለም ዘላለም

"ምን ያለው አሞራ ከዛፍ ይሟገታል
ከወደደው ጋራ ማን ሲኖር አይቶታል

.....

አመመኝ ፍቅርሽ አደከመኝ . . ."
🖤



@AdamuReta
@isrik

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.