የትራምፕ አጋሮች ዜለንስኪ አካሄዳቸውን እንዲቀይሩ ወይም ስልጣን እንዲለቁ ግፊት እያደረጉ መሆኑ ተነገረ
ከዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጋር ቅርርብ ያላቸዉ ከፍተኛ የሪፐብሊካን ባለስልጣናት የዩክሬኑን ፕሬዝዳንት ቮልዲሚር ዘለንስኪን ከሩሲያ ጋር በሚያደርጉት ጦርነት ላይ ያላቸውን አቋም እንዲቀይሩ ወይም ወደ ስልጣን እንዲለቁ በመገፋፋታቸዉ ባለፈው ሳምንት አወዛጋቢው የዋይት ሀውስ ስብሰባ በዩክሬን መሪ ላይ ጫና ፈጥሯል።
የአውሮፓ መሪዎች እሁድ እለት በለንደን በተካሄደው ስብሰባ ላይ ለዘለንስኪ አጋርነታቸዉን ያሳዩ ሲሆን የብሪታኒያ ጠቅላይ ሚኒስትር ኬይር ስታርመር አጋሮቻቸው የመከላከያ ጥረታቸውን እንዲያጠናክሩ አሳስበዋል፡፡ ትራምፕ እና ምክትል ፕሬዝዳንት ጄዲ ቫንስ በሞላላዉ የዋይት ሀዉስ ጽህፈት ቤታቸዉ ውስጥ ከዘሌንስኪ ጋር ከተጋጩ በኋላ የታቀደዉን የማዕድን ውል ሳይፈርሙ ቀደም ብሎ እንዲሄድ ምክንያት ሆኗል፡፡
ዘሌንስኪ በስብሰባው ላይ የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲንን እ.ኤ.አ. በ 2019 የተኩስ አቁም ስምምነትን አላከበሩም እና ገዳይ እና አሸባሪ ናቸዉ ሲሉ ተከራክረዋል ።የትራምፕ የብሄራዊ ደህንነት አማካሪ ማይክ ዋልትዝ ዘለንስኪ ጦርነቱን ለማቆም ለመደራደር ዝግጁ መሆናቸዉን ለዋሽንግተን አስተዳደር ግልፅ አይደለም ብለዋል። ዋልትዝ የትራምፕን ግብ በሞስኮ እና በኪየቭ መካከል የግዛት ስምምነትን በማካተት በአውሮፓ የሚመራ የደህንነት ዋስትናን በመተካት ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን አጽንኦት ሰጥተዋል።
ትራምፕ ዘለንስኪ ከስልጣን እንዲለቁ ይፈልጉ እንደሆነ የተጠየቁት ዋልትዝ "ከእኛ ጋር የሚመክር፣ በመጨረሻም ከሩሲያውያን ጋር እና ይህን ጦርነት የሚያቆም መሪ እንፈልጋለን" ብለዋል።"የፕሬዚዳንት ዘለንስኪ ግላዊ ወይም ፖለቲካዊ ተነሳሽነት በሀገራቸው ውስጥ ያለውን ውጊያ ከማስቆም የተለየ መሆኑ ከታወቀ፣ በእጃችን ላይ እውነተኛ ጉዳይ ያለን ይመስለኛል" ሲሉ ዋልትዝ አክለዋል።የዩናይትድ ስቴትስ ከፍተኛ የትራምፕ አጋር እና የዩክሬን ተሟጋች የሆኑት የደቡብ ካሮላይና ሴናተር ሊንሴይ ግራሃም ለጋዜጠኞች በሰጡት አስተያየት የዋይት ሀውስ ግጭትን ተከትሎ ዩናይትድ ስቴትስ ከዘለንስኪ ጋር መስራት ትችል እንደሆነ ጥያቄ እንደፈጠረባቸዉ ተናግረዋል፡፡
በስምኦን ደረጄ
@Ethionews433 @Ethionews433
ከዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጋር ቅርርብ ያላቸዉ ከፍተኛ የሪፐብሊካን ባለስልጣናት የዩክሬኑን ፕሬዝዳንት ቮልዲሚር ዘለንስኪን ከሩሲያ ጋር በሚያደርጉት ጦርነት ላይ ያላቸውን አቋም እንዲቀይሩ ወይም ወደ ስልጣን እንዲለቁ በመገፋፋታቸዉ ባለፈው ሳምንት አወዛጋቢው የዋይት ሀውስ ስብሰባ በዩክሬን መሪ ላይ ጫና ፈጥሯል።
የአውሮፓ መሪዎች እሁድ እለት በለንደን በተካሄደው ስብሰባ ላይ ለዘለንስኪ አጋርነታቸዉን ያሳዩ ሲሆን የብሪታኒያ ጠቅላይ ሚኒስትር ኬይር ስታርመር አጋሮቻቸው የመከላከያ ጥረታቸውን እንዲያጠናክሩ አሳስበዋል፡፡ ትራምፕ እና ምክትል ፕሬዝዳንት ጄዲ ቫንስ በሞላላዉ የዋይት ሀዉስ ጽህፈት ቤታቸዉ ውስጥ ከዘሌንስኪ ጋር ከተጋጩ በኋላ የታቀደዉን የማዕድን ውል ሳይፈርሙ ቀደም ብሎ እንዲሄድ ምክንያት ሆኗል፡፡
ዘሌንስኪ በስብሰባው ላይ የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲንን እ.ኤ.አ. በ 2019 የተኩስ አቁም ስምምነትን አላከበሩም እና ገዳይ እና አሸባሪ ናቸዉ ሲሉ ተከራክረዋል ።የትራምፕ የብሄራዊ ደህንነት አማካሪ ማይክ ዋልትዝ ዘለንስኪ ጦርነቱን ለማቆም ለመደራደር ዝግጁ መሆናቸዉን ለዋሽንግተን አስተዳደር ግልፅ አይደለም ብለዋል። ዋልትዝ የትራምፕን ግብ በሞስኮ እና በኪየቭ መካከል የግዛት ስምምነትን በማካተት በአውሮፓ የሚመራ የደህንነት ዋስትናን በመተካት ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን አጽንኦት ሰጥተዋል።
ትራምፕ ዘለንስኪ ከስልጣን እንዲለቁ ይፈልጉ እንደሆነ የተጠየቁት ዋልትዝ "ከእኛ ጋር የሚመክር፣ በመጨረሻም ከሩሲያውያን ጋር እና ይህን ጦርነት የሚያቆም መሪ እንፈልጋለን" ብለዋል።"የፕሬዚዳንት ዘለንስኪ ግላዊ ወይም ፖለቲካዊ ተነሳሽነት በሀገራቸው ውስጥ ያለውን ውጊያ ከማስቆም የተለየ መሆኑ ከታወቀ፣ በእጃችን ላይ እውነተኛ ጉዳይ ያለን ይመስለኛል" ሲሉ ዋልትዝ አክለዋል።የዩናይትድ ስቴትስ ከፍተኛ የትራምፕ አጋር እና የዩክሬን ተሟጋች የሆኑት የደቡብ ካሮላይና ሴናተር ሊንሴይ ግራሃም ለጋዜጠኞች በሰጡት አስተያየት የዋይት ሀውስ ግጭትን ተከትሎ ዩናይትድ ስቴትስ ከዘለንስኪ ጋር መስራት ትችል እንደሆነ ጥያቄ እንደፈጠረባቸዉ ተናግረዋል፡፡
በስምኦን ደረጄ
@Ethionews433 @Ethionews433