📌ከሥራ ቦታቸው ታፍሰውና ለሁለት ሳምንታት ታስረው የተለቀቁ ግለሰቦች ስለቆይታቸው ተናገሩ
📌‹‹በወንጀል የሚጠረጠሩ ግለሰቦችን ካልሆነ በስተቀር ፖሊስ በዘፈቀደ ከመንገድ ዳር አፍሶ አያስርም››
- አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን
ከሥራ ቦታቸው ታፍሰው አዲስ አበባ ቃልቲ የአሽከርካሪዎች ማሠልጠኛ አካባቢ ውኃ ልማት ጀርባ በሚገኘው ካምፕ ለአሥራ አምስት ቀናት ያህል ቆይተው መለቀቃቸውን፣ ከካምፑ የወጡ ግለሰቦች ተናገሩ፡፡ በወንጀል የሚጠረጠሩ ግለሰቦችን ካልሆነ በስተቀር ፖሊስ ከመንገድ ዳር አፍሶ እንደማያስር የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ምላሽ ሰጥቷል፡፡
በለውዝ ንግድ የምትተዳደረውና ስሟ እንዲጠቀስ ያልፈለገች አስተያየት ሰጪ ለሪፖርተር እንደተናገረችው፣ ለውዝ ከምትነግድበት ቦሌ መድኃኔዓለም አካባቢ ጥር 27 ቀን 2017 ዓ.ም. ከቀኑ አምስት ሰዓት ፖሊሶች በፓትሮል መኪና ጭነው እንደወሰዷት ተናግራለች፡፡
‹‹የምሸጠውን ለውዝ እንደያዝኩ ፖሊሶች በመኪና ጭነው አዲስ እየተገነባ በሚገኘው ‹አደይ አበባ› ስቴዲየም አካባቢ ወዳለው ፖሊስ ጣቢያ ይዘውኝ ሄዱ፤›› የምትለው አስተያየት ሰጪዋ፣ ወንዶችና ሴቶች ተቀላቅለው በሚታሰሩበት በዚሁ ፖሊስ ጣቢያ ለሦስት ቀናት ማደሯን ተናግራለች፡፡
ከሦስት ቀናት የፖሊስ ጣቢያ ቆይታ በኋላ ከሌሊቱ አምስት ሰዓት ከሌሎች እንደ እሷ ከመንገድ ከታፈሱ ወንዶችና ሴቶች ጋር በመሆን በአውቶቡስ ተጭነው፣ ቃሊቲ የአሽከርካሪዎች ማሠልጠኛ አካባቢ ወደሚገኘው ካምፕ መወሰዳቸውን ገልጻለች፡፡..........................
[ @MadoNews ]
📌‹‹በወንጀል የሚጠረጠሩ ግለሰቦችን ካልሆነ በስተቀር ፖሊስ በዘፈቀደ ከመንገድ ዳር አፍሶ አያስርም››
- አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን
ከሥራ ቦታቸው ታፍሰው አዲስ አበባ ቃልቲ የአሽከርካሪዎች ማሠልጠኛ አካባቢ ውኃ ልማት ጀርባ በሚገኘው ካምፕ ለአሥራ አምስት ቀናት ያህል ቆይተው መለቀቃቸውን፣ ከካምፑ የወጡ ግለሰቦች ተናገሩ፡፡ በወንጀል የሚጠረጠሩ ግለሰቦችን ካልሆነ በስተቀር ፖሊስ ከመንገድ ዳር አፍሶ እንደማያስር የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ምላሽ ሰጥቷል፡፡
በለውዝ ንግድ የምትተዳደረውና ስሟ እንዲጠቀስ ያልፈለገች አስተያየት ሰጪ ለሪፖርተር እንደተናገረችው፣ ለውዝ ከምትነግድበት ቦሌ መድኃኔዓለም አካባቢ ጥር 27 ቀን 2017 ዓ.ም. ከቀኑ አምስት ሰዓት ፖሊሶች በፓትሮል መኪና ጭነው እንደወሰዷት ተናግራለች፡፡
‹‹የምሸጠውን ለውዝ እንደያዝኩ ፖሊሶች በመኪና ጭነው አዲስ እየተገነባ በሚገኘው ‹አደይ አበባ› ስቴዲየም አካባቢ ወዳለው ፖሊስ ጣቢያ ይዘውኝ ሄዱ፤›› የምትለው አስተያየት ሰጪዋ፣ ወንዶችና ሴቶች ተቀላቅለው በሚታሰሩበት በዚሁ ፖሊስ ጣቢያ ለሦስት ቀናት ማደሯን ተናግራለች፡፡
ከሦስት ቀናት የፖሊስ ጣቢያ ቆይታ በኋላ ከሌሊቱ አምስት ሰዓት ከሌሎች እንደ እሷ ከመንገድ ከታፈሱ ወንዶችና ሴቶች ጋር በመሆን በአውቶቡስ ተጭነው፣ ቃሊቲ የአሽከርካሪዎች ማሠልጠኛ አካባቢ ወደሚገኘው ካምፕ መወሰዳቸውን ገልጻለች፡፡..........................
[ @MadoNews ]