🇵🇸ሐምዱ ቋንጤ🇵🇸


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha
Toifa: ko‘rsatilmagan


ይህ ቻናል ቁርኣን እና ሐዲስ መሰረት በማድረግ የመልካም ቀደምቶቻችን ፋና በመከተል ስለ እስልምናችን የምንማማርበት እና የምንመካከርበት ቻናል ነው።
✍እስልምና አማራጭ የሌለው መፍትሔ ነው‼
👇🏾👇🏾👇🏾
@hamdquante
አስተያየትዎ ይበልጥ ይገነባናል
👉🏿 @hamdquante_bot👈🏿

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Toifa
ko‘rsatilmagan
Statistika
Postlar filtri



   ሀዘኔን ብሶቴ
መከራ ጭንቀቴ

  ወደ ማን ላሰማ
ማን ነው የሚሰማ??

  ችግሬን ሚረዳው
መላ ሚያመጣው??


ወዳጄ ብነግረው  ውስጡ ይጨነቃል
  ሊረዳኝ ካልቻለ  ልቡ ይሰበራል።

ጠላቴ ብነግረው  ይበልጥ ይደሰታል
አይደለም ሊረዳኝ  ጭራሽ ይሳለቃል።



🤲የሰማዩ ጌታ   የምድር ባለቤት🤲
ጭንቀቴን አንሳልኝ  ላንተ ልበል አቤት።

ውስጤን የረበሸው  ልቤን ያስጨነቀው
🤲ሁሉም እንዲሳካ  ይሆናል ሁን በለው🤲





https://t.me/hamdquante


🤲



     ኣይ የእኛ ዘመን……………

   አንድ ሰው መሸጥ ሲፈልግ ብቻ ነው የሌሎች ቋንቋ መልመድ የሚጠበቅበት;

መግዛት ሲፈልግማ…………
ሁሉም የእሱ ቋንቋ ይለማመዳሉ!!






https://t.me/hamdquante



የታደለ ሰው ማለት……………

🌠
ረመዷን ከመግባቱ በፊት ነፍሱን ያስተካከለ ነው!!





https://t.me/hamdquante



ያሳዝናል በጣም!!

ወደ ጀሀነም ሲሄድ ሁሉም ጓደኞቹ አጣቸው: እዛ የሉም። ለካስ; ሁሉም ሳይነግሩት ተውበት አርገው ወደ አላህ ተመልሰው ነበር።


እንዲህም ሊከሰት ይችላልና…………
ማንም ሳትጠብቅ, ማንም ሳታማክር አሁኑኑ ወደ አላህ ተመልሰህ ነፍስህን አድን!!





https://t.me/hamdquante



   የነብዩ ሙሐመድﷺ በላጭነት…………

ይህ ደሞ በጣም ለየት ያለ ነው!!
    አላህ ከነብዩ ሙሐመድ በፊት የላካቸው ነብያቶች ከህዝቦቻቸው የተለያዩ ትችት እና ማነወር ሲደርስባቸው: ነብያቶቹ ራሳቸው ነበር ለተቃዋሚያቸው ምላሽ የሚሰጡት። ወይም ራሳቸው ምላሽ እንዲሰጡ አላህ ያዛቸው ነበር።


ለምሳሌ፦
የኑህ ህዝቦች ለኑህ እንዲህ ብለው ተቹት……
📖{قَالَ ٱلْمَلَأُ مِن قَوْمِهِۦٓ إِنَّا لَنَرَىٰكَ فِى ضَلَٰلٍۢ مُّبِينٍۢ}
{ከሕዝቦቹ (የካዱት) መሪዎቹ "እኛ በግልጽ ጥመት ውስጥ ሆነህ እናይሃለን" አሉት፡፡}


ኑህ በራሱ እንዲህ ሲል መለሰላቸው………
{قَالَ يَٰقَوْمِ لَيْسَ بِى ضَلَٰلَةٌۭ وَلَٰكِنِّى رَسُولٌۭ مِّن رَّبِّ ٱلْعَٰلَمِينَ}
{"ህዝቦቼ ሆይ! ምንም ጥመት የለብኝም፡ ግን እኔ ከዐለማት ጌታ የተላክሁ ነኝ" አላቸው።}

    [አል_አዕራፍ::⁶¹]


ለሁድ ህዝቦቹ እንዲህ ተቹት………
📖{قَالَ ٱلْمَلَأُ ٱلَّذِينَ كَفَرُوا۟ مِن قَوْمِهِۦٓ إِنَّا لَنَرَىٰكَ فِى سَفَاهَةٍۢ وَإِنَّا لَنَظُنُّكَ مِنَ ٱلْكَٰذِبِينَ}
{ከሕዝቦቹ እነዚያ የካዱት መሪዎች "እኛ በሞኝነት ላይ ሆነህ እናይሃለን፡ እኛም ከውሸተኞቹ ነህ ብለን እንጠረጥርሃለን" አሉት፡፡}


በራሱ እንዲህ መለሰላቸው…………
{قَالَ يَٰقَوْمِ لَيْسَ بِى سَفَاهَةٌۭ وَلَٰكِنِّى رَسُولٌۭ مِّن رَّبِّ ٱلْعَٰلَمِينَ}
{"ህዝቦቼ ሆይ! እኔ ሞኝነት የለብኝም፡ ግን እኔ ከዐለማት ጌታ የተላክሁ ነኝ" አላቸው»

       [አል_አዕራፍ::⁶⁷]


ለሙሳ ፊርዓውን እንዲህ ተቸው……………
📖{فَقَالَ لَهُ فِرْعَوْنُ إِنِّي لَأَظُنُّكَ يَا مُوسَى مَسْحُورًا}
{ፊርዓውን ለእሱ "ሙሳ ሆይ! እኔ የተደገመብህ ትመስለኛለህ" አለው።}


ሙሳ ራሱ እንዲህ መለሰለት…………
 {وَإِنِّي لَأَظُنُّكَ يَا فِرْعَوْنُ مَثْبُورًا}
{"ፊርዓውን ሆይ! የምትጠፋ እንደሆንክ ነው የምገምትህ" አለው።}

      [አል_ኢስራእ:¹⁰²]


   ነብዩ ሙሐመድ ግን ከህዝቦቻቸው የተለያዩ ትችት እና ማነወር በሚደረግባቸው ጊዜ ከሌሎቹ ለየት ባለ መልኩ ራሳቸው ሳይሆኑ ቀጥታ አላህ ነበር ለተቃዋሚዎቻቸው ምላሽ የሚሰጣቸው።

ለምሳሌ፦
   ህዝቦቻቸው "እብድ" እያሉ ሲተቿቸው; አላህ እንዲህ መለሰላቸው………
📖{وَمَا صَاحِبُكُم بِمَجْنُونٍ}
{ባልደረባችሁ እብድ አይደለም።}

     [አል_ተክዊር:²²]


   ህዝቦቻቸው "ጥመት ላይ ወድቆ ነው" እያሉ ሲተቿቸው; አላህ እንዲህ ሲል ምላሽ ይሰጣቸዋል………
📖{مَا ضَلَّ صَاحِبُكُمْ وَمَا غَوَى}
{ባልደረባችሁ አልጠመም አልተሳሳተምም።}

    [አል_ነጅም:²]


ህዝቦቹ "ገጣሚ…… ምናምን" እያሉ ሲተቿቸው; አላህ እንዲህ ብሎ ይመልስላቸዋል………
📖{وَمَا عَلَّمْنَٰهُ ٱلشِّعْرَ وَمَا يَنۢبَغِى لَهُۥٓ ۚ إِنْ هُوَ إِلَّا ذِكْرٌۭ وَقُرْءَانٌۭ مُّبِينٌۭ}
{(ሙሐመድን) ግጥምን አላስተማርነውም፡ ለእሱም አይገባውም፡፡ እርሱ (መጽሐፉ) መገሰጫና ገላጭ ቁርኣን እንጅ (ግጥም}) አይደለም፡፡}

       [ያሲን:⁶⁹]



የእሳቸው ተከታይ መሆን ክብር ያጎናፅፋል!!
صلوا عليه وسلموا تسليما 
https://t.me/hamdquante



አስቤዛ ገዝቶ እንዲመጣ ከላከችው በኋላ የተወሰነውን ገዛዝቶ አካውንቱ ቀይ ሲያበራበት በቃኝ ብሎ ወደ ቤት ይመለሳል።

ፌስታሉን ተቀብላው ስትፈታትሽ ለካስ በጣም የምትፈልገው ነገር አልተገዛም ኖሯል።

ብስጭት ብላ መጥታ "ሽንኩርት አልገዛህም እንዴ?" ስትለው

"ውዴን የሚያስለቅስ ነገርማ በፍፁም ወደ ቤታችን አይገባም።"
እና ይሙት እንዴ?





https://t.me/hamdquante



ዒባዳ ሰርቶ ከሚኩራራ ሰው;
ወንጀል ሰርቶ የሚፀፀት ሰው ይሻላል።


ወንጀል ላይ ከሆንክ;   ተመለስ!!
ዒባዳ ላይ ከሆንክ; ተናነስ!!





https://t.me/hamdquante


ቀኑ ረዘመብኝ ለሊቱም አይነጋ

እንዴት እፎይ ልበል ልቤስ እንዴት ይርጋ

ጭራሽም ባሰብኝ ጨመረ ጉጉቴ

ሀረም እስክገባ ወጥቼ ከቤቴ

      እንቅፋት የሆነው ወንጀሌ ነውና

ጌታዬዋ ጥፋቴን ምረኸኝ ዐፉ በለኝና

      እባክህን ጥራኝ መካና መዲና



👉በውስጥ ከደረሰን
                  https://t.me/mesjidalteqwawenabo

👆
👇
https://t.me/hamdquante



ሕይወት በውሳኔ የተሞላች ናት፡፡

በተለይም አንዳንድ ጊዜ በሕይወትህ ውስጥ እንቅፋት የሚሆኑብህንና ደስታህን የሚያጨልሙብህ ሰዎች ካንተ ማራቅ የግድ ነው፡፡

ይህን ማድረግ ካቃተህ: የሕይወት ፈተናዎችህ ጉልበት እንዲኖራቸው አቅም እየሰጠህ መሆኑን እወቅ።


ራሱን ያወቀ ሰው ሁልጊዜ በኑሮው ደስተኛ ነው!!

ሌላ ሰው ለመምሰል ስትሞክር: ማንነትህ ታጣና ሕይወትህ ለዛ አይኖራትም!!




      🤝መልካም አዳር
https://t.me/hamdquante



    መንግስት ቸላ ብሎን እንጂ በብዙ እብዶች እኮ ነው ተከበን ያለነው። ሆ!!



https://t.me/hamdquante



ብዛቱ ሳይሆን እውነቱን ነው የተፈለገው!!


አንዱ መርቃን ነው። ሰላት አትሰግድም ተብሎ ይታሰራል። ለቃለ መጠይቅ ቃዲ ዘንድ ይቀርብና……

ቃዲው… "ለምንድን ነው ሰላት የማትሰግደው?"
መርቃን… "እሰግዳለሁ እኮ ዋሽተውብኝ ነው።"
ቃዲው… "የፈጅር ሰላት ስንት ረከዐ ነው የሚሰገደው?"
መርቃን… "ሀያ ረከዐ"
ቃዲው… "አስራችሁ ወደ እስር ቤት አስገቡት።"



እስር ቤት ከገባ በኋላ እዛ ከነበሩ ሌሎች ታራሚዎች ጋ ጨዋታ ይጀምራል።

ታራሚው… "ምን ሰርተህ ነው የታሰርከው?"
መርቃኑ…"ዳኛው የፈጅር ረከዐ ስንት ነው ሲለኝ ሀያ ብዬው"
ታራሚው… "ፋራ ነህ እንዴ? ለምን ሁለት አላልከውም?"

መርቃኑ…… "አንተ ጀዝባ! ሀያ ብዬው ራሱ አላስደሰተውም ጭራሽ ለምን ሁለት አላልከውም ትለኛለህ?"







https://t.me/hamdquante



"🤳አካውንትህ ላክልኝ"
ከሚለው ንግግር በላይ አነቃቂ የለም።



ይላል የዘመኑ አባባል
https://t.me/hamdquante



በመስጂድ, በመድረሳ, በየትኛውም ዐይነት የዳዕዋ ዘርፍ እየተንቀሳቀስክ እንደሆነ ካወቀህ ገና ሲያይህ በስስት በሽታ የገረጣ ፊቱ የሚቀያይርብህ በኺል በሞላበት;

"ዳዕዋው የእኔም የአንተም አደራ ነው!! አብሽር በምችለው ከጎናችሁ ነኝ!!"
በሚሉ የኢማን ሽቶ ግንባራቸው ላይ በሚያበራ ወንድሞች ላይ የአላህ ሰላምታ ይስፈን!!



ዲን ላይ መተጋገዝ የነብያቶች አካሄድ ነው፦
📖 {…سَنَشُدُّ عَضُدَكَ بِأَخِيكَ …}
{…ጡንቻህን በወንድምህ እናጠነክራለን…}





https://t.me/hamdquante



    የሸመገሉ አባቶች "ሸይኽ" እያሉ ማክበር ኢስላማዊ ስርዓት ነው!!

📖{قَالَ مَا خَطْبُكُمَا ۖ قَالَتَا لَا نَسْقِى حَتَّىٰ يُصْدِرَ ٱلرِّعَآءُ ۖ وَأَبُونَا شَيْخٌۭ كَبِيرٌۭ}
{……"ጉዳያችሁ ምንድን ነው?" አላቸው፡፡ "እረኞቹ ሁሉ (መንጋዎቻቸውን) እስከሚመልሱ አናጠጣም፡ አባታችንም ትልቅ ሸይኽ (ሽማግሌ) ነው» አሉት፡፡}

         [አል_ቀሰስ:²³]



📖{قَالُوا۟ يَٰٓأَيُّهَا ٱلْعَزِيزُ إِنَّ لَهُۥٓ أَبًۭا شَيْخًۭا كَبِيرًۭا فَخُذْ أَحَدَنَا مَكَانَهُۥٓ ۖ إِنَّا نَرَىٰكَ مِنَ ٱلْمُحْسِنِينَ}
{የተከበርከው ሆይ! "ለእርሱ ትልቅ ሸይኽ (ሽማግሌ) አባት አለው፡፡ ስለዚህ በእርሱ ስፍራ አንደኛችንን ያዝ፡፡ እኛ ከመልካም ሠሪዎች ሆነህ እናይሃለን" አሉት፡፡}

        [ዩሱፍ:⁷⁸]



📖{قَالَتْ يَٰوَيْلَتَىٰٓ ءَأَلِدُ وَأَنَا۠ عَجُوزٌۭ وَهَٰذَا بَعْلِى شَيْخًا ۖ إِنَّ هَٰذَا لَشَىْءٌ عَجِيبٌۭ}
{"ዋልኝ! እኔ አሮጊት ይህም ባሌ ሸይኽ (ሽማግሌ) ሆኖ ሳለ እወልዳለሁን? ይህ በእርግጥ አስደናቂ ነገር ነው" አለች፡፡}

          [ሁድ:⁷²]



🤝ለስላሳ: ትሁት እና ገር ባሪያ ሁን!!
https://t.me/hamdquante



    ነብዩﷺ  አላህ መልእክተኛ አድርጎ የላካቸው ትልቁ ዐላማ ሽርክን ገርስሶ ተውሒድ ለማስፈን ነው።

   እንደሚታወቀው ብዙኃን ሙሽሪኮች አላህ ላይ የሚያጋሯቸው ነብያቶች እና በሆነ ዘመን የነበሩ ደጋግ ሰዎችን ነው። ስለሆነም ነብዩ ነብያቶችን ለአላህ አጋር አድርጎ ከመያዝ አጥብቀው ያወግዛሉ።

  ሌሎች ነብያቶች እንዳይመለኩ ከሚያወግዙት በበለጠ ራሳቸው እንዳይመለኩ አስጠንቅቀው ያስተምራሉ። ቀብራቸው እንዳይመለክ ጌታቸውን ይማፀናሉ። ከፊል ሰዎች ቀላል የሚመስላቸው ነገር ላይ ራሱ "አላህ እና አንተ ከፈለክ" ሲባሉ በቁጣ «ለአላህ ቢጤ እያደረከኝ ነው??» ብለው ያወግዛሉ። ይህ የሲራጠል ሙስተቂም መንገድ ነው!!


እናም ወዳጄ………
  አንድ ሸይኽ ወይም አንድ ኡስታዝ ሰዎችን በጭፍን ከመከተል እያወገዘ የሚያስተምር ከሆነ: ራሱ በሚያስተምረው ትምህርት መሰረት እሱንም ቢሆን ተማሪዎቹ በጭፍን መከተል እንደሌለባቸው እሱና አድማጮቹ ሊገነዘቡ ይገባቸዋል።


  የኢስላም ፈርጥ የሆኑ ቀደምት ዑለማዎች ከመሃላቸው አንዱን ነጥሎ ተቅሊድ ማድረግ የማይቻል ነገር ሆኖ: የአንተን ሸይኽ መከተል ግን የምታግራራ ከሆነ ገና መታጠብ ያለበት ነገር ለመኖሩ ማሳያ ነው።




https://t.me/hamdquante



እርሶ የቱጋ ኖት??

የመጀመሪያ ሚስት………
የላጤ አስተዳደር ላይ የሚደረግ አመፅ ተደርጋ ትታያለች፣።

ሁለተኛዋ ሚስት………
የመጀመሪያ ትግል ላይ የተፈፀሙ ስህተቶች የሚታረሙበት ሂደት ተደርጋ ትታያለች።

ሦሥተኛዋ ሚስት…………
ጠንካራ የሆነ ግዛት እንደ መመስረት ተደርጋ ትታያለች።

አራተኛዋ ሚስት………
ደህንነቱ የተጠበቀ ህዝብ እና ጠንካራ መከላከያ ያለው መንግስት ለመመስረትህ ማረጋገጫ ናት።




ባረከላሁ ፊክ!!
ካነበብከው በኋላ ለግዛት ሰላም ስትል ከስልክህ ላይ ደልተው።





https://t.me/hamdquante


🤳
ሌላው ይደረስበታል…………

ቀጣይ ግን ልክ ከኤርፖርት ሲወርዱ ጀምሮ GPS መግጠም ሳያስፈልግ አይቀርም!!



   ሕይወት በድመት እና በአይጥ መሃል እንዳለ ውድድር ናት። ብዙ ጊዜ አይጧ ታሸንፋለች።

ምክንያቱም፦
  ድመቷ ለምግብ ስትሮጥ፤
  አይጧ ግን ለሕይወት ነው የምትሮጠው።


የምልህ ከገባህ ......
  👌ሁል ጊዜ ከፍላጎትህ; አላማህን አስቀድም!!




https://t.me/hamdquante



“እየሱስ ይወድሃል” ይለዋል
"አዎን! ሁሉም ሙስሊም ሙስሊም ወንድሙ ይወዳል።" አለው


እኛም ሙስሊም ወንድማችን ስለ ሆነ እንወደዋለን!!




https://t.me/hamdquante

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.