ማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማእከል


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha
Toifa: ko‘rsatilmagan


በማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማእከል የምዕመናን መረጃ መለዋወጫና ትምህርት መስጫ አውታር ነው፡፡

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Toifa
ko‘rsatilmagan
Statistika
Postlar filtri


የማኅበሩ ዋና ሥራ አስፈፃሚ መምህር ዋሲሁን በላይ ግንባታው  አሁን ያለበትን ደረጃና በዚህ ዓመት የተያዘውን እቅድ አስመልክቶ  ያቀረቡ ሲሆን በዚህ የቀጣይ የቤተክርስቲያን አገልግሎትን የሚያሳልጥ ማእከል ግንባታ የማኅበሩ አባላት እና የአገልግሎቱ ደጋፊዎች የበኩላቸውን በማድረግ የዚህ ታሪክ እንዲሆኑ ጠይቀዋል ::

የአሜሪካ ማእከል አባላትም በልኀቀት ማእከሉ ግንባታ ላይ የበኩላቸውን አሻራ እንደሚያስቀምጡ በውይይቱ ላይ ቃል ገብተዋል።

ዘገባው የአሜሪካ ማእከል ሚዲያ ክፍል ነው።


ለልኀቀት ማእከሉ ግንባታ የበኩላቸውን ድርሻ ለመወጣት  ዝግጁ መሆናቸውን የአሜሪካ ማእከል አባላት አሳወቁ !!!

ማኅበሩ ባለ 14 ወለል የልኀቀት  ማእከል ግንባታ  ግንባታ መጀመሩንም ለአባላቱ አብስሯል:: በውይይቱ በመገኘት መልእክት ያስተላለፉት የማኅበረ ቅዱሳን  ሰብሳቢ አቶ ካሳሁን ኅ/ማርያም የማኅበሩ አገልግሎት እየዘመነ እና እየሰፋ በመሄዱ ተጨማሪ ሕንጻ ግንባታ ማከናወን እንዳስፈለገው አብራርተዋል :: በተጨማሪም የሚገነባው የልኀቀት  ማእከል የማኅበሩ አገልግሎት የደረሰበትን ጥልቀት እና ስፋት ከግምት በማስገባት የተጀመረ ሥራ መሆኑን አንስተው ሲጠናቀቅ ማኅበሩ ለቅድስት ቤተክርስቲያን የሚያበረክተውን ጉልህ አስተዋጽኦ የሚያግዝ ይሆናል ብለዋል::

የልኀቀት ማእከሉ ከመሬት በላይ 14 ወለል የሚኖሩት ሲሆን ከመሬት በታች ደግሞ 2 ወለሎች ይኖሩታል :: እስከ 1000 ሰው ድረስ የሚይዝ ግዙፍ መሰብሰቢያ አዳራሽ እስከ 40 ሰዎች የሚይዙ የተለያዩ መለስተኛ አዳራሾች እና ዘመናዊ የሚዲይ ስቱዲዮዎች በልኀቀት  ማእከሉ የሚካተቱ ናቸው። ለማኅበሩ አገልግሎት የሚሆኑ በርካታ ቢሮዎች እና በቂ የመኪና መቋሚያም የማእከሉ ግንባታ የሚያካትታቸው መሆኑ በውይይቱ ተገልጿል :: ይህን ማእከል ለመገንባት 4 መቶ ሚሊዮን ብር የሚያስፈልግ ሲሆን እስካሁን በተከናወነው ሥራ የከርሰ ምድር ቁፋሮን ጨምሮ ከመሬት በታች ያሉት ሥራዎች ተከናውነዋል ::


ካቴድራሉም ተጠናቆ ተመርቆ ለአገልግሎት በመብቃቱ በጣም ደስተኞች ነን ብለዋል፡፡ 

ልዑካኑ ከብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ታዋድሮስ የግብጽ ኮፕቲክ ፓትርያርክ የተላከውን ስጦታ ለብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ያስረከቡ ሲሆን ቅዱስነታቸውም ስለ ስጦታው አመስገነዋል። ልዑካኑም ስለተደረገላቸው መልካም አቀባበልና ይሁንታ መደሰታቸውን ገልጸዋል።

አያይዘውም የቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በኢትዮጵያውያን ምእመናን ዕድሳቱ ተሠርቶ ማለቁ እጅግ ደስ እንዳሰኛቸው በመግለጽ የግብጽ ኮፕቲክ እንደተለመደው በካቴድራሉ መገልገል የሚችሉበት መንገድ ስለ ተመቻቸላቸው አመስገነዋል፡፡

ሜትሮፖሊታን በመጨረሻም ለኦርቶዶክሳውያን ምእመናን ባስተላለፉት መልእክት “ኢትዮጵያውያን በእምነታችሁ ጠንካራ ክርስቲያኖች ናችሁ፡፡ የሰይጣን ፈተና በመላው ዓለም ለምንኖር ክርስቲያኖች ቢሆንም እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ነው፤ ፈተናውን ያሳልፍልናል፡፡ በቤተክርስቲያን ሁናችሁ ጸልዩ" ሲሉ አባታዊ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

ምንጭ :- የኢኦተቤ መገናኛ ብዙኀን አገልግሎት ሥርጭት ድርጅት


ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ  የግብጽ ኦርቶዶክስ ኮፕቲክ ቤተክርስቲያን ልዑካንን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው ማነጋገራቸው ተገለጸ፡፡

ጥር ፳፬/፳፻፲፯ ዓ.ም

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበ ተክለ ሃይማኖት የግብጽ ኮፕቲክ ቤተርክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ ታውድሮስ ሁለተኛ መልእክት ይዘው የመጡትን ሜትሮፖሊታን አምባ ቢመን የነጋዳን፣ ጉስ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅዱስ ሚካኤል ገዳም ሓላፊን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው ጥር ፳፬ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም አነጋግረዋል፡፡

ሜትሮፖሊታን አምባ ቢመን ኮፕቲክ ቤተርክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ ታውድሮስ ሁለተኛ ያመጡትን መልእክት ለብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ያቀረቡ ሲሆን በዚህም  ቅዱስነታቸው የግብጽ ኮፕቲክ ልዑካንን ተቀብለው በማነጋገራቸው መደሰታቸውን ገልጸው፤ ይህም የሁለቱ አብያተ ክርስቲያናትን  አንድነት የሚያሳይ ነው ብለዋል ፡፡

በሁለቱ አብያተ ክርስቲያናት መካከል ያለው ግንኙነት የጥንት መሆኑን ያስረዱት ሜትሮፖሊታን አምባ ቢመን “በግብጽ በርካታ ኢትዮጵያውያን ይኖራሉ፤ በዚያም ቤተክርስቲያን አላቸው ይጸልያሉ፡፡ የግብጽ ቤተክርስቲያን በኢትዮጵያ ለአማኞቿ አገልግሎት የምትሰጥበትን የመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል  በጥሩ ሁኔታ ዕድሳት ተደርጎለት ተመርቆ ለአገልግሎት የሚጀምሩበትን ደብዳቤ ከቅዱስነታቸው መቀበላቸውን” አስረድተዋል፡፡

የሁለቱም አብያተ ክርስቲያንናት ግንኙነትም በጣም ጥሩ ነው ያሉት አቡነ ኤንገሎስ ኤልነጋዲ በኢትዮጵያ የግብጽ ቤተክርስቲያን ተወካይ እንደተናገሩት፤ በዚያም ቤተክርስቲያን አላቸው ይጸልያሉ፡፡ በኢትዮጵያም የግብጽ ቤተክርስቲያን አገልግሎቷን በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳምና በመንበረ ፀባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ታካሂዳለች፡፡




ከዚህ አንጻር ወደ ፊት እንደ ሀገረ ስብከት ኮሚቴዎችን በማስተባበርና በጋራ በመሆን የተጀመሩ አገልግሎቶችን በማጠናከር፣ አዲስ አማንያንን በማፍራት፣ መዋቅረ ቤተ ክርስቲያንንና ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንን ጠብቆ በማገልገል፣ አብያተ ክርስቲያናትን በማስፋፋት ምእመናን አገልግሎት እንዲያገኙ ለማድረግ በጋራ እየሠሩ እንደሚገኙ ጠቁመዋል።

ብፁዕ አቡነ ያዕቆብ በሩቅ ምሥራቅ የአብነት ትምህርት ቤቶች ከ22 አገራት በላይ እየተስፋፋ እንደሚገኝ በመግለጽ በዚህም በአካባቢው ዲያቆናትና ካህናት አባቶች አገልግሎቱን እያከናወኑ እንደሚገኙ ተናግረዋል።

አያይዘውም “ዓለም አቀፋዊ ሥራ ለመሥራትና ብዙዎችን ለማምጣትና ለማስተማር የተማረ የሰው ኃይል ያስፈልገናል፤ በተለይም ቤተ ክርስቲያንን ለማገልገል እንዲሁም ወንጌልን ለማስፋፋት ፍቅር፣ ሰላምና መከባበር ማእከላችን መሆን አለበት” በማለት መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።


በጃፓንና በኮሪያ አገራት የአብነት ትምህርት ቤቶች እየተስፋፉ እንደሚገኝ ተገለጸ

ጥር ፳፫/፳፻፲፯ ዓ.ም

በሩቅ ምሥራቅ የአብነት ትምህርት ቤቶች እየተስፋፋ እንደሚገኝ ብፁዕ አቡነ ያዕቆብ የሩቅ ምሥራቅ የእንግሊዝ፣ አየር ላንድና አከባቢው አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ የቅዱስ ሲኖዶስ አባልና በዩኒቨርሳል ሰላም ፌዴሬሽን የሰላም አምባሳደር ከማኅበረ ቅዱሳን ሚዲያ ጋር በቨርቿል (በበይነ መረብ) ባደረጉት ቆይታ ገልጸዋል።

የማኅበረ ቅዱሳን የሩቅ ምሥራቅ ማእከል ሰብሳቢ አቶ አንዱ አምላክ ተአምራት በአብነት ትምህርት ቤት፣ ግቢ ጉባኤያትና የስብከተ ወንጌልን አገልግሎት ላይ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሠራ እንደሚገኝ በመግለጽ አባቶችና ሀገረ ስብከቱ በሚሰጡን አቅጣጫ መሠረት ሐዋርያዊ ተልዕኮ ከሰንበት ትምህርት ቤቶችና ከምእመናን ጋር በመሆን በመተባበርና በመናብብ የተለያዩ ሥራዎችን እየሠሩ እንደሚገኙ ገልጸዋል።

በዚህም ሐዋርያዊ ተልዕኮ ከቻይናና ከሌሎች አገራት የተወጣጡ ተማሪዎችን በማስተማር፣ የተጠማቂያንን ፕሮጀክት በመሥራት፣ የአብነት ትምህርቶችን በመስጠት ድቁና እንዲቀበሉ በማድረግ እንዲሁም በሩቅ ምሥራቅና ለትምህርት በተለያዩ አከባቢዎች ለሚገኙ ምእመናን በአካልና በበይነ መረብ ሥልጠናዎችን እየሰጡ እንደሚገኙ አክለው አመላክተዋል።

ዲያቆን ዶ/ር ውብዓለም ደስታ የሩቅ ምሥራቅ ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ በበኩላቸው ቤተ ክርስቲያን ሥራዋን አስፍታ ከሠራች ለውጥ ማምጣት እንደሚቻል ገልጸው ሀገረ ስብከቱ ከሁሉም ባለ ድርሻ አካላት ጋር ተቀራርቦና ተናቦ መሥራቱን አስረድተው “በተለይ ለአገልጋዮች ሙሉ ኃላፊነትን ከተጠያቂነት ጋር በነጻነት የማገልገል ዕድል መስጠትና በቅርበት እየተከታሉ ለሚፈጠሩ ችግሮች መፍትሔዎችን መስጠት ለውጥ እንደሚያመጣ አይተናል” ብለዋል።


“ ቦሩ ሜዳ” የፊት ለፊት የጥያቄና መልስ መድረክ በማኅበረ ቅዱሳን ሚዲያ

“ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ለምን የአዋልድ መጻሕፍትን ትጠቀማለች ?''

በማኅበረ ቅዱሳን ወርኃዊ የስብከተ ወንጌል ጉባኤ ላይ

ጥር 25 ቀን 2017 ዓ.ም
ከቀኑ 7፡30 ጀምሮ በጠቅላይ ቤተክህነት አዳራሽ

በዕለቱ ስብከተ ወንጌልን ጨምሮ የአዋልድ መጻሕፍት መነሻ እና መድርሻ ከየት ወዴት እንደሆነ በሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ምላሽ ይሰጣል፡፡

እርስዎም የእምነት ልዩነት ሳይገድብዎ ከአዋልድ መጻሕፍት ጋር ተያይዞ ያሎዎትን ጥያቄ በማንሳት ምላሽ ያገኙ ዘንድ ተጋብዘዋል፡፡




One of the Jews seized the coffin with his hands, which were separated instantly from his body and they remained attached to the coffin. He regretted his evil deed and wept bitterly. Through the supplications of the saintly apostles, his hands were reattached to his body, and he believed in the Lord Christ. When they placed the body in the tomb, the Lord hid it from them.
Saint Thomas the Apostle was not present at the time of Saint Mary’s departure. He wanted to go to Jerusalem and a cloud carried him there. On his way, he saw the pure body of Saint Mary carried by the angels and ascended to heaven with it. One of the angels told him, “Make haste and kiss the pure body of Saint Mary,” and he did.
When Saint Thomas arrived where the disciples were, they told him about Saint Mary’s departure and he said to them, “You know how I conducted myself at the resurrection of the Lord Christ, and I will not believe unless I see her body.” They went with him to the tomb, and uncovered the place of the body but they did not find it. Everyone was perplexed and surprised. Saint Thomas told them how he saw the holy body and the angels that were ascending with it. They heard the Holy Spirit saying to them, “The Lord did not will to leave her body on earth.” The Lord had promised his pure apostles to let them see her in the flesh once again. They were waiting for this promise to be fulfilled, until the 16th day of the month of Nehassie (August), when the promise was fulfilled and they saw her.
The years of her life on earth were 60 years. She was 12 years old when she left the temple. She spent 34 years in Joseph’s house, until the Ascension of the Lord, and 14 years with Saint John the Evangelist, according to the commandment of the Lord which he told her at the cross, “Behold, this is your son,” and to Saint John, “Behold, this is your mother.”
May Saint Mary’s intercession and blessings be with us; Amen!
Source: Coptic Synaxarium


The Departure of Saint Mary
Our Lady, the all pure, Virgin Saint Mary, the Mother of God, departed on Tir 21. As she was always praying in the holy sepulcher, the Holy Spirit informed her that she was about to depart from this temporal world. When the time of her departure arrived, the virgins of the Mount of Olives came to her, with the apostles, who were still alive, and they surrounded her bed. The Lord Jesus Christ, to Whom is the glory, with a host of thousands and thousands of angels came to her and comforted her. He also told her about the eternal joy that was prepared for her, and she rejoiced. Then, the apostles and the virgins asked her to bless them. She stretched her hand and blessed them all, and she gave up her pure spirit in the hand of her Son and God. He then took her spirit to the heavenly mansions.
The apostles prepared the body in a fitting manner and carried it to Gethsemane. Some of the Jews blocked their way to prevent them from burying the body.


ቅዱስ ጴጥሮስና ሐዋርያት ሁሉም ‹‹ወደ አንቺ እንድንመጣ መንፈስ ቅዱስ አዘዘን፤ በደመና ላይም በተጫን ጊዜ ወደ አንቺ እንደ ዐይን ጥቅሻ ፈጥነን ደረስን›› አላት፡፡ በዚያን ጊዜ የክብር ባለቤት ልጇ ወዳጇ ኢየሱስ ክርስቶስ እልፍ አእላፍ መላእክቱን አስከትሎ ወደ እርሷ መጣ፡፡ (ጥር ፳፩ ስንክሳር)
እንዲህም አላት ‹‹እናቴ ሆይ ከዚህ ዓለም ድካም ላሳርፍሽ መጥቻለሁ›› አላት፡፡ እርሷ ግን ‹‹ልጄ ሰማይና ምድር የማይወስኑህን ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን በማኅፀኔ ተሸክሜህ፤ በድንግልና ወልጀህ እሞታለሁን?›› አለችው፡፡ በዚህ ጊዜ በሲኦል የነበሩ ነፍሳትን ሁሉ አሳያትና ‹‹እናቴ ሆይ ሞትሽ ለእነዚህ ሁሉ ነፍሳት መዳን ምክንያት (ቤዛ) ይሆናቸዋል›› አላት፡፡ ‹‹እነዚህን ሁሉ ከማርክልኝስ ይሁን›› አለች፡፡ በዚህ ጊዜ ቅድስት ሥጋዋን ከክብርት ነፍሷ ለይቶ በቃለ አቅርንት በይባቤ መላእክት በክብር ነፍሷን ዐሳረጋት፡፡ (መዝገበ ታሪክ ቁጥር አንድ ገጽ ፻፶፭፣ ጥር ፳፩ ስንክሳር)
የእመቤታችን አማላጅነትና ተረዳኢነት አይለየን፤ አሜን!


አስተርዮ ማርያም
የማይታየው የታየበት፣ የራቀው የቀረበበት፣ የረቀቀው መለኮት በገዘፈ ሥጋ ማርያም የተገለጠበት፣ የወልድ ልጅነት በአብና በመንፈስ ቅዱስ የተመሰከረበት፣ በልደቱ፣ በጥምቀቱ አንድነት በሦስትነት እንዲሁም መለኮት በሥጋ ሥጋም በመለኮት በተዋሕዶ ተገልጦ ምሥጢሩ ገሃድ የሆነበት የመገለጥ የመታየት ጊዜ የሆነው ወቅት በቤተ ክርስቲያናችን አስተምህሮ ዘመነ አስተርዮ እየተባለ ይጠራል፡፡
በዚሁ በዘመነ አስተርዮ መካከል የሚገኝ ስለሆነ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም “በዓለ ዕረፍት አስተርዮ ማርያም” እየተባለ ይጠራል፡፡ ይህ አስተርዮ ማርያም የምንለው ታላቅ በዓል እናታችን እመቤታችን ከዚህ ዓለም ድካም ያረፈችበት መታሰቢያ ሲሆን ቀኑም ጥር ፳፩ ነው፡፡ ሰማይና ምድር የማይወስኑትን የወሰነች፣ ሞትን በሞቱ የመሻር ሥልጣን ያለውን፣ ዓለምን በመዳፉ የጨበጠውን የወለደች ክብርት ቅድስት እመቤታችን ከዚህ ዓለም ድካም የምታርፍበት ቀን በደረሰ ጊዜ ይኸውም ጥር ፳፩ ቀን በዕለተ እሑድ በ፷፬ ዓመቷ፣ በ፵፱ ዓ.ም መንፈስ ቅዱስ የዕረፍቷ ጊዜ መድረሱን ነግሯት በልጇ መቃብር ሆና ጸሎት ታድርስ ነበር፡፡ እንዲህም ብላ ጸለየች፤ ‹‹ልጄ ወዳጄ ሆይ ልመናዬን ተቀብለህ ደቀ መዝሙርህን ዮሐንስን በዚህች ሰዓት አምጣው፤ እንዲሁም በሕይወተ ሥጋ ያሉ ሐዋርያትን ሁሉንም፣ ነፍሳቸውንም የለየሃቸውን አምጣቸው፤ አንተ የሕያዋንና የሙታን አምላክ ነህና›› አለች፡፡ (የጥር ፳፩ ስንክሳር)
በዚህ ጊዜ ዮሐንስን ደመና ተሸክማ ከኤፌሶን አመጣችው፤ ምስጋናም አቀረበላት፤ ሁሉም ሐዋርያት የሞቱትም ከመቃብር ተነሥተው ወደ እመቤታችን ደርሰው ሰገዱላት፡፡ እንዲህም ስትል ጠየቀቻቸው፤ ‹‹ትነግሩኝ ዘንድ እሻለሁ፤ ከዚህ ዓለም እንደምለይ ከወዴት ሰማችሁ?›› አለቻቸው፡፡


በውይይቱ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንና የሕንድ ማላንካራ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን በሚገኙባቸው የውጭ ሀገራት አንዱ ባንዱ የመገልገል እንድል የሚያመቻቹበት ሁኔታም እንደሚኖር  ተገልጿል።

ልዑካኑ አክለው እንደገለፁት በዐረብ ሀገራት ላይ ቤተክርስቲያንን ለማስፋፋት ያደረገችውን ጥረት በማድነቅ በሌሎች ክፍላተ ዓለማት ለምታደርገው እንቅስቀሴ ለመደገፍ ከጎን መሆናቸውን በማረጋገጥ ቃላቸውን ሰጥተዋል።

በመጨረሻም  በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ የማጠቃለያ ሐሳብና ለልዑካኑ የበረከት ስጦታ በመስጠት ውይይቱ ተጠኗቋል።



15 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.