አቡ አሚር አብደላህ (عبدالله الف نور)


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha
Toifa: ko‘rsatilmagan


ሙስሊሞችን እና የሙስሊም ሀገራትን የተመለከተ ትኩስ መረጃና ትንታኔ ለማግኘት ይህን ቻናል ይቀላቀሉ።

Связанные каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Toifa
ko‘rsatilmagan
Statistika
Postlar filtri


ማስታወሻ!

ሸር ይደረግ

ትልቅ ሆነህ ሳለ ትልቅ የሚያደርግህን መንገድ አትዘንጋ!!ተሳስተህ ሰው አታሳስት

አሁን አሁን በተጨባጭ የምመለከተው አንዳንድ ሰዎች ተሳስተው እያሳሳቱ ይገኛሉ። ከነሱ የተለየ አቋም ያንፀባረቁ ሰለፊዮችን ያለአግባብ በመውጋት የሚገኝ "ሰለፊያነት" ብዙ ርቀት አያስጉዝም።

ልዩነት ካለህ በአግባቡ ግለፅ።ከዚያ ውጭ የፈረስክን ልጓም ገታ አድርገው። ተሳስተህ ሰው አታሳስት። በነገራችን ላይ ተህዚር የምናደርግበት መንገድ ከመንሃጀዳእዋ ተለይቶ የማይታይ መሆኑን ማሰብ ይኖርብናል። ትልቅ ሆነህ ሳለ ትልቅ የሚያደርግህን መንገድ አትዘንጋ!! ደግሞም ሰውን ስትሀይስ ሂስህ ወዳንተ ዞሮ አንተኑ ሊያስተችህ የሚችል መሆን የለበትም።

ትልቅ ሰው አንዴ ይሳሳታል። ግን እንዴት በዚያ ላይ ይዘዎትራል?


አዲስ የኮሮና ዝርያ ተገኘ! ምንጭ ቢቢሲ

ለመሆኑ ይህ አዲስ የኮቪድ ዝርያ ምንድነው?
1ኛ፡- በብሪታኒያ በተለይም በሎንደንና አካባቢው እስከዛሬ ታይቶ የማይታወቅ የተህዋሲው ናሙና ተገኝቷል፡፡ መገኘቱ ብቻ ሳይሆን በታመሙ ሰዎች ላይ በብዛት የሚታየው የቫይረስ ዓይነትም ይኸው ዝርያ መሆኑ ድንጋጤን ፈጥሯል፡፡
2ኛ፡- ይህ የቫይረስ ዝርያ ሌሎች የተህዋሲ ዝርያዎችን በፍጥነት እየተካ ቦታውን እየያዘ መሆኑ ተጠቁሟል፡፡
3ኛ፡- ራሱን የሚያባዛበት መንገድ ለየቅል መሆኑ ምናልባት ለቁጥጥር ያስቸግር ይሆን የሚል ስጋትን ጨምሯል፡፡ ከመተንፈሻ አካል ውጭ ያሉ ሴሎችንም ራሱን እየለወጠ የማጥቃት አቅም ሊኖረው ይችል ይhoን የሚል ስጋትም አለ፡፡
4ኛ፡- ለመጀመርያ ጊዜ ይህ የተህዋሲ ዝርያ የተገኘው በመስከረም ወር ነበር፡፡ በጥቅምት ወር ሎንዶን አካባቢ በኮቪድ ከተያዙት ሲሶዎቹ የዚህ ተህዋሲ መልክ ተገኘባቸው፡፡ በታኅሣሥ ወር ደግሞ 75 ከመቶዎቹ ታማሚዎችን የለከፈው ይህ ልዩ ተህዋሲ መሆኑ ተረጋገጠ፡፡
5ኛ፡- ጠቅላይ ሚኒስትር ቦሪስ ጆንሰን ቅዳሜ ዕለት በሰጡት መግለጫ ይህ ተህዋሲ እስከዛሬ ከነበረው ቫይረስ ጋር ሲወዳደር የመዛመት ዕደሉ በ70 ከመቶ የፈጠነ ነው ብለዋል፡፡
6ኛ፡- አዲሱ የተህዋሲ ዝርያ በጊዜ ሂደት ራሱን ቀይሮ ይሁን ወይም ከሌላ ቦታ መጥቶ ለጊዜው የታወቀ ነገር የለም።
7ኛ፡- አዲሱ የተህዋሲ ዝርያ በመላው ብሪታኒያ የተሰራጨ ቢሆንም አሁን ክምችቱ በብዛት የሚኘው በለንደንና አካባቢው ነው፡፡ ከለንደን በተጨማሪ በደቡብ ምሥራቅና በምሥራቅ ኢንግላንድም እንዲሁ በስፋት ተመዝግቧል፡፡
8ኛ፡- ኔክስትስትሬይን የተሀዋሲ ዝርያዎችን የዘረ መል ኮድ የሚመዘግብ ድርጅት ሲሆን፣ ይህ ልዩ የተህዋሲ ዝርያ ከብሪታኒያ ወደ ዴንማርክና አውስትራሊያ መዛመቱን ተናግሯል፡፡ ኔዘርላንድና ጣሊያንም ይህ አዲሱ የተህዋሲው ዝርያ አገራቸው መግባቱን አረጋግጠዋል፡፡
9ኛ፡- ይህ ልዩ የተህዋሲ ዝርያ ቅንጣት በደቡብ አፍሪካም ተገኝቷል የተባለ ሲሆን በኋላ ላይ የወጡ መረጃዎች ግን ከዚህ ብሪታኒያ ተገኘ ከተባለው ተህዋሲ ጋር የዝርያ ተመሳሳይነት የላቸውም ብለዋል፡፡
10ኛ፡- ተህዋሲው ራሱን ቆርጦ እየቀጠለና እያባዛ ሊያመልጥ ቢችልም አሁን ወደ ገበያ እየገቡ ያሉ ክትባቶች ግን ማንነቱን ያጠፉታል፣ ፈውስም ይሆናል ተብሎ በስፋት ታምኗል፡፡




ሪፖርት አድርገዋል ፤ >> ሲሉ ለዚህ ፅሁፍ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል ። "በዚህ በመረጃ በታጨቀ ፅሁፍ ጋዜጠኛ ተመስገን የፍትህ ምንጮቹን ጠቅሶ " የቀድሞው የክልሉ የልዩ ኃይል አዛዥ ብ/ጄ ተፈራ ማሞ ፤ ከወራቶች በፊት ሁኔታውን ገምግመው < ችግር ሊፈጠር ይችላል > የሚል ግምት በመያዛቸው ፣ አንድ ሻንበል ልዩ - ኃይል ሞጣ ላይ ሰፍሮ እንዲጠብቅ መድበው እንደነበረ ተናግረዋል ። … "ይህ ኃይልም በቅማንት ጉዳይ እንደተነሳና ተመልሶ ወደ ሞጣ እንዳልሄደ ተመስገን ያብራራል ።

#### የሙስሊሞች የተቃውሞ እንቅስቃሴ

የክልሉ መንግሥት የተቃጠሉ መስጅዶችን እንዲገነባ፤ ንብረታቸው ለወደመባቸው ወገኖች ካሳ እንዲከፍል እና መልሶ እንዲያቋቁም ቢጠየቅም በንቀትና በትእቢት ተወጥሮ በማለፉ ህዝበሙስሊሙ በአራቱም ማእዘን እንዲሁም በውጭ ሀገር ጭምር ከፍተኛ ቁጣ አሰማ። በእምነት ላይ ያነጣጠረው ሙስሊም ተኮር ጥቃት በጓዳ የተቀመጡ እናቶችን እንኳ ሳይቀር ገፍቶ ያስወጣ ነበር።በእለቱ በባህርዳር ከተሰሙ መፈክሮች ውስጥ "በአማራ ክልል እያቆጠቆጠ የመጣው የመንግስት የሀይማኖት ጋብቻ መፍትሄ ይሰጠው" የሚል ይገኝበታል።በተለይ ኮምቦልቻ ከተማ ከዚህም ጠንከር ያሉ መፈክሮች ተደምጠዋል።

አጣሪ ቡድኑ ለአማራ ክልል ሁኔታውን ለማስረዳት ያደረገው ሙከራ ውጤት አልባ ሆነ።ሙስሊሙ ያስቀመጣቸው የካሳ፣ መልሶ የማቋቋምና የይቅርታ ጥያቄዎች ምላሽ ስላላገኙ የፌደራል መንግስት አቤት አለ። ፌደራል መንግስቱ ግን ጣልቃ ለመግባት አልደፈረም። ለራሱ ፖለቲካ እንዲመቸው ብቻ ግን ከአመት በኋላ እነስክንድርን ለመክሰስ የሞጣውን ጉዳይ አጣቅሶታል።

ለጥር 22 በተደረገው አለማቀፍ የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም ላይ በመላው አለም የተበተነው ኢትዮጵያዊ ሙስሊም መዋጮ አድርጓል። አንዳንድ ቅን ክርስቲያኖችም አስተዋፅኦ አድርገዋል። በዚህም ከ200 ሚሊየን ብር በላይ ተሰብስቧል።ግን ገንዘቡ እስካሁን ድረስ በግማሽ እንኳ ስራ ላይ አልዋለም።

ደዩስ ካልሆነ በስተቀር እያንዳንዱ ሙስሊም ይሄን እኩይ ተግባር በአይምሮው ቀርፆ ና በማስታወሻው መዝግቦ ለልጅ ልጁ የሚያስተላልፈው እንደሚሆን ይገመታል። ጉዳዩ እስካሁን ፍትህ አላገኘም። ስለዚህ የሚተው አይደለም።

ሸር ሸር


ልክ የዛሬ አመት ታህሳስ 10 /2012 በሞጣ የተከሰተው የሽብር ጥቃት

ሁሉም ሙስሊም ሸር ያድርገው!!
ሸር ሸር!! 100 ሸር!!

እለቱ አርብ ነበር። ታህሳስ 10 ኢትዮጵያ ሳታላይት ለመጀመሪያ ጊዜ ያመጠቅችበት እና በህዝቡ ዘንድ የኩራትና የከፍታ ስሜት የተፈጠረበት እለት ነበር።ሆኖም በተቃራኒው አመሻሽ ላይ በምስራቅ ጎጃም ሞጣ ከተማ የህዝቡን የከፍታ ስሜት አፈር እድሜ ያበላ የዝቅጠትና የጭካኔ ድርጊት ተፈፀመ።

በዚያ እለት አርብ (ጁማአ)ማታ በሞጣ ሙስሊሞች ላይ የተደረገው የሽብር ክስተት እንዲህ ነበር።

የሞጣ ከተማ አውቶቡስ መናህሪያ ገና ከቀኑ 11 ሰአት ላይ ተዘጋ፣ወደሞጣ የሚያስገቡ መንገዶች በተደራጁ አሸባሪዎች ተዘጉ፣ ኔትወርክ ተቋረጠ፣ የፓሊስ ፒክአፕ መኪናዎች ለሽብር ተግባር የሚውል ቤንዚን አመላለሱ፣ በሙስሊም ሱቆችና መኖሪያ ቤቶች የተከራዩ የከተማዋ ክርስቲያኖች ለቀው እንዲወጡ ተደረገ። ከዚያም 11 ሰዓት ገደማ ጊወርጊስ ቤተክርስቲያን ተቃጠለ በሚል ሙስሊሞችን ለማጥቃት በሽብር ቡድኑ ሆም ተብሎ ወሬ ተሰራጨ ።

ከዚያም ከጊዎርጊስ ቤተክርስቲያን ተደራጅተው የመጡ አሸባሪዎች መስጅዶችን ማንደድ ተያያዙት።ሙስሊሞች ተደናግጠው ሲወጡ የታጠቀ ፓሊስ "ግባ" እያለ እያስፈራራ አስመለሳቸው። የህዝብ ሰላም ለማስከበር አደራ የተሰጠው አካል እንዲህ ሆኖ ቀረ። የሽብር ቡድኑ የአካባቢውን ህዝብ በማደናበር የሙስሊሞችን ንብረት እና ምልክት(symbol) ወደማውደም፣ ማቃጠልና እና መዝረፍ አመራ ።

ከባህርዳር የተነሳው ልዩ ሀይል መንገድ ተዘጋብኝ በሚል ነገር አለሙ እስኪያልቅ ድረስ ዘገየ። በመሆኑም ድርጊቱ የቆመው ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ ልዩ ኃይል ወደ ከተማዋ ከገባ በኋላ ነበር። ባጠቃላይ ወደ300 ሱቆች ፣ 4 መስጊዶችና በውስጣቸው ያሉ ቅዱሳን መፅሀፍቶች፣ ግዙፍ የንግድ ህንፃዎች እና ብዙ ተሽከርካሪዎች በእሳት ጋዩ። የሞጣው የሽብር ድርጊት ከቃጠሎና ዘረፋ በተጨማሪ ድብደባና የግድያ ሙከራዎችም ነበሩበት።በአንደኛው መስጅድ ቅጥር ግቢ ውስጥ የነበረ ኢማም ከውስጥ እንዳለ ሊያቃጥሉት ሲሉ በመስኮት ዘሎ ሂወቱን ማትረፍ ችሏል።

አሸባሪዎችም ጊዎርጊስ የኛ፣ ማሪያም የኛ እያሉ በደቦ ጨፈሩ።የሙስሊም ሱቆች እና ቤቶች እንዲቃጠሉ የተደረገው የሽብር ቡድኑ ቀድሞ ባዘጋጀው የስም ዝርዝር አማካይነት እየተመረጠ ነበር።

ከክስተቱ ሁለት ሳምንታት በፊት «ሙስሊሞች ሊያጠቋችሁ ነው» በሚል ክርስቲያኖችን በሙስሊሞች ላይ የሚያነሳሳ የተቀናበረ ፊልም በተለያዩ የአገሪቱ ክፍል ሲታይ ሙስሊም አክቲስቶች ነገሩ አደገኛ ነው ብለው አስጠንቅቀው ነበር። ግን ትኩረት አላገኘም ነበር።
በሞጣ ከተማ ከቃጠሎው 15 ቀናት በፊት ሙስሊሞች በሰንበት ቀን ስራ እንዳይሰሩ የመከልከል እንቅስቃሴ ተጀምሮ ነበር።

####የክልሉ መንግስት ምላሽ

የክልሉ ርእሰመስተዳደር አቶ ተመስገን ጥሩነህ በጊዜው አንዲት ቃል መግለጫ እንኳ ትንፍሽ አላለም። ከ19 ቀን በኋላ ለገና በአል እንኳን አደረሳችሁ ለማለት በዋዜማው በኢቲቪ ብቅ ሲል እግረመንገዱን ስለክስተቱ ሲያነሳ«ሕጋዊ የሆነውን መጅሊስ ለማፍረስ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ግለሰቦች በመስጊዶቹ ቃጠሎ መሳተፋቸውን» በመግለፅ ሙስሊሞችን ወነጀለ። አገር አንቀጥቅጥ ተቃውሞ ሲደረግሞ "ማንም ስለጮኸ አይደለም! ሲል ንቀቱን አሳየ።

የአዴፓ ፅ/ቤት ሃላፊ አቶ ዮሃንስ ቧ ያለው ወደአፋር ሄዶ ከሙስሊም ወጣቶች ተቃውሞ ሲገጥመው እኛ በሀይማኖት ጉዳይ ጣልቃ አንገባም ብለን ነው ዝም ያልነው በማለት በኦርቶዶክስ ላይም ተመሳሳይ ጥቃት ሲፈፀም አልፈነዋል አለ።

ይህ ብቻ ሳያንስ በክልሉ የሚገኙ ሚዲያዎች ዶ/ር አብይ እና ታከለ ኡማ የሞጣውን ጥቃት ለምን አወገዙ ብለው አለቃቀሱ ።የክልሉ የሰላምና ደህንነት ቢሮ ሃላፊ አቶ አገኘሁ ተሻገር በድርጊቱ ላይ የተሳተፉ አካላትን ከማሳደድ ይልቅ በህዝበሙስሊሙ መካከል ያለውን ልዩነት ነቅሶ አውጥቶ ማራገብ መረጠ።«መንገድ ተዘጋብኝ» ያለው በእሱ ስር የነበረው ልዩ ኃይል ወደቦታው የደረሰው ሁሉም ነገር ተቃጥሎ ካለቀ በኋላ መሆኑ እየታወቀ መንገድ የዘጋውን ቡድን ለማደን አልቻለም።

መጅሊስ በሞጣ የተደረገውን የሽብር ጥቃት የሚያጣራ አብይ ኮሚቴ አዋቅሮ ወደቦታው ልኮ ነበር።አብይ ኮሚቴው ወደቦታው ሲሄድ እገታ ካጋጠመው በኋላ በድርድር ሞጣ ገብቶ ተጎጅዎችን አነጋግሮ ተቋማቱን ጎብኝቶ የታዘበውን ነገር ወይም ያገኘውን ግኝት መሰረት አድርጎ ከክልሉ አመራር ጋር ለመነጋገር ወደመስተዳድር ሲሄድ "በአስቸኳይ ስብሰባ ምክንያት" የክልሉን ፕሬዝደንት አቶ ተመስገንን ማግኘት አይቻልም የሚል ምላሽ ተሰጥቶታል።አጣሪ ኮሚቴው ወደሞጣ በሄደበት ወቅትም የሞጣ ከተማ አስተዳደር ፅፈት ቤት ኮሚቴውን ለማናገር ፈቃደኛ አልነበረም።

በአካባቢው የተሰማራው ፀጥታ አስከባሪ ወደዚያ ቦታ የሚያቀኑ ከፌደራልና ከክልል የተውጣጡ እንግዶች በካሜራ ያለውን ሁኔታ መቅረጽ እንዳይችሉ አግዷል።

በሞጣው ቃጠሎና ዝርፊያ ጋር በተያያዘ በቁጥጥር ስር ውለዋል የተባሉት ሰዎች ገሚሶቹ በሁለት ሺ ብር ዋስ የተፈቱ ሲሆን ቀሪዎቹ ደግሞ የወንጀል ህጉ አንቀፅ 420 ተጠቅሶ እስከ3 ወር ብቻ ሊያስፈርድባቸው በሚችል ክስ ተከሰሱ።

በሞጣ የደረሰውን የመስጊድና ቢዝነስ ተቋማት ውድመት ለማውገዝ በተለያዩ የአማራ ክልል ከተሞች ተቃውሞ እንደሚደረግ አቶ አበረ አዳሙ ባወቀ ጊዜ ሊደረግ የታሰበውን ተቃውሞ ክልሉን የማፍረስ ተግባር እንደሆነ በሚከተለውን መልኩ ገልፆት ነበር።"በግድ ይህ ክልል ይፍረስ ብሎ የሚመኝ አካል ካለ ተስፋ ይቁረጥ"።
እነዚህ ሰዎች ዛሬም በደህንነት መስሪያ ቤት ፣ በክልሉ ርእሰመስተዳድር ና በፓሊስ ኮሚሽነትርነት ቦታ ተወዝፈዋል።

###ከጥቃቱ በኋላ መረጃን ማድበስበስና ሌሎችን ተጠያቂ ለማድረግ የተደረገ ሙከራ

በሞጣው የሽብር ድርጊት በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ እጁ ያለበት ተጠርጣሪ ተጠያቂ እንዳይሆን አስቀድሞ ሌሎችን መክሰስ መርጧል።እስቲ በምሳሌ እንይ

የመንግስት ሚዲያዎች በተለይም የአማራ ክልል ሚዲያ መስጊድ ተቃጠለ ላለማለት ቤተእምነቶች ተቃጠሉ የሚል ሀረግ እየመዘዙ አስቀየሱ።
አንዳንድ የአማራ ክልል አመራሮች ጣታቸውን ወደ ህዋሃት ቀሰሩ።ሌሎች ደግሞ ሀይማኖትን የማይወክሉ "ትቂት ፅንፈኞች" በሚል አደባበሰዋቸው። እንደእስክንድር አይነቱ አሸባሪ ደግሞ ወደ የኦሮሚያ ብሄርተኞችን ተጠያቂ አደረገ።ማህበረቅዱሳን የተባለ ፅንፈኛ ድርጅት በሙስሊሞች የርስ በርስ መከፋፈል የመነጨ እንደሆነ በማስመሰል የራሱን የሀሰት ወሬ በቴሌቪዥኑ አሰራጨ።ዘመድኩንን የመሰሉ አንዳንድ ቁማርተኛ የኦርቶዶክስ ሰባኪዎች "ውሃብያ" የሚል ፈሊጥ ተጠቅመው ጉዳዩን በዚህ ምናባዊ ቡድን ላይ ለማላከክ ሞክረዋል። አንዳንድ ድኩማን አክቲቪስት ነን ባዮች ደግሞ ጉዳዩ የውጭ እጅ አለበት እስከማለት ደረሱ።ይሄ ሁሉ አካል መስጅዶች መልሰን ለመገንባት እንሰራለን የሚል የመደለያ ሩጫ ተሯሯጠ።ሩጫቸው ግን የሙስሊሙን ለቅሶ ለመቀማት እንጅ መልሶ ለመገንባት አልነበረም።

ከሌሎች በተለየ ስለሁኔታው የተሻለ ዘገባ የሰራው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በፍትህ ጋዜጣ ላይ ነበር። ፍትህ ጋዜጣ "ጎንደር እሽሩሩ" በሚለው ፅሁፉ የሚከተለውን አትቷል

"ስማቸውን መናገር ያልፈለጉ የፀጥታ ሀላፊ ፦


ለድንቁርና ተጣሪ መልስ አትስጥ

ከሸይኽ ኤሊያስ እና ከሸይኽ አህመድ አደም ኢልም አትያዝ የሚለውን የድንቁር ምክር አትስማ።

ይልቁንም ሳያፍር ባደባባይ እንዲህ የሚለውን ሰው ምንነት መልሰህ ገምግም ኢልም ያለችው ከማን ዘንድ እንደሆነች ያኔ ይገባሃል።

t.me/tewhidandmanner


አብይ በፓርላማ ካደረገው ንግግር መገንዘብ የሚቻለው

1)አባይ ሚዲያ የተባለ ሚዲያ የቀድሞው ደህንነት መስሪያ ቤት ያቋቋመው ነው።
2)የሀገር መከላከያ ልክ እንደምክር ቤት ስላልሆነ ከያንዳንዱ ብሄር የግድ እኩል ውክልና ሊኖረው አይችልም።የትግራይ ክልል በህዝቡ ቁጥር ልክ የሰራዊት አመራር ሊኖረው ይገባል።
3)ከሹመት(መጋቢት 24/2010) ጀምሮ በ2 አመት ተኩል ጊዜ ውስጥ የመንግስትን ትኩረት የሳቡ 113 ጎላ ያሉ ግጭቶች ተከስተዋል። ከነዚህ ውስጥ 37ቱ በኦሮሚያ 23ቱ በአማራ ክልል፣ 15 በቤኒሻንጉል፣ 14 በአዲስአበባ የተከሰተ ነው።ከነዚህም ውስጥ ባሌና ሞጣ ላይ የተከሰቱት ሀይማኖትን መሰረት ያደረጉ ናቸው።
4)አብዲ ኢሌ ከ30 ሺ በላይ ልዩ ሀይል ነበረው
5) ድሉ ወደእብሪትና ትእቢት ሊወስደን አይገባም።ድል ወደመናጠቅ እንዳንገባ የድል ጮቤ መርገጥ ማቆም አለብን።
6)ከትግራይ ህጋዊ ፓርቲዎች በስተቀር ትግራይን አንድም ሰው እንዲያስተዳድር አንፈልግም አናደርገውምም። ስለጦርነቱ ከህጋዊ የትግራይ ስራ አስፈፃሚ ዶ/ር ሙሉ ጋር ድርድር አድርገናል።
7)ህገመንግስቱን ማስጠበቅ
8)የኤርትራ ህዝብ ራቁት የነበረውን የሰሜን እዝ ወታደር አብልቶታል፣አልብሶታል፣አስታጥቆታል።

9)የሚኒስትሮች ምክር ቤትና ስራ አስፈፃሚውን ሳንድዊች አድርገን (መሀል ላይ ትተን) የውስጥ ምክክር እያደረግን ከህዝብ ጋር ተገናኘን(ወደህዝብ ወረድን)
10)በሚስጥር የሪፐብሊካን ጋርድ አቋቁመናል።መከላከያን በአዲስ ለማደራጀት ሚስጥራዊ ስራ ሰርተናል። ከፍተኛ፣ መካከለኛና ዝቅተኛ ብለን አመራሩን በ3 ከፍለነዋል። አዳዲስ መሳሪያዎችንም ታጥቀናል።

አስተያየት:በበኩሌ የሞጣውን ጥቃት እንደተራ ግጭት ብሎ መቁጠሩ እና ሙስሊም የሚበዛባቸው ብሄረሰቦች በመከላከያ ውስጥ አናሳ ሆነው እንዲቀጥሉ የሚያበረታታ ስርአት ማስቀጠሉን አልወደድኩለትም።የአባይ ሚዲያን ምንነት ማጋለጡ እና ድሉ ወደእብሪትና ትእቢት ሊወስደን አይገባም ማለቱን ግን ወድጀዋለሁ። አሃዳውያን በሚፈልጉት መልኩ ህገመንግስቱ ከተቀየረ አብይ መጀመሪያ የሚጣላው ከኢትዮጵያ ሙስሊም ጋር ነው። ከዚህ በኋላ አብይ መስራት ያለበት በዋናነት ከፌደራል ሀይሎች ጋር ነው፣ የትኩረት አቅጣጫውም የተዳከመውን ፌደራሊዝም መጠገንና ማከም ላይ መሆን አለበት። የመገንጠል እና የዘውጌ አክራሪነትን ግን ቢያስወግድ ጥሩ ነው።


ሕዳር 21/2013 የፓርላማ ውሎ

T.me//tewhidandmanner


ቅጥፈቶች

ቅጥፈት 1: የፓኪስታን መሪ ኢምራምን ካህን ለእስራኤል እውቅና እንድንሰጥ ሳውዲ ግፊት አድርጋብናለች ብሏል የሚለው ውሸት ነው።

ቅጥፈት 2: የእስራኤል ጠ/ሚ በሳውዲ ጉብኝት አድርጎ ከሙሀመድ ቢን ሰልማን ጋር ተወያይቷል የሚለው ቅጥፈት ነው

t.me//tewhidandmanner






ከአማራ ቴሌቪዥን ማታ የተከታተልኩት ነውር

በአማራ ላይ የተነሱ ጠላቶችና የተደረጉ ወረራዎች
1)ግራኝ(የግራኝ ወረራ)
2)የግራኝ ወረራን ተከትሎ የተደረገው(አቅራቢው በግልፅ ስሙን ባይጠቅሰውም ምን ለማለት እንደፈለገ ታሪክ ያሸተተ ሁሉ በቀላሉ የሚያውቀው ነው)
3)የጣሊያን ወረራ
4)የህዋሃት ወረራ

ልብ በሉ የመንግስት ሚዲያ ነኝ እያለ የአማራ ሙስሊም በሚከፍለው ግብር እየሰራ ኢማም አህመድን ወራሪና የአማራ ጠላት አድርጎ አስቀምጦታል።በስሙ እንኳ ለመጥራትም አልወደደም።

ኢማም አህመድ ከሱ በኋላ የመጡ መሪዎች ያጠበቧትን ኢትዮጵያ አስፍቶ የመራ ጀግና ነው። ሀይማኖቱን መሰረት አድርገህ ልታኮስሰው ብትሞክር የምትኮስሰው አንተ ነህ!
በዚህ የሚሸማቀቅ ሙስሊም ሊኖር አይችልም።




ትዝብት

ስለአንድነት ማውራት ገሪብ እስኪመስል ድረስ ድንገት በደርስ መሀል ስለአንድነት የሚያወራ አንቀፅ ከመጣ ስለአንድነት እንዲሁ ማውራት እየተቻለ አብሮ ስለልዩነት ካላወራ የሚያቅበዘብዘው ሰው በአካል አይቸ ታዝቤያለሁ። የአንድነትን ርእስ ለኢኽዋን አሳልፈን የሰጠነው ራሳችን ነን። እስቲ ምን ያህል ሙሀደራ ስለአንድነት ተደርጓል? ይችን ያዳምጡ

https://t.me/abujunaidposts/132


እየተዋጉ ያሉት በሀገር ውስጥ ያሉ ታጣቂ ሀይሎች ብቻ አይደሉም።ውጊያው ከሀገር ውጭም ቀጥሏል።ይሄን ውጊያ ግን ለየት የሚያደርገው የትጥቅ ትግል ሳይሆን የሀሳብና የዲፕሎማሲ መሆኑ ነው።ለዚህ ማሳያ ካነበብኳቸው ትቂት ልቀንጭብላችሁ

በአልጀዚራ ላይ ረጅም ፅሁፍ የፃፈው የህግ ምሁር ዶክተር አወል አሎ ጦርነቱ የፌደራል አቀንቃኝ የሆነውን የትግራይ አስተዳደር(ቲ ፒ ኤል ኤፍን) የማንበርከክ የሀይል ጦርነት እንደሆነ ያትታል። ከዚህ በፊት በወላይታ፣ በሲዳማ እና በሌሎች ቦታዎች ላይ ከተወሰደው መሰል የሀይል እርምጃ የቀጠለ ነው ይላል። በጥቅሉ ጦርነቱ ህግ የማስከበር ሳይሆን ፌደራሊዝምን የመደፍጠጥ ህገወጥ እርምጃ ነው ይላል።

How Abiy Ahmed’s Ethiopia-first nationalism led to civil war"
The war in Tigray is a continuation of the violent and widespread repression Abiy began in Oromia, Walaita and Sidama against those who resisted his vision of the future.
At the heart of the current civil war and the political upheavals that rocked the country since Abiy’s rise to power are two radically contrasting and seemingly irreconcilable visions of the future. On the one hand is Abiy’s vision of a centralised and unitary state in which the centre determines the political, economic, and cultural policies of the periphery. On the other hand is a vision represented by the TPLF, the Oromo opposition camp and other nations and nationalities in the south of the country, of an Ethiopia in which political authority is constitutionally divided between the central government and autonomous regional governments responsible for determining policies central to their political, economic, and cultural futures.(Awol Allo, 25 Nov 2020, Aljazeera)

በሌላ በኩል ፎሬይን ፓሊሲ በተባለው አሜሪካ ውስጥ በሚታተም መፅሄት ላይ ፅሁፉን ያሰፈረው ካሳሁን መለሰ የተባለ ምሁር ጦርነቱ የህዋሃትን የኢኮኖሚ የበላይነት ለመድፈቅ የተደረገ የኢኮኖሚ ትግል እንጅ በፌደራሊስትና አሃዳውያን መካከል የተፈጠረ የፓለቲካ አይዲዮሎጅ ጦርነት አይደለም ይላል። ለዚህም ማሳያ የፌደራል ስርአቱ በአብይ አስተዳደር እንደተጠበቀ ነው የሚለውን መከራከሪያ ያነሳል።

Tigray’s War Against Ethiopia Isn’t About Autonomy. It’s About Economic Power."
It is clear that the current conflict is not over who gets to govern Tigray because the postponement of national and regional elections extended the tenure of the legislative and executive branches of all regional governments in the country, including in Tigray, which is still ruled by the TPLF. Nor is it a clash between federalists and unitarists; Ethiopia’s federal system remains intact".(kasahun Melese, 19 Nov 2020, Foreign Policy)




ስፓኒሽ ፍሉ ጥሎት ያለፈው ቆሻሻ የማቃጠል እና የማጠን ባህል

ልክ ዛሬ ህዳር 12 ቀን፣ ነገር ግን በ1911 ዓ.ም በአዲስ አበባ የህዳር በሽታ እጅግ የበዛ ሰው ገደለ። በዚህ ምክንያት ዛሬም ድረስ ህዳር 12 ቀን ሲመጣ ከማለዳ ጀምሮ፤ አዲስ አበባ በጭስ ትታጠናለች። ሁሉም ከየቤቱ ቆሻሻ አውጥቶ ያቃጥላል። ይህ የህዳር 12 ባህል ከመቶ አመት በላይ ሆነ። በዚህ ቀን በአዲስ አበባ እዚህም እዚያም ጭስ ስለሚታይ፤ ብዙዎች “ህዳር ታጠነ” በሚል ያልፉታል። ለመሆኑ ከዚህ የህዳር በሽታ ጀርባ ምን ታሪክ አለ?
ነገሩ እንዲህ ነው። ይህ የህዳር በሽታ በአንደኛው የአለም ጦርነት ወቅት፤ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎች ሞተዋል። በሽታው እንደጉንፋን አድርጎ በሳል ይጀምርና በሽተኛው ላይ ከፍ ያለ ትኩሳት ያወርድበት ነበር። የሰውነት ውጋት እና ቁርጥማትም የበሽታው ምልክቶች ነበሩ። ምናልባት አሁን በመላው አለም ከተዛመተው የኮቪድ 19 ጋር የሚያመሳስለው ምልክት በዛ ያለ በመሆኑ፤ “ኮሮና ድሮም ነበር እንዴ?” ያስብላል። የሆኖ ሆኖ ብዙዎች ይህን በሽታ ግሪፕ ይሉታል። ሌሎች ደግሞ ስፓኒሽ ፍሉ ይሉታል።
በመላው አለም በዚህ የህዳር በሽታ ምክንያት 50 ሚሊዮን ሰው ሞተ። በመላው አለም ከሚገኙት ህዝቦች 1/3ኛው በዚህ በሽታ ተጠቅቶ፤ መልሶ አገገመ። በኢትዮጵያም በህዳር በሽታ ምክንያት በአዲስ አበባ ውስጥ ብቻ አርባ ሺህ ሰው ሞተ። ይህም የቀብር ስርአት የተደረገላቸውን እንጂ፤ በየቦታው ሳይቀበሩ የቀሩትን አይጨምርም። በዚህ የህዳር በሽታ ምክንያት በአንድ ቤት ውስጥ የሚገኙ እናት አባት፤ ልጆች ጭምር አብረው ሞተው ይገኙ ነበር። በብዙ ቦታዎች የአዲስ አበባ ሟች የሚቀብረው ሰው ጠፍቶ፤ አውሬ ይበላው ጀመር። መቃብር ቆፋሪ ብቻ ሳይሆን ሬሳ ተሸክሞ የሚወስድ ሰው ጠፋ። በአንድ መቃብር ውስጥ ሁለት እና ሶስት ሰዎች ይቀበሩም ነበር።
ይህ በሽታ በንፋስ መጣ ተብሎ ስለሚታመን በወቅቱ የነበሩ አዋቂዎች የንፋስ ቸነፈር ብለው ይጠሩታል። በሽታው በሸዋ እና በሌሎች አካባቢዎች ተዛምቶ ስለነበር፤ በኦሮምኛ “ዱኩባ ቂሌንሳ” ወይም የንፋስ በሽታ የሚል ስም ተሰጥቶት ነበር። በዚያን መጥፎ ዘመን… ከታዋቂ ሰዎች መካከል የአዲስ አበባ ከንቲባ የነበሩት ወሰኔ ዛማኔል ህዳር 12 ቀን ሞተ… አዲስ አበባ ያለመንግስት ቀረች። ከሶስት ወራት በኋላ ግን ነገሮች እየተሻሻሉ መጥተው፤ ለአዲስ አበባም ቀኛዝማች ማተቤ አዲስ ከንቲባ ሆነው ተሾሙ -1911። ከዚያ በኋላ በየ አመቱ ህዳር ሲመጣ አዲስ አበባ ትታጠን ጀመር። ከህዳር ውስጥ ደግሞ …በተለይ ህዳር 12 ቀን ተመርጦ ቆሻሻ ይቃጠልበት ጀመር። ቆሻሻ የማቃጠሉ ባህል በአዲስ አበቤዎች ዘንድከአንድ መቶ አመታት በላይ ቆየ - እነሆ ባህልም ሆነ።

ዳዊት ከበደ ወየሳ




ሀይማኖታዊ ፓለቲካ በመረጃ ቲቪ

መረጃ ቲቪ ሀይማኖታዊ ፖለቲካን በመስበክ እና ፀረሙስሊም ትርክት በመሰስተጋባት የታወቀ ህገወጥ ቲቪ ነው። ህገወጥነቱን የብሮድካስት ባለስልጣን በቅርቡ ይፋ አድርጓል።

ሆኖም በእንቅርት ላይ ጀሮ ደግፍ እንዲሉ ዘመድኩን በቀለን በመጋበዝ ለሳተላይት ክፍያ የሚሆን የገንዘብ መዋጮ በጎ ፈንድ ሚ አካሂዷል ።

ዘመድኩን ለሽብር የሚቀሰቅስ አሃዳዊ ሜንታሊቲ የተጠናወተው እና ኢስላሞፎቢክ ግለሰብ ነው ። ይህ ፅንፈኛ ሰው እነሀብታሙ አያሌውና ኤርሚያስ ለገሰ በሚቀርቡበት መረጃ ቲቪ ላይቭ ገብቶ ከስር የምታዩትን ምስል ይዞ ገንዘብ እያሰባሰበ ነው።

ድሮ ያለፍነው አሃዳዊዩ ሀይማኖታዊ ፓለቲካ ጥርሱን አግጥጦ መጣ ማለት ነው።




ድንበር ማለፍን(ኢፍራጥ) እና የአቋም መውረድን(ተፍሪጥን) የምትለካው በሰዎች ማንነት ሳይሆን በመርህ መሆን አለበት

"እነእከሌ ድንበር አልፈዋል እኔ ደግሞ እንደነሱ አይደለሁም ስለዚህ ድንበር አላለፍኩም አትበል። ምናልባት እነሱ ድንበር ያለፉት ሀያ ሜትር ያህል ሊሆን ይችላል።አንተ ደግሞ አስራአምስት ሜትር ላይ ቆመህ ሊሆን ይችላል። ሁሉም ድንበር ማለፍ ነው።"

እነከሌ ተንሸራተቱ ምናምን ከማለትህ በፊት አንተ ስንት ሜትር ከፍታ ላይ እንዳለህ መርምር።

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.

340

obunachilar
Kanal statistikasi