በወረታ ከተማ በተደረገ ኦፕሬሽን ውጤታማ ተግባር መከናወኑን የወረታ ከተማ አስተዳደር ሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት አስታወቀ።
በወረታ ከተማ አስተዳደር ስር በሚገኘው ቋሃር ሚካኤል በተባለ የገጠር ቀበሌ ውስጥ በዛሬው ዕለት ማለትም ጥር 27/2017 ዓ.ም እረፋድ ላይ በነበረው የሰላም ማስከበር ኦኘሬሽን በፅንፈኛው ላይ የተሳካ ኦፕሬሽን መደረጉን የወረታ ከተማ አስተዳደር ሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት አስታውቋል።
የመንግስት ታጣቂ ኃይሎች በወሰዱት የጸጥታ ማስከበር ኦኘሬሽን እርምጃ ላይ 5 የፅንፈኛ ቡድን መደምሰሱንና 8 የጠላት ቡድን ደግሞ መቁሰሉን እንዲሁም 1 ብሬንና 4 ክላሽ የጦር መሣሪያዎች መማረካቸውን ጽ/ቤቱ ገልጿል።
በተደረገው ኦኘሬሽን ላይ ከመንግስት ጸጥታ አስከባሪና ታጣቂ ኃይሎች ላይ ምንም አይነት ጉዳት አለመድረሱንና ይህም ድል የተገኘው በተደራጀና በተቀናጀ የመረጃ መዋቅር ፣በወረታ ከተማ አስተዳደር ጸጥታ አስከባሪ ኃይሎችና አድማ ብተና እንዲሁም በፎገራ ወረዳ አጋዥ አድማ ብተናና የጸጥታ ኃይሎች አማካኝነት መሆኑን በጽ/ቤቱ ጨምሮ ገልጿል።
መረጃው፦የወረታ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ኮሙኒኬን ነው።
በወረታ ከተማ አስተዳደር ስር በሚገኘው ቋሃር ሚካኤል በተባለ የገጠር ቀበሌ ውስጥ በዛሬው ዕለት ማለትም ጥር 27/2017 ዓ.ም እረፋድ ላይ በነበረው የሰላም ማስከበር ኦኘሬሽን በፅንፈኛው ላይ የተሳካ ኦፕሬሽን መደረጉን የወረታ ከተማ አስተዳደር ሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት አስታውቋል።
የመንግስት ታጣቂ ኃይሎች በወሰዱት የጸጥታ ማስከበር ኦኘሬሽን እርምጃ ላይ 5 የፅንፈኛ ቡድን መደምሰሱንና 8 የጠላት ቡድን ደግሞ መቁሰሉን እንዲሁም 1 ብሬንና 4 ክላሽ የጦር መሣሪያዎች መማረካቸውን ጽ/ቤቱ ገልጿል።
በተደረገው ኦኘሬሽን ላይ ከመንግስት ጸጥታ አስከባሪና ታጣቂ ኃይሎች ላይ ምንም አይነት ጉዳት አለመድረሱንና ይህም ድል የተገኘው በተደራጀና በተቀናጀ የመረጃ መዋቅር ፣በወረታ ከተማ አስተዳደር ጸጥታ አስከባሪ ኃይሎችና አድማ ብተና እንዲሁም በፎገራ ወረዳ አጋዥ አድማ ብተናና የጸጥታ ኃይሎች አማካኝነት መሆኑን በጽ/ቤቱ ጨምሮ ገልጿል።
መረጃው፦የወረታ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ኮሙኒኬን ነው።