የተሻለ ፖሊሳዊ ስነ ምግባር የተላበሱ ብቁ የፖሊስ አባላትን ለማፍራት በጋራ መስራት ይገባል ተባለ።
የካቲት 25/2017 ዓ.ም
በብርሸለቆ መሠረታዊ ዉትድርና ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት የአማራ ፖሊስ ኮሌጅ እያሰለጠነ ባለው የ33ኛ ዙር የመደበኛና አድማ መከላከል ምልምል ፖሊስ ሰልጣኞች ላይ አጠቃላይ ከሰው ሀይል ምልመላና መረጣ የስልጠና ሂደትና በቀጣይ በዉህደት ተግባራት ዙሪያ በተዘጋጀው የዳሰሳ ፅሑፍ መነሻ ውይይት ተደርጓል።
የአማራ ፖሊስ ኮሌጅ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ኮማንደር አብይወት ሽፈራው እንዳሉት በእዉቀቱ፣ በአመለካከትና በክህሎቱ ጠንካራ የፖሊስ አመራርና አባላት በማፍራት ዙሪያ ወደፊት መደረግ ባለባቸው ተግባራት ጉዳይ በርካታ ጠቃሚ ሀሳቦች መነሳታቸውን ገልፀዋል። በቀጣይም ጥራት ያለው ትምህርትና ስልጠና ለመስጠት ትልቅ ተሞክሮ እንደሚሆን ኮማንደር አብይወት ገልፀዋል።
አስተያየታቸዉን የሰጡን የዉይይቱ ተሳታፊዎች የተነሱት ሀሳቦች ጠንካራ የፖሊስ ተቋም ለመገንባት በህዝብ ቅቡሉነት ያለዉና በስልጠና ሂደቱም ጠንካራ የአመራር ቁጥጥርና ድጋፍ መኖር ለሰልጠናው ከፍተኛ አሰተዋጽኦ አበርክቷል በተለይም ስልጠና ወሰደው ምደባ የሚደረግላቸው አባላት ከምድብ ቦታቸው ከደረሱ በኀላ ያለው አቀባበል እና ከነባር የሠው ሀይልና ማህበረሰቡ እንዲሁም አጋር አካላት ጋር ትውውቅ ምቹ የስራ አካባቢ መፍጠር ከተቻለ በተደራጀ ዕቅድ ከተመራ ውጤታማና የሚጠበቀውን ግብ ያሳካ ተግባር መስራትና የሚሠጣቸውን ግዳጅ መፈጸም የሚችል ሰራዊት ለመፍጠር የጎላ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ብለዋል።
ዘገባው ፦የአማራ ፖሊስ ኮሌጅ የህዝብ ግኑኝነት ክፍል ነው።
ከብርሸለቆ
የካቲት 25/2017 ዓ.ም
በብርሸለቆ መሠረታዊ ዉትድርና ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት የአማራ ፖሊስ ኮሌጅ እያሰለጠነ ባለው የ33ኛ ዙር የመደበኛና አድማ መከላከል ምልምል ፖሊስ ሰልጣኞች ላይ አጠቃላይ ከሰው ሀይል ምልመላና መረጣ የስልጠና ሂደትና በቀጣይ በዉህደት ተግባራት ዙሪያ በተዘጋጀው የዳሰሳ ፅሑፍ መነሻ ውይይት ተደርጓል።
የአማራ ፖሊስ ኮሌጅ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ኮማንደር አብይወት ሽፈራው እንዳሉት በእዉቀቱ፣ በአመለካከትና በክህሎቱ ጠንካራ የፖሊስ አመራርና አባላት በማፍራት ዙሪያ ወደፊት መደረግ ባለባቸው ተግባራት ጉዳይ በርካታ ጠቃሚ ሀሳቦች መነሳታቸውን ገልፀዋል። በቀጣይም ጥራት ያለው ትምህርትና ስልጠና ለመስጠት ትልቅ ተሞክሮ እንደሚሆን ኮማንደር አብይወት ገልፀዋል።
አስተያየታቸዉን የሰጡን የዉይይቱ ተሳታፊዎች የተነሱት ሀሳቦች ጠንካራ የፖሊስ ተቋም ለመገንባት በህዝብ ቅቡሉነት ያለዉና በስልጠና ሂደቱም ጠንካራ የአመራር ቁጥጥርና ድጋፍ መኖር ለሰልጠናው ከፍተኛ አሰተዋጽኦ አበርክቷል በተለይም ስልጠና ወሰደው ምደባ የሚደረግላቸው አባላት ከምድብ ቦታቸው ከደረሱ በኀላ ያለው አቀባበል እና ከነባር የሠው ሀይልና ማህበረሰቡ እንዲሁም አጋር አካላት ጋር ትውውቅ ምቹ የስራ አካባቢ መፍጠር ከተቻለ በተደራጀ ዕቅድ ከተመራ ውጤታማና የሚጠበቀውን ግብ ያሳካ ተግባር መስራትና የሚሠጣቸውን ግዳጅ መፈጸም የሚችል ሰራዊት ለመፍጠር የጎላ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ብለዋል።
ዘገባው ፦የአማራ ፖሊስ ኮሌጅ የህዝብ ግኑኝነት ክፍል ነው።
ከብርሸለቆ