የእምነት ጥበብ dan repost
ለቅባቶች አድርሱልኝ የሰው ልጅ ተፈጥሮ በTheophilus of Antioch, Theophilus to Autolycus
አንድ ሰው ደግሞ፣ “ሰው የተፈጠረው ሟች ሆኖ ነው?” ብሎ ሊጠይቅ ይችላል። በፍጹም እንደዚያ አይደለም። “እንግዲውስ የማይሞት ነበር?” የሚለውንም አንቀበልም። “ታዲያ ምንም አልነበረም ማለት ነው?” የሚለውስ? ይሄም አይሆንም።ሰው ሲፈጠር ሟችም፣ የማይሞትም አልነበረም። ከመጀመሪያውኑ የማይሞት አድርጎት ቢፈጥረው፣ አምላክ ይሆን ነበር። ሟች አድርጎት ቢፈጥረው ደግሞ፣ እግዚአብሔር የሞቱ ምክንያት ይመስል ነበር። ስለዚህ፣ እግዚአብሔር ሰውን ሟችም የማይሞትም አድርጎ አልፈጠረውም። ይልቁንስ፣ ለሞትም ለሕይወትም የሚሆን አድርጎ ነው የፈጠረው። የእግዚአብሔርን ትእዛዝ ጠብቆ ወደ ዘላለም ሕይወት ቢመራ፣ የማይሞት ሕይወት ተሰጥቶት እንደ አምላክ ይሆን ነበር። ነገር ግን እግዚአብሔርን ሳያከብርና ወደ ሞት ቢሄድ፣ የራሱ ሞት ምክንያት ይሆን ነበር። እግዚአብሔር ሰውን ነፃና በራሱ ላይ ሥልጣን ያለው አድርጎ ፈጥሮታል። ሰው ባለመታዘዝ በራሱ ላይ ያመጣውን ሞት፣ እግዚአብሔር አሁን በምሕረቱና በቸርነቱ፣ ሰዎች ሲታዘዙት እንደ ስጦታ ይሰጣቸዋል። ሰው ባለመታዘዝ ሞትን ወደ ራሱ እንዳመጣ፤ በተመሳሳይ፣ የእግዚአብሔርን ፈቃድ የሚታዘዝ ሁሉ የዘላለም ሕይወት ሊያገኝ ይችላል። እግዚአብሔር ሕግና ትእዛዝ ሰጥቶናል፤ ይህን የሚጠብቅ ይድናል፣ ከሞት ተነስቶም የማይጠፋ ሕይወት ይወርሳል።
https://t.me/WisdomOfTheFaith
አንድ ሰው ደግሞ፣ “ሰው የተፈጠረው ሟች ሆኖ ነው?” ብሎ ሊጠይቅ ይችላል። በፍጹም እንደዚያ አይደለም። “እንግዲውስ የማይሞት ነበር?” የሚለውንም አንቀበልም። “ታዲያ ምንም አልነበረም ማለት ነው?” የሚለውስ? ይሄም አይሆንም።ሰው ሲፈጠር ሟችም፣ የማይሞትም አልነበረም። ከመጀመሪያውኑ የማይሞት አድርጎት ቢፈጥረው፣ አምላክ ይሆን ነበር። ሟች አድርጎት ቢፈጥረው ደግሞ፣ እግዚአብሔር የሞቱ ምክንያት ይመስል ነበር። ስለዚህ፣ እግዚአብሔር ሰውን ሟችም የማይሞትም አድርጎ አልፈጠረውም። ይልቁንስ፣ ለሞትም ለሕይወትም የሚሆን አድርጎ ነው የፈጠረው። የእግዚአብሔርን ትእዛዝ ጠብቆ ወደ ዘላለም ሕይወት ቢመራ፣ የማይሞት ሕይወት ተሰጥቶት እንደ አምላክ ይሆን ነበር። ነገር ግን እግዚአብሔርን ሳያከብርና ወደ ሞት ቢሄድ፣ የራሱ ሞት ምክንያት ይሆን ነበር። እግዚአብሔር ሰውን ነፃና በራሱ ላይ ሥልጣን ያለው አድርጎ ፈጥሮታል። ሰው ባለመታዘዝ በራሱ ላይ ያመጣውን ሞት፣ እግዚአብሔር አሁን በምሕረቱና በቸርነቱ፣ ሰዎች ሲታዘዙት እንደ ስጦታ ይሰጣቸዋል። ሰው ባለመታዘዝ ሞትን ወደ ራሱ እንዳመጣ፤ በተመሳሳይ፣ የእግዚአብሔርን ፈቃድ የሚታዘዝ ሁሉ የዘላለም ሕይወት ሊያገኝ ይችላል። እግዚአብሔር ሕግና ትእዛዝ ሰጥቶናል፤ ይህን የሚጠብቅ ይድናል፣ ከሞት ተነስቶም የማይጠፋ ሕይወት ይወርሳል።
https://t.me/WisdomOfTheFaith