Bule Hora University


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha
Toifa: Ta’lim


Bule Hora University Official telegram

Связанные каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Statistika
Postlar filtri


ክፍት የስራ ማስታወቂያ (ለውስጥ )


New Doc 03-28-2024 18.58


ሴቶችን እናብቃ፣ ሰላምና ልማትን እናረጋግጥ "በሚል መሪ ቃል ለ48 ጊዜ በኢትዮጵያ የሚከበረውን የአለም የሴቶች ቀን በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲም ነገ በ06/07/2016ዓ.ም ይከበራል። ሁላችሁም እንድተገኙ ተጋብዛችኋል።


የካቲት 24/2016 ዓ.ም
የሃዘን መግለጫ
ወይዘሮ መሰረት አለሙ ከእናቷዋ ከወይዘሮ ጣይቱ ቢሎ እንዲሁም ከአባቱዋ ከአቶ አለሙ በዳሶ በ1980 ዓ.ም በምዕራብ ጉጂ ዞን በቡሌ ሆራ ወረዳ በሙሪ ቱርቁማ ቀበሌ ተወለዱ። ወይዘሮ መሰረት አለሙ እስከ ህልፈተ ህይወታቸው ድረስ በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ በላይብረሪና ዲክመንቴሽን ዳይሬክቶሬት ክፍል ውስጥ አቴንዳንት በመሆን በታማኝነትና በቅንነት ያገለገሉ ሲሆን፣ ባደረባቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው ትላንት የካቲት 23/2016 ዓ.ም ከዚህ አለም በሞት ተለይተዋል።
የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ በወ/ሮ መሰረት ሞት የተሰማውን ሀዘን እየገለፀ ለመላው የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ፣ ለወላጅ ዘመድ እንዲሁም ለጓደኞቿ መጽናናትን ይመኛል።

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ


የካቲት 24/2016 ዓ.ም

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ አዲስ የቦርድ ሰብሳቢ ሆነው ከተሾሙት ዶ/ር ከይረዲን ተዘራ ጋር የትውውቅ ሥነ-ሥርዓት ተካሄደ፡፡

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ በመንግስት የተሠጠውን አዋጅ ተከትሎ ማናቸውንም በዩኒቨርሲቲው የሚከናወኑ ተግባራትን በቦርድ አፅድቆ እያከናወነ ይገኛል፡፡ በመሆኑም ቀደም ሲል የዩኒቨርሲቲው ቦርድ ሰብሳቢ ሆነው ሲያገለግሉ የነበሩት ዶ/ር ስዩም መስፍን በመልቀቃቸው ምክንያት በምትክ የዩኒቨርሲቲው ቦርድ ሰብሳቢ ሆነው ከተሾሙት የሠላም ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ከይረዲን ተዘራ ጋር አዲስ አበባ ካፒታል ሆቴል ስብሰባ አዳራሽ ከቦርድ አባላትና ከዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች ጋር የትውውቅ ሥነ-ሥርዓት ተከናዉኗል፡፡

የትውውቅ ስነ-ሥርዓት ከተካሄደ በኃላ የዩኒቨርሲቲው የ2016 ዓ.ም የግማሽ ዓመት የሥራ ክንውን ሪፖርት በዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶ/ር ብርሃኑ ለማ አማካኝነት ቀርቦ ውይይት የተደረገ ሲሆን በዋናነትም የመማር ማስተማሩን ተግባር ጨምሮ በማህብረሰብ አገልግሎት፣በጥናትና ምርምር፣ በመልካም አስተዳደርና በአለም አቀፋዊነት ዙሪያ በስፋት ውይይት ተደርጓል:: የቦርዱ ሰብሳቢ ዶ/ር ከይረድን ተዘራም ቀጣይ ሥራዎች ተጠናክሮ በሚቀጥሉበት ሁኔታ ላይ የሥራ መመሪያ ሰጥቷል፡፡

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ


የካቲት 19/2016 ዓ.ም

የ2016 ዓ.ም በጀት ዓመት የቀሪ ስድስት ወራት በተከለሰው ዕቅድ ዙሪያ ውይይት ተደረገ።

ዩኒቨርሲቲው በቅርብ ጊዜ የ2016 ዓ.ም የግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ በማካሄድ በቀጣይ ስድስት ወራት ትኩረት ተሰጥቶ መከናወን ባለባቸዉ ሥራዎች ዙሪያ አቅጣጫ ማስቀመጡን መዘገባችን ይታወሳል፡፡

በተቀመጠው አቅጣጫ መሠረት ራሱን የቻለ ኮሚቴ ተዋቅሮ ከባለፈው ዕቅድ ግምገማ በመነሳት በቀጣይ ትኩረት ተሰጥቶ መከናወን ባለባቸው ሥራዎች ዙሪያ ዕቅዱን ክለሳ በማድረግ የበለጠ ላማዳበር ለውይይት የቀረበ ስለመሆኑ የዕቅድና በጀት ክትትል ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ መሰለ አለማየሁ ተናግሯል፡፡ የዕቅድ ክለሳው የተቋሙን ነባራዊ ሁኔታ በቅድሚያ የዳሰሰ እና በዋናነት የመማር ማስተማሩን ተግባር ማዕከል በማድረግ ከበጀት ጋር በሚጣጣም መልኩ በዋና ዋና ግቦችና ስትራቴጅክ ዓላማዎች ተዘርዝሮ የቀረበ መሆኑንም ዳይሬክተሩ ተናግረዋል፡፡

አቶ መሠለ አያይዘውም ተከልሶ የቀረበው ዕቅድ አዲሱን የሰው ኃይል ምደባና የሥራ ዘርፎችን ታሳቢ በማድረግ የተዘጋጀ መሆኑንና እያንዳንዱን የሥራ ክፍልም ያካተተ ስለመሆኑ አስረድተዋል፡፡
በውይይቱ ላይ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶ/ር ብርሃኑ ለማ ተገኝተው በቀሪ ወራት ትኩረት ተደርጎ መሠራት ባለባቸው ሥራዎች ዙሪያ ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን በአዲሱ የሰው ኃይል ምደባ መሠረት በሥራ አስፈፃሚ መደብ ላይ ተወዳድረው ያለፉ ኃላፊዎችም ተሣታፊ ሆነዋል፡፡

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ


የካቲት 19/2016 ዓ.ም

ማስታወቂያ
በተለያዩ የሃላፊነት ቦታዎች ላይ ያመለከታችሁ የአካዳሚክ ዘርፍ አመልካቾች በሙሉ
ነገ የካቲት 20/2016 ዓ.ም ከሰዓት 8:00 ሰዓት ላይ ሰኔት አዳራሽ እንድትገኙ እናሳስባለን::

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ


የመውጫ ፈተና(Exit Exam) ውጤት በተመለከተ

በ2016 ዓ.ም ዓመት የመውጫ ፈተና የወሰዳችሁ ተማሪዎች ውጤታችሁን ለማየት ከታች ያለውን ሊንክ ተጠቀሙ፦

https://result.ethernet.edu.et/


February 20/2014

Bule Hora University hosts University of Venda delegation

Bule Hora University received a delegation of 20 higher officials and students from the University of Venda in South Africa on February 20, 2024. The visit was part of a Memorandum of Understanding (MOU) signed between the two universities to collaborate on various academic and research issues.

The Bule Hora University president, Dr. Birhanu Lema, the Vice President of Academic, Research, Technology Transfer and Community Service, Dr. Tinsae Tamrat, and other staff members welcomed the Venda team at Hawassa Airport.

The Internationalization Directorate of BHU said that the University Of Venda delegation arrived at a special time, as they would witness the 75th power transfer of the Gujii Oromoo Gadaa Baallii, Indigenous Oromo Democratic governance sytem.
The Directorate also said that they looked forward to exchanging experiences and knowledge with the BHU students and leaders during their stay.

Bule Hora University


05/06/2016 E.C
For Exit Exam Examinees

Bule Hora University


የካቲት 02/2016 ዓ.ም

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የተለያዩ ሰብሎችን ለመዝራት የእርሻ ሥራ ጀምሯል፡፡

ዩኒቨርሲቲው ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የተሻሻሉ የግብርና የእርሻ መሣሪያዎችን እና ግብዓቶችን በመጠቀም ሥራዎችን አጠናክሮ እየሰራ መሆኑ ይታወሳል፡፡ በተመሳሳይ መልኩ በ2016 ዓ.ም ይህንኑ በስፋት በመቀጠል ስንዴና ሌሎች ሰብሎችን ለመዝራት የዩኒቨርሲቲዉ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ብርሃኑ ለማ እና የግብርና ልማት ማዕከል ኃላፊ መ/ር ሀሮ አዱላ በተገኙበት የእርሻ ሥራው ተጀምሯል፡፡

ዩኒቨርሲቲው የልህቀት ማዕከል አድርጎ ከሚሰራባቸው ተግባራት አንዱ ግብርና መሆኑን የጠቀሱት ዶ/ር ብርሃኑ ለማ በአሁኑ ሰዓት የተጀመረው የእርሻ ሥራ ለመማር ማስተማሩ እንደ ምርምር ማዕከል ሆኖ ከማገልገሉም በላይ እየታየ ያለውን የዋጋ ንረት ከመቀነስና በተለይም መንግስት የስንዴ አቅርቦትን በሀገር ዉስጥ አምራቾች ብቻ ለመሸፈን እያደረገ ያለውን ጥረት የሚደግፍ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ




ጥር 29/2016 ዓ.ም

75ኛውን የጉጂ ጋዳ ባሊ ሥልጣን ርክክብን አስመልክቶ እየተከናወኑ ባሉ ሥራዎች ዙሪያ የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ብርሃኑ ለማ መግለጫ ሰጥቷል፡፡

ዩኒቨርሲቲው የልህቀት ማዕከል አደርጎ ከሚሠራባቸው ሥራዎች አንዱ በሀገር በቀል ዕውቀት ላይ መሆኑን እና ለዚሁም ሥርዓተ ትምህርት ተቀርፆ የባህል እና የጋዳ ሥርዓት ጥናት ኢንስቲትዩት በመክፈት ተማሪዎችን ከመጀመሪያ ድግሪ ጀምሮ እስከ ሦስተኛ ድግሪ ድረስ የማስተማር ሥራውን እያከናወነ መሆኑን በመግለጽ የጀመሩት ፕሬዝዳንቱ በየስምንት ዓመቱ የሥልጣን ሽግግር ሲደረግበት ቆይቶ ለ75ኛ ጊዜ መጪው የካቲት ወር የሥልጣን ርክክብ የሚደረግበትን የጋዳ ባሊ ሥርዓት ጋር ተያይዞ በዩኒቨርሲቲ ደረጃ በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡

የሥልጣን ርክክቡ ሠላማዊ በሆነ መልኩ እንዲከናወን ቅድሚያ የሚሠሩ ሥራዎችን በተቀናጀ መልኩ መምራት እንዲቻል የዩኒቨርሲቲው የከፍተኛ አመራሩ ጭምር ያሉበት ኮሚቴ ተዋቅሮ የተለያዩ ተግባራት እያከናወኑ መሆኑን ያነሱ ሲሆን ከነዚህም መካከል ‹‹የጋዳ ሣምንት›› በሚል ስያሜ የጋዳ ዋንጫ የእግር ኳስ ጨዋታ በተማሪዎች  መካከል መደረጉንና እጅግ ባማረ እና ደማቅ በሆነ ሁኔታ በተማሪዎች መካከል የልዩ ተስጥኦ የባህል ትዕይንቶች ውድደር ተደርጎ እርስ በእርስ የባህል ልውውጥና አንድነትን የሚያጠናክሩ ሥራዎች መሠራታቸውን ገልፀዋል፡፡
ፕሬዝዳንቱ አያይዘውም ለማከናወን እቅድ ከተያዙ አንዱ የሆነው የተለያዩ ምሁራን በተገኙበት የፓናል ውይይት ለማድረግ ሰፊ ዝግጅት መደረጉንና ለዚሁም ከሀገር ውስጥ ከሚመጡት ምሁራን በተጨማሪ ከደቡብ አፍሪካ ዩኒቨርሲቲዎች የተጋበዙ ምሁራን የተወሰኑ ተማሪዎችን ይዘው በመምጣት በፓናል ውይይቱ ላይ በመካፈል በሁለቱ ዩኒቨርሲቲዎች መካከል የልምድ ልውውጥ የሚካሄድ መሆኑን ያስረዱ ሲሆን ከዚህ በተጨማሪም የተዋቀረው ኮሚቴም ቀደም ብሎ ሥርዓቱ በሚከናወንበት ሚኤ ቦኮ በመገኘት ሁኔታዎችን የማመቻቸትና የማስተዋወቅ ሥራ የሚሠራ ስለመሆኑም ገልፀዋል፡፡

ፕሬዝዳንቱ በመጨረሻ ባስተላለፉት መልዕክት ሥርዓቱ በUNESCO በቅርስነት የተመዘገበ እንደ መሆኑ መጠን በርካታ እንግዶች ከሀገር ውስጥም ሆነ ከውጭ የሚገኙበት በመሆኑ እነዚህን እንግዶች ሥርዓቱን በሚመጥን መልኩ ለማስተናገድ እንዲቻል የሚመለከታቸው አካላት የድርሻቸውን እንዲወጡ ያሳሰቡ ሲሆን በቀጣይ በተጠናከረ ሁኔታ ዩኒቨርሲቲው ጋዳን ማዕከል ባደረገ መልኩ ሥራዎችን በስፋት ለመሥራት የተለያዩ ዶክመንተሪ ሥራዎችን ለማከናወን የፕሮፖዛል ዝግጅት መጠናቀቁንም ተናግረዋል::

በሌላ መልኩ የሥልጣን ሽግግሩን በሚመለከት እየተደረገ ባለው ዝግጅት ዙሪያ መግለጫ የሰጡት የባህልና ጋዳ ሥርዓት ጥናት ኢንስቲትዩት ዳይሬክተር መ/ር ሶራሌ ጅሎ የሥልጣን ሽግግሩ ሠላማዊ በሆነ ሁኔታ እንዲፈፀም ዳይሬክቶሬቱ ከዩኒቨርሲቲው የበላይ አመራሮች ጋር በመናበብ በርካታ ሥራዎችን እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ዳይሬክተሩ አያይዘውም የሥልጣን ርክክቡ ከመደረጉ በፊት ቅድሚያ የሚከናወኑ ተግባራት እንደተጠበቁ ሆነው ሥርዓቱ በሚፈፀምበት ቦታ ጭምር በመገኘት የሚከናወኑ ተግባራት በሙሉ ተሰንደዉ እና ዶክመንተሪ ተሰርቶ ለመማር ማስተማሩ ግብዓት እንዲሆኑ ጭምር በስፋት በዳይሬክቶሬቱ በኩል የሚከናወን ተግባር መሆኑንም አስረድተዋል፡፡

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ



14 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.