#ሃይማኖትና ምግባር
እግዚአብሔር አምላክ በመጻሕፍቱ እንደነገረን በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርሰቲያን ወደ መንግሥተ ሰማያት ለመግባት የሚያስፈልጉ ሁለቱ ዓቢይ ነገሮች ናቸው።
እነዚህም ሃይማኖትና ምግባር ናቸው። ይህም እምነትና መልካም ሥራ ማለት ነው።
ሃይማኖትና ምግባር _ በአንድ ላይ ካልተጣመሩ መዳን እይቻልም። ሃይማኖት ብቻውን ወይም ምግባር ብቻውን አያድንም።
ቅዱስ ያዕቆብ ይህን ሲገልጽ ሰይጣን ያምናል መልካም ሥራ ሰለሌለው አይድንም ብሎ ሁለቱ ካልተዋሓዱ ትርጉም አንደሚያጣ ተናግሯል።
“አጋንንት ደግሞ ያምናሉ ይንቀጠቀጡማል።" ያዕ ፪(2:19)
ስከዚህ በእምነት ብቻ እድናለሁ ብሎ ማሰብ ከእግዚአብሔር ቃል ውጪ ነው። ስለዚህ ነው ሐዋርያውም ጨምሮ በምሳሌ ሲያስተምረን፡-
“ከነፍስ የተለየ ሥጋ የሞተ እንደሆነ እንዲሁ ደግሞ ከሥራ የተለየ እምነት የሞተ ነው፡፡“ ያዕ ፪፡፳፮ (2፡26)
ስለዚህም ከአንድ ክርሰቲያን ምግባር ወይም በጎ ሥራ መሥራት ከሃይማኖት ጋር መንግሥተ ሰማያትን ለመውረስ የሚያበቃ ነው። በማቴዎስ ወንጌል እንደተጻፈ ጌታ ለፍርድ ሲመጣ የሚጠይቀው የምግባር ጥያቄ ነው።
ማቴ ፳፭ ፦ ፴፬ (25:34)። ጻድቃንም ሆኑ ኃጥአን በምድር የሚሠሩት ይከተላቸዋል።
“ሥራቸውም ይከተላቸዋል“ ራዕ ፲፬፡፲፫ (14፡13)
ይሀን ሳንረዳ በዕምነት ብቻ ወይም በጸጋው ብቻ እንድናለን ብለን በጎ ምግባርን ሳንፈጽም ብንቀር አስደንጋጭ የሆነ የጌታ ቃል በአኛ ላይ ተቃቷል ፡-
“በስማያት ያለውን የአባቴን ፈቃድ የሚያደርግ እንጂ ጌታ ሆይ ጌታ ሆይ የሚለኝ ሁሉ መንግሥተ ሰማያት የሚገባ አይደለም…..የዚያን ጊዜም ከቶ አላውቃችሁም እናንተ ዓመፀኞች ከእኔ ራቁ ብዬ እመስከርባቸዋለሁ።” ማቴ ፯፡፳፩-፳፫ (7:21-23)
”አሁንስ ምሳር ደግሞ በዛፎች ሥር ተቀምጧል እንግዲህ መልካም ፍሬ የማያደርግ ዛፍ ሁሉ ይቆረጣል ወደ እሳትም ይጣላል።”
ሉቃ ፫:፱ (3:9)
ይህ ሁሉ የወንጌል ቃል የሚመከረን ሃይማኖትን ከምግባር አስተባብረን በመያዝ ለመንግሥተ ሰማያት የበቃን እንሆን ዘንድ ነው። ምከንያቱም የከብር ጌታ ለሁሉ ሳያዳላ የሚፈርደው እንደ ሥራችን መጠን ነውና።
”አንተ ለእያንዳንዱ እንደ ሥራው ፍዳውን ትስጣለህና። " መዝ ፷፩፡ ፲፪ (61፡12)
“እነሆ በቶኰ አመጣለሁ ለእያንዳንዱም እንደ ሥራው መጠን እከፍል ዘንድ ዋጋዬ ከእኔ ጋር አለ።” ራዕ ፳፪፡፲፪(22:12)
”በጎ ሥራ የሚሠሩ ሰዎችን ግን እግዚአብሔር ከመከራው ሁሉ እንደ ጠበቀው እንደ ኢዮብ ባሮቹ ይሆኑ ዘንድ እግዚእብሔር በበጎ ሥራው ሁሉ ይጠብቃቸዋል።” ፩መቃ ፴፮፡፲፮ (36፡16)
ሃይማኖትና ምግባርን ይዘን በቀኙ ለመቆም ያብቃን።
አሜን!
@Deaconchernet
@Deaconchernet
@Deaconchernet
እግዚአብሔር አምላክ በመጻሕፍቱ እንደነገረን በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርሰቲያን ወደ መንግሥተ ሰማያት ለመግባት የሚያስፈልጉ ሁለቱ ዓቢይ ነገሮች ናቸው።
እነዚህም ሃይማኖትና ምግባር ናቸው። ይህም እምነትና መልካም ሥራ ማለት ነው።
ሃይማኖትና ምግባር _ በአንድ ላይ ካልተጣመሩ መዳን እይቻልም። ሃይማኖት ብቻውን ወይም ምግባር ብቻውን አያድንም።
ቅዱስ ያዕቆብ ይህን ሲገልጽ ሰይጣን ያምናል መልካም ሥራ ሰለሌለው አይድንም ብሎ ሁለቱ ካልተዋሓዱ ትርጉም አንደሚያጣ ተናግሯል።
“አጋንንት ደግሞ ያምናሉ ይንቀጠቀጡማል።" ያዕ ፪(2:19)
ስከዚህ በእምነት ብቻ እድናለሁ ብሎ ማሰብ ከእግዚአብሔር ቃል ውጪ ነው። ስለዚህ ነው ሐዋርያውም ጨምሮ በምሳሌ ሲያስተምረን፡-
“ከነፍስ የተለየ ሥጋ የሞተ እንደሆነ እንዲሁ ደግሞ ከሥራ የተለየ እምነት የሞተ ነው፡፡“ ያዕ ፪፡፳፮ (2፡26)
ስለዚህም ከአንድ ክርሰቲያን ምግባር ወይም በጎ ሥራ መሥራት ከሃይማኖት ጋር መንግሥተ ሰማያትን ለመውረስ የሚያበቃ ነው። በማቴዎስ ወንጌል እንደተጻፈ ጌታ ለፍርድ ሲመጣ የሚጠይቀው የምግባር ጥያቄ ነው።
ማቴ ፳፭ ፦ ፴፬ (25:34)። ጻድቃንም ሆኑ ኃጥአን በምድር የሚሠሩት ይከተላቸዋል።
“ሥራቸውም ይከተላቸዋል“ ራዕ ፲፬፡፲፫ (14፡13)
ይሀን ሳንረዳ በዕምነት ብቻ ወይም በጸጋው ብቻ እንድናለን ብለን በጎ ምግባርን ሳንፈጽም ብንቀር አስደንጋጭ የሆነ የጌታ ቃል በአኛ ላይ ተቃቷል ፡-
“በስማያት ያለውን የአባቴን ፈቃድ የሚያደርግ እንጂ ጌታ ሆይ ጌታ ሆይ የሚለኝ ሁሉ መንግሥተ ሰማያት የሚገባ አይደለም…..የዚያን ጊዜም ከቶ አላውቃችሁም እናንተ ዓመፀኞች ከእኔ ራቁ ብዬ እመስከርባቸዋለሁ።” ማቴ ፯፡፳፩-፳፫ (7:21-23)
”አሁንስ ምሳር ደግሞ በዛፎች ሥር ተቀምጧል እንግዲህ መልካም ፍሬ የማያደርግ ዛፍ ሁሉ ይቆረጣል ወደ እሳትም ይጣላል።”
ሉቃ ፫:፱ (3:9)
ይህ ሁሉ የወንጌል ቃል የሚመከረን ሃይማኖትን ከምግባር አስተባብረን በመያዝ ለመንግሥተ ሰማያት የበቃን እንሆን ዘንድ ነው። ምከንያቱም የከብር ጌታ ለሁሉ ሳያዳላ የሚፈርደው እንደ ሥራችን መጠን ነውና።
”አንተ ለእያንዳንዱ እንደ ሥራው ፍዳውን ትስጣለህና። " መዝ ፷፩፡ ፲፪ (61፡12)
“እነሆ በቶኰ አመጣለሁ ለእያንዳንዱም እንደ ሥራው መጠን እከፍል ዘንድ ዋጋዬ ከእኔ ጋር አለ።” ራዕ ፳፪፡፲፪(22:12)
”በጎ ሥራ የሚሠሩ ሰዎችን ግን እግዚአብሔር ከመከራው ሁሉ እንደ ጠበቀው እንደ ኢዮብ ባሮቹ ይሆኑ ዘንድ እግዚእብሔር በበጎ ሥራው ሁሉ ይጠብቃቸዋል።” ፩መቃ ፴፮፡፲፮ (36፡16)
ሃይማኖትና ምግባርን ይዘን በቀኙ ለመቆም ያብቃን።
አሜን!
@Deaconchernet
@Deaconchernet
@Deaconchernet