በሚቀጥሉት ወራት ለኢትዮጵያ ህዝብ ብስራቶች ይኖሩናል፦ የብልፅግና ፓርቲ ፕሬዚዳንት ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
**************
የብልፅግና ፓርቲ በሚቀጥሉት ወራት ለኢትዮጵያ ህዝብ ብስራቶች ይኖሩታል ሲሉ የፓርቲው ፕሬዚዳንት ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተናገሩ።
“ባለፉት ጥቂት ዓመታት የተጓዝነው የብልፅግና ጉዞ ምዕራፍ አንድ ከጥልቅ እንቅልፍ፣ ከብዙ ዕዳ መንቃት የጀመርንበት የመነሳት ዘመን ነበር” ብለዋል በብልፅግና ፓርቲ 2ኛ ጉባኤ የመክፈቻ ንግግራቸው።
በዚህ ምዕራፍ የታሰረ ይፈታ፣ የተሰደደ ይመለስ፣ ያኮረፈ ይታረቅ፣ ከመከላከያም ሆነ ከዩኒቨርሲቲ የተባረረ ይመለስ፣ በእምነት ተቋማት የተከፋፈለ ይደመር፣ አቧራ ይራገፍ፤ ፀጋ ይገለጥ በሚል በርካታ ሥራዎች መከናወናቸውን አንስተዋል።
ኢትዮጵያ ያለፈችበትን የመነሳት ዘመን አንድ አውሮፕላን መብረር ሲጀምር ተሳፋሪዎቹ ከሚሰማቸው ስሜት ጋር ያመሳሰሉት የፓርቲው ፕሬዚዳንት፤ አውሮፕላኑ የበረራ መስመሩን ከያዘ በኋላ ግን ተሳፋሪዎች ያለምንም መረበሽ መጓዝ ይችላሉ ነው ያሉት።
ብልፅግና ፓርቲ አሁን ምዕራፍ አንድ፣ የመነሳት ዘመንን አጠናቆ የቁልቁለትና የጎንዮሽ ጉዞ የሚያበቃበትን ምዕራፍ ሁለት፣ የማንሰራራት ዘመንን በይፋ የጀመረበት ወቅት መሆኑንም አስታውቀዋል።
https://web.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid0vPPijDUivZKaE8FW3MAruqR3K34tbRwDM6a29pRaVJ9UGEYJHQ1VoTQ5ZcMQqEfal
**************
የብልፅግና ፓርቲ በሚቀጥሉት ወራት ለኢትዮጵያ ህዝብ ብስራቶች ይኖሩታል ሲሉ የፓርቲው ፕሬዚዳንት ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተናገሩ።
“ባለፉት ጥቂት ዓመታት የተጓዝነው የብልፅግና ጉዞ ምዕራፍ አንድ ከጥልቅ እንቅልፍ፣ ከብዙ ዕዳ መንቃት የጀመርንበት የመነሳት ዘመን ነበር” ብለዋል በብልፅግና ፓርቲ 2ኛ ጉባኤ የመክፈቻ ንግግራቸው።
በዚህ ምዕራፍ የታሰረ ይፈታ፣ የተሰደደ ይመለስ፣ ያኮረፈ ይታረቅ፣ ከመከላከያም ሆነ ከዩኒቨርሲቲ የተባረረ ይመለስ፣ በእምነት ተቋማት የተከፋፈለ ይደመር፣ አቧራ ይራገፍ፤ ፀጋ ይገለጥ በሚል በርካታ ሥራዎች መከናወናቸውን አንስተዋል።
ኢትዮጵያ ያለፈችበትን የመነሳት ዘመን አንድ አውሮፕላን መብረር ሲጀምር ተሳፋሪዎቹ ከሚሰማቸው ስሜት ጋር ያመሳሰሉት የፓርቲው ፕሬዚዳንት፤ አውሮፕላኑ የበረራ መስመሩን ከያዘ በኋላ ግን ተሳፋሪዎች ያለምንም መረበሽ መጓዝ ይችላሉ ነው ያሉት።
ብልፅግና ፓርቲ አሁን ምዕራፍ አንድ፣ የመነሳት ዘመንን አጠናቆ የቁልቁለትና የጎንዮሽ ጉዞ የሚያበቃበትን ምዕራፍ ሁለት፣ የማንሰራራት ዘመንን በይፋ የጀመረበት ወቅት መሆኑንም አስታውቀዋል።
https://web.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid0vPPijDUivZKaE8FW3MAruqR3K34tbRwDM6a29pRaVJ9UGEYJHQ1VoTQ5ZcMQqEfal