የጨፌ ኦሮሚያ መደበኛ ጉባኤ እየተካሄደ ነው
*******************
የጨፌ ኦሮሚያ 4ኛ ዓመት 6ኛ የሥራ ዘመን 8ኛ መደበኛ ጉባኤ በአዳማ ጨፌ አዳራሽ መካሄድ ጀምሯል፡፡
በጉባኤው ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር ሽመልስ አብዲሳ፣ የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱራህማንና በየደረጃው የሚገኙ የክልሉ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም የጨፌው አባላት ተሰይመዋል።
የጨፌ ኦሮሚያ መደበኛ ጉባኤ በክልሉ በኢኮኖሚ፣ ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ ዘርፎች የተገኙ ስኬቶችን ማስቀጠል በሚያስችሉ አጀንዳዎች ላይ መክሮ ተግዳሮቶችን መፍታት የሚያስችሉ አቅጣጫዎችን እንደሚያስቀምጥ ይጠበቃል፡፡
ጨፌው የክልሉን ህዝብ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውሳኔዎችና የተለያዩ ሹመቶችን መርምሮ ያጸድቃል ተብሎም ይጠበቃል።
በሀምራዊት ብርሀኑ
*******************
የጨፌ ኦሮሚያ 4ኛ ዓመት 6ኛ የሥራ ዘመን 8ኛ መደበኛ ጉባኤ በአዳማ ጨፌ አዳራሽ መካሄድ ጀምሯል፡፡
በጉባኤው ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር ሽመልስ አብዲሳ፣ የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱራህማንና በየደረጃው የሚገኙ የክልሉ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም የጨፌው አባላት ተሰይመዋል።
የጨፌ ኦሮሚያ መደበኛ ጉባኤ በክልሉ በኢኮኖሚ፣ ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ ዘርፎች የተገኙ ስኬቶችን ማስቀጠል በሚያስችሉ አጀንዳዎች ላይ መክሮ ተግዳሮቶችን መፍታት የሚያስችሉ አቅጣጫዎችን እንደሚያስቀምጥ ይጠበቃል፡፡
ጨፌው የክልሉን ህዝብ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውሳኔዎችና የተለያዩ ሹመቶችን መርምሮ ያጸድቃል ተብሎም ይጠበቃል።
በሀምራዊት ብርሀኑ