የዓድዋ ድል ነፃነትን ለሚሹ ሁሉ የማይጠፋ የብርሃን ፀዳል ነው - ፕሬዚዳንት ታየ አጽቀ ሥላሴ
*********************
“የዓድዋ ድል ነፃነትን ለሚሹ ሁሉ የማይጠፋ የብርሃን ፀዳል ነው” ሲሉ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታየ አጽቀ ሥላሴ ተናግረዋል፡፡
ድሉ የቅኝ ግዛት እሳቤን ያንበረከከ፣ ለሰው ልጆች ሁሉ ሰብዓዊ ክብርን ያጎናጸፈ እና የኢትዮጵያውያንን ጅግንነት ለዓለም ያሳየ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡
ለድሉ መገኘት መሰረት የሆነው የኢትዮጵያዊነት ሐሳብ እና ፍልስፍና በትውልዱ በጥልቀት ሊመረመር እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡
ዓድዋ የኢትዮጵያ ሴት አርበኞችን ብርቱ ተሳትፎ እና የፖለቲካ ብለሃት የገለጠ ድል መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡
የዓድዋ ድል የአንድ ወቅት ብያኔ ሳይሆን ትናንትን የወሰነ፣ ዛሬን የገለጠ እና ነገን የተለመ ጠንካራ አስተሳሳሪ ሰንሰለት እንደሆነም ገልጸዋል፡፡
129ኛው የዓድዋ ድል በዓል "ዓድዋ የጥቁር ህዝቦች ድል" በሚል መሪ ሐሳብ በዓድዋ ድል መታሰቢያ በመከበር ላይ ይገኛል።
መሐመድ ፊጣሞ
*********************
“የዓድዋ ድል ነፃነትን ለሚሹ ሁሉ የማይጠፋ የብርሃን ፀዳል ነው” ሲሉ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታየ አጽቀ ሥላሴ ተናግረዋል፡፡
ድሉ የቅኝ ግዛት እሳቤን ያንበረከከ፣ ለሰው ልጆች ሁሉ ሰብዓዊ ክብርን ያጎናጸፈ እና የኢትዮጵያውያንን ጅግንነት ለዓለም ያሳየ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡
ለድሉ መገኘት መሰረት የሆነው የኢትዮጵያዊነት ሐሳብ እና ፍልስፍና በትውልዱ በጥልቀት ሊመረመር እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡
ዓድዋ የኢትዮጵያ ሴት አርበኞችን ብርቱ ተሳትፎ እና የፖለቲካ ብለሃት የገለጠ ድል መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡
የዓድዋ ድል የአንድ ወቅት ብያኔ ሳይሆን ትናንትን የወሰነ፣ ዛሬን የገለጠ እና ነገን የተለመ ጠንካራ አስተሳሳሪ ሰንሰለት እንደሆነም ገልጸዋል፡፡
129ኛው የዓድዋ ድል በዓል "ዓድዋ የጥቁር ህዝቦች ድል" በሚል መሪ ሐሳብ በዓድዋ ድል መታሰቢያ በመከበር ላይ ይገኛል።
መሐመድ ፊጣሞ