ዓድዋ የፅናት ተምሳሌት እና የአብሮነት ማሳያ ነው - አቶ አሻድሊ ሐሰን
***************
የዓድዋ ድል የፅናት ተምሳሌት እና የአብሮነት ማሳያ መሆኑን የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር አቶ አሻድሊ ሐሰን ተናግረዋል፡፡
ድሉ የባርነት ቀንበር ተጭኗቸው ለነበሩ አፍሪካውያን እና በመላው ዓለም ለሚገኙ ጥቁር ሕዝቦች የነጻነት ጎህ መቅደዱንም አውስተዋል፡፡
ዓድዋ አፍሪካውያን ለነፃነታቸው በጽናት እንዲታገሉ የወኔ ስንቅ ሆኖ ከማገልገሉም ባሻገር የፓን አፍሪካኒዝም እሳቤ እንዲጎለብት ማገዙን ገልጸዋል፡፡
ርዕሰ መሥተዳድሩ የአሁኑ ትውልድ በተባበረ ክንድ ኢትዮጵያን ከድህነት በማላቀቅ የዓድዋን ድል መድገም እንዳለበት አስገንዝበዋል፡፡
129ኛው የዓድዋ ድል በዓል በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በአሶሳ ከተማ በተለያዩ ዝግጅቶች ተከብሯል።
በነስረዲን ሀሚድ
***************
የዓድዋ ድል የፅናት ተምሳሌት እና የአብሮነት ማሳያ መሆኑን የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር አቶ አሻድሊ ሐሰን ተናግረዋል፡፡
ድሉ የባርነት ቀንበር ተጭኗቸው ለነበሩ አፍሪካውያን እና በመላው ዓለም ለሚገኙ ጥቁር ሕዝቦች የነጻነት ጎህ መቅደዱንም አውስተዋል፡፡
ዓድዋ አፍሪካውያን ለነፃነታቸው በጽናት እንዲታገሉ የወኔ ስንቅ ሆኖ ከማገልገሉም ባሻገር የፓን አፍሪካኒዝም እሳቤ እንዲጎለብት ማገዙን ገልጸዋል፡፡
ርዕሰ መሥተዳድሩ የአሁኑ ትውልድ በተባበረ ክንድ ኢትዮጵያን ከድህነት በማላቀቅ የዓድዋን ድል መድገም እንዳለበት አስገንዝበዋል፡፡
129ኛው የዓድዋ ድል በዓል በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በአሶሳ ከተማ በተለያዩ ዝግጅቶች ተከብሯል።
በነስረዲን ሀሚድ