አባዬ የግጥም መድብል አዘጋጅቶ ዛሬ ታትሞ ተለቋል። በቅርብ ለገበያ ይለቀቃል፡፡ ድንገት መንገድ ላይ ካያችሁት ከቻላችሁ ግዙለት፣ ካልሆነም ገለጥ ገለጥ አርጉለት።
በሰባ ዓመቱ ገጥሞ፣ ታይፕ አርጎ (በቤተሰብ ርብርብም) ያዘጋጀው ነው። (በቀን ቤት ውስጥ ስንት ግጥም እንደሚነበብልን አትገምቱም። አብሶ ያቺ ትርንጎ የምትለው ግጥሙን ሁሌ ሲያነብ የተወለደበት አርማንያ/ሰሜን ሸዋ/ ትዝ እያለው እንባ እንባ ስለሚለው የቤታችን ዓባይ ግጥም ናት።) ታድያ ስብስቡን እኔ ላርምልህ ስለው 'አይሆንም አንቺ ታሪኬን ታርሚያለሽ' ብሎ ኸገጣሚው ኤፍሬም ሥዩም ጋር ነው የከረሙበት። ይመቻቸው። ጨርሰዉት ታትሟል።
እዚህም ቻናል ላይ ስላለ በዛው በሰበቡ ስለሱ ትንሽ ስጎርር እንዲያይ ብዬ ነው 😍 በቅርብ ደግሞ የሕይወት ታሪኩ ይለቀቃል።
ፎቶዎች ይከተላሉ።
መጽሐፍ፡ ጥዱ የአያቴ እኩያ ዛፍ
ደራሲ፡ ስምዖን ማርዬ
ሽፋን ዲዛይን፡ ዮፍታሄ ኃይሉ
ጥር 8 2017 ዓ.ም.
በሰባ ዓመቱ ገጥሞ፣ ታይፕ አርጎ (በቤተሰብ ርብርብም) ያዘጋጀው ነው። (በቀን ቤት ውስጥ ስንት ግጥም እንደሚነበብልን አትገምቱም። አብሶ ያቺ ትርንጎ የምትለው ግጥሙን ሁሌ ሲያነብ የተወለደበት አርማንያ/ሰሜን ሸዋ/ ትዝ እያለው እንባ እንባ ስለሚለው የቤታችን ዓባይ ግጥም ናት።) ታድያ ስብስቡን እኔ ላርምልህ ስለው 'አይሆንም አንቺ ታሪኬን ታርሚያለሽ' ብሎ ኸገጣሚው ኤፍሬም ሥዩም ጋር ነው የከረሙበት። ይመቻቸው። ጨርሰዉት ታትሟል።
እዚህም ቻናል ላይ ስላለ በዛው በሰበቡ ስለሱ ትንሽ ስጎርር እንዲያይ ብዬ ነው 😍 በቅርብ ደግሞ የሕይወት ታሪኩ ይለቀቃል።
ፎቶዎች ይከተላሉ።
መጽሐፍ፡ ጥዱ የአያቴ እኩያ ዛፍ
ደራሲ፡ ስምዖን ማርዬ
ሽፋን ዲዛይን፡ ዮፍታሄ ኃይሉ
ጥር 8 2017 ዓ.ም.