የአምስት ሚኒስትሮች ሹመት በነገው ዕለት በፓርላማ ሊጸድቅ ነው
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በነገው ዕለት በሚያካሄደው መደበኛ ስብሰባው፤ ከአንድ ሳምንት በፊት በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ የተሾሙትን ጨምሮ የአምስት ሚኒስትሮችን ሹመት መርምሮ ሊያያጸድቅ ነው። ፓርላማው በዚሁ ስብሰባው፤ የከተማ መሬትን የተመለከቱትን ሁለት የአዋጅ ረቂቆችን ጨምሮ አራት አዋጆችን ለሚመለከታቸው የምክር ቤቱ ቋሚ ኮሚቴዎች ይመራል።
መደበኛ ስብሰባዎቹን ማክሰኞ እና ሐሙስ የሚያካሄደው የተወካዮች ምክር ቤት፤ ለነገ ጥቅምት 19፤ 2017 ሰባት አጀንዳዎችን ይዟል። በህዝብ ተወካዮች እና በፌደሬሽን ምክር ቤቶች የመክፈቻ የጋራ ስብሰባ ላይ፤ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀስላሴ ያደረጉትን የመክፈቻ ንግግር አስመልክቶ የሚቀርብ “የድጋፍ ሞሽን” ማድመጥ የሚለው ከአጀንዳዎቹ መካከል አንዱ ነው።
አቶ ታዬ የኢፌዲሪ ፕሬዝዳንት ሆነው የተሾሙት፤ በመስከረም ወር መጨረሻ በተካሄደው በዚሁ የመክፈቻ ስነ ስርዓት ላይ እንደነበር ይታወሳል። ከዚህ ስነ ስርዓት አንድ ሳምንት በኋላ፤ ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞትዮስ አቶ ታዬን በመተካት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነው ተሹመዋል።
በነገው የፓርላማ ስብሰባ፤ የዶ/ር ጌዲዮን፤ በፍትህ ሚኒስትርነት እርሳቸውን የተኳቸው የወ/ሮ ሃና አርአያ ስላሴ፣ የቱሪዝም ሚኒስትር የሆኑት ወ/ሮ ሰላማዊት ካሳ ሹመት ይጸድቃል። ባለፈው ዓመት ሰኔ ወር መጨረሻ የተሾሙት የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትሩ ዶ/ር ካሳሁን ጎፌ እና የባህል እና ስፖርት ሚኒስትሯ ወ/ሮ ሸዊት ሻንካም፤ በነገው ዕለት በፓርላማ በመገኘት ቃለ መሃላ እንደሚፈጽሙ ተገልጿል።
🔵 ሙሉ ዘገባውን ለማንበብ:- https://ethiopiainsider.com/2024/14448/
@EthiopiaInsiderNews
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በነገው ዕለት በሚያካሄደው መደበኛ ስብሰባው፤ ከአንድ ሳምንት በፊት በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ የተሾሙትን ጨምሮ የአምስት ሚኒስትሮችን ሹመት መርምሮ ሊያያጸድቅ ነው። ፓርላማው በዚሁ ስብሰባው፤ የከተማ መሬትን የተመለከቱትን ሁለት የአዋጅ ረቂቆችን ጨምሮ አራት አዋጆችን ለሚመለከታቸው የምክር ቤቱ ቋሚ ኮሚቴዎች ይመራል።
መደበኛ ስብሰባዎቹን ማክሰኞ እና ሐሙስ የሚያካሄደው የተወካዮች ምክር ቤት፤ ለነገ ጥቅምት 19፤ 2017 ሰባት አጀንዳዎችን ይዟል። በህዝብ ተወካዮች እና በፌደሬሽን ምክር ቤቶች የመክፈቻ የጋራ ስብሰባ ላይ፤ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀስላሴ ያደረጉትን የመክፈቻ ንግግር አስመልክቶ የሚቀርብ “የድጋፍ ሞሽን” ማድመጥ የሚለው ከአጀንዳዎቹ መካከል አንዱ ነው።
አቶ ታዬ የኢፌዲሪ ፕሬዝዳንት ሆነው የተሾሙት፤ በመስከረም ወር መጨረሻ በተካሄደው በዚሁ የመክፈቻ ስነ ስርዓት ላይ እንደነበር ይታወሳል። ከዚህ ስነ ስርዓት አንድ ሳምንት በኋላ፤ ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞትዮስ አቶ ታዬን በመተካት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነው ተሹመዋል።
በነገው የፓርላማ ስብሰባ፤ የዶ/ር ጌዲዮን፤ በፍትህ ሚኒስትርነት እርሳቸውን የተኳቸው የወ/ሮ ሃና አርአያ ስላሴ፣ የቱሪዝም ሚኒስትር የሆኑት ወ/ሮ ሰላማዊት ካሳ ሹመት ይጸድቃል። ባለፈው ዓመት ሰኔ ወር መጨረሻ የተሾሙት የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትሩ ዶ/ር ካሳሁን ጎፌ እና የባህል እና ስፖርት ሚኒስትሯ ወ/ሮ ሸዊት ሻንካም፤ በነገው ዕለት በፓርላማ በመገኘት ቃለ መሃላ እንደሚፈጽሙ ተገልጿል።
🔵 ሙሉ ዘገባውን ለማንበብ:- https://ethiopiainsider.com/2024/14448/
@EthiopiaInsiderNews