በማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ምክንያት የአምራች ኢንዱስትሪዎች የብር ፍላጎት “በእጥፍ መጨመሩን” የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ ተናገሩ
የኢትዮጵያ መንግስት ከስድስት ወራት በፊት ተግባራዊ ባደረገው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ምክንያት፤ የሀገሪቱ የአምራች ኢንዱስትሪዎች “የብር ፍላጎት” “በእጥፍ እንደጨመረ” የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል ተናገሩ።
ሚኒስትሩ ባለፉት ስድስት ወራት ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የቀረበው ብድር “አጥጋቢ” እንዳልሆነ ዛሬ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አስረድተዋል።
አቶ መላኩ የመስሪያ ቤታቸውን የስራ አፈጻጸም ለፓርላማ ባቀረቡበት ወቅት እንዳሉት ባለፈው መንፈቅ ዓመት ለአነስተኛ እና መካከለኛ አምራች ኢንዱስትሪዎች የስራ ማስኬጃ ብድር እና የሊዝ ፋይናንስ ለማቅረብ ታቅዶ የነበረው የገንዘብ መጠን 3.4 ቢሊዮን ብር ነው።
ሆኖም በዚህ ጊዜ ውስጥ ለኢንዱስትሪዎቹ የቀረበው 7.8 ቢሊዮን ብር እንደሆነ ሚኒስትሩ ገልጸዋል። የገንዘብ መጠኑ ከ2016 ተመሳሳይ ወቅት ወቅት ጋር ሲነጻጸር በ4.4 ቢሊዮን ብር ገደማ ከፍ ያለ ነው።
ለከፍተኛ አምራች ኢንዱስትሪዎች 28.7 ቢሊዮን ብር ለማቅረብ ታቅዶ እንደነበር ለፓርላማ አባላት ቤቱ ያስረዱት አቶ መላኩ፤ የተሳካው 24.87 ቢሊዮን ብር እንደሆነ ተናግረዋል።
ለከፍተኛ አምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ብድር ከዕቅዱ አኳያ ዝቅ ቢልም፤ ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር ግን 4.9 በመቶ ብልጫ እንዳሳየ ሚኒስትሩ አመልክተዋል።
🔴 ሙሉ ዘገባውን ለማንበብ ➡️ https://ethiopiainsider.com/2025/14887/
@EthiopiaInsiderNews
የኢትዮጵያ መንግስት ከስድስት ወራት በፊት ተግባራዊ ባደረገው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ምክንያት፤ የሀገሪቱ የአምራች ኢንዱስትሪዎች “የብር ፍላጎት” “በእጥፍ እንደጨመረ” የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል ተናገሩ።
ሚኒስትሩ ባለፉት ስድስት ወራት ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የቀረበው ብድር “አጥጋቢ” እንዳልሆነ ዛሬ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አስረድተዋል።
አቶ መላኩ የመስሪያ ቤታቸውን የስራ አፈጻጸም ለፓርላማ ባቀረቡበት ወቅት እንዳሉት ባለፈው መንፈቅ ዓመት ለአነስተኛ እና መካከለኛ አምራች ኢንዱስትሪዎች የስራ ማስኬጃ ብድር እና የሊዝ ፋይናንስ ለማቅረብ ታቅዶ የነበረው የገንዘብ መጠን 3.4 ቢሊዮን ብር ነው።
ሆኖም በዚህ ጊዜ ውስጥ ለኢንዱስትሪዎቹ የቀረበው 7.8 ቢሊዮን ብር እንደሆነ ሚኒስትሩ ገልጸዋል። የገንዘብ መጠኑ ከ2016 ተመሳሳይ ወቅት ወቅት ጋር ሲነጻጸር በ4.4 ቢሊዮን ብር ገደማ ከፍ ያለ ነው።
ለከፍተኛ አምራች ኢንዱስትሪዎች 28.7 ቢሊዮን ብር ለማቅረብ ታቅዶ እንደነበር ለፓርላማ አባላት ቤቱ ያስረዱት አቶ መላኩ፤ የተሳካው 24.87 ቢሊዮን ብር እንደሆነ ተናግረዋል።
ለከፍተኛ አምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ብድር ከዕቅዱ አኳያ ዝቅ ቢልም፤ ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር ግን 4.9 በመቶ ብልጫ እንዳሳየ ሚኒስትሩ አመልክተዋል።
🔴 ሙሉ ዘገባውን ለማንበብ ➡️ https://ethiopiainsider.com/2025/14887/
@EthiopiaInsiderNews