በሶማሊያ የሰላም ማስከበር ተልዕኮ የግብጽ ተሳትፎ፤ “የትኛውንም ሀገር የማስፈራራት ዓላማ” እንደሌለው የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት ተናገሩ
የግብጽ በአዲሱ የአፍሪካ ህብረት የሶማሊያ ድጋፍ እና ማረጋጋት ተልዕኮ ውስጥ መሳተፍ “የትኛውንም ሀገር የማስፈራራት ዓላማ” እንደሌለው የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት አብዱል ፋታህ አልሲሲ ተናገሩ።
ፕሬዝዳንቱ “የሶማሊያን ደህንነት እና መረጋጋት ለማስፈን” ያለመ ባሉት አዲሱ ሰላም አስከባሪ ውስጥ፤ የግብጽ “ተሳትፎ አዎንታዊ” እንደሆነ ገልጸዋል።
አል ሲሲ በጉዳዩ ላይ አስተያየት የሰጡት ዛሬ ሐሙስ ጥር 15 ከሶማሊያ ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ መሐሙድ ጋር በካይሮ ተገናኝተው ከተወያዩ በኋላ በጋራ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ነው።
ሐሰን ሼክ ወደ ካይሮ ያቀኑት በአዲስ አበባ ከጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ተገናኝተው፤ የሶማሊያ እና የኢትዮጵያን ግንኙነት ወደ ነበረበት ለመመለስ በተስማሙ በ12ኛው ቀን ነው።
ግብጽ እና ሶማሊያ ያላቸውን ግንኙነት ወደ “ስልታዊ አጋርነት (strategic partnership) ለማሳደግ የጋራ ፖለቲካዊ ቃል ኪዳን” እንደተፈራረሙ በዛሬው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ይፋ ተደርጓል።
በሶማሊያ ያለው ሁኔታ ግብጽን ከ30 ዓመታት በላይ ሲያሳስብ የቆየ እንደሆነ በዚሁ መግለጫ ላይ የጠቀሱት ፕሬዝዳንት አልሲሲ፤ ሀገራቸው በሰላም አስከባሪው ተልዕኮ ውስጥ የሚኖራት ተሳትፎ በዋናነት “ለሶማሊያ ህዝብ ያላትን አጋርነት ለማሳየት ያለመ” እንደሆነ አስረድተዋል።
🔴 ሙሉ ዘገባውን ለማንበብ ➡️ https://ethiopiainsider.com/2025/14893/
@EthiopiaInsiderNews
የግብጽ በአዲሱ የአፍሪካ ህብረት የሶማሊያ ድጋፍ እና ማረጋጋት ተልዕኮ ውስጥ መሳተፍ “የትኛውንም ሀገር የማስፈራራት ዓላማ” እንደሌለው የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት አብዱል ፋታህ አልሲሲ ተናገሩ።
ፕሬዝዳንቱ “የሶማሊያን ደህንነት እና መረጋጋት ለማስፈን” ያለመ ባሉት አዲሱ ሰላም አስከባሪ ውስጥ፤ የግብጽ “ተሳትፎ አዎንታዊ” እንደሆነ ገልጸዋል።
አል ሲሲ በጉዳዩ ላይ አስተያየት የሰጡት ዛሬ ሐሙስ ጥር 15 ከሶማሊያ ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ መሐሙድ ጋር በካይሮ ተገናኝተው ከተወያዩ በኋላ በጋራ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ነው።
ሐሰን ሼክ ወደ ካይሮ ያቀኑት በአዲስ አበባ ከጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ተገናኝተው፤ የሶማሊያ እና የኢትዮጵያን ግንኙነት ወደ ነበረበት ለመመለስ በተስማሙ በ12ኛው ቀን ነው።
ግብጽ እና ሶማሊያ ያላቸውን ግንኙነት ወደ “ስልታዊ አጋርነት (strategic partnership) ለማሳደግ የጋራ ፖለቲካዊ ቃል ኪዳን” እንደተፈራረሙ በዛሬው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ይፋ ተደርጓል።
በሶማሊያ ያለው ሁኔታ ግብጽን ከ30 ዓመታት በላይ ሲያሳስብ የቆየ እንደሆነ በዚሁ መግለጫ ላይ የጠቀሱት ፕሬዝዳንት አልሲሲ፤ ሀገራቸው በሰላም አስከባሪው ተልዕኮ ውስጥ የሚኖራት ተሳትፎ በዋናነት “ለሶማሊያ ህዝብ ያላትን አጋርነት ለማሳየት ያለመ” እንደሆነ አስረድተዋል።
🔴 ሙሉ ዘገባውን ለማንበብ ➡️ https://ethiopiainsider.com/2025/14893/
@EthiopiaInsiderNews