የአፈር ማዳበሪያ አቅርቦት እና ስርጭት መዘግየት፤ ዘንድሮም በፓርላማ ማነጋገሩን ቀጥሏል
የግብርና ሚኒስቴር ኃላፊዎች የሩብ፣ የመንፈቅ፣ የዘጠኝ ወር አሊያም የዓመት የስራ አፈጻጸም ሪፖርታቸውን ለማቅረብ ወደ ፓርላማ በሚመጡበት ጊዜ ሁልጊዜም ከአንድ ጉዳይ ጋር የተያያዙ በርከት ያሉ ጥያቄዎች ይቀርቡላቸዋል። ጉዳዩ አብዛኛውን የሀገሪቱን ህዝብ ብዛት የሚወክለውን አርሶ አደር በቀጥታ የሚመለከተው የአፈር ማዳበሪያ አቅርቦት እና ስርጭት ነው።
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ትላንት ሰኞ ጥር 19፤ 2017 ባካሄደው ልዩ ስብሰባ ላይ ይህ ጉዳይ ተነስቶ መወያያ ሆኗል። ለልዩ ስብሰባው በቀዳሚነት የተያዘው አጀንዳ፤ “የግብርና ሚኒስቴር የ2017 በጀት ዓመት የስድስት ወራት የእቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ማዳመጥ” የሚል ነበር።
በዚህም መሰረት የግብርና ሚኒስትሩ ዶ/ር ግርማ አመንቴ የመስሪያ ቤታቸውን የመንፈቅ ዓመት የስራ አፈጻጸም፤ ግማሽ ሰዓት ያህል ወስደው በንባብ አሰምተዋል። ሚኒስትሩ በሪፖርታቸው ካነሷቸው አንኳር ጉዳዮች መካከል የአፈር ማዳበሪያን የተመለከተው ይገኝበታል።
የኢትዮጵያ መንግስት ለዘንድሮ በጀት ዓመት ለአፈር ማዳበሪያ ግዢ የሚውል 1.3 ቢሊዮን ዶላር እና 156 ቢሊዮን ብር በጀት መያዙን ዶ/ር ግርማ በሪፖርታቸው ላይ አስታውሰዋል። በተያዘው የ2017 በጀት ዓመት፤ ለመኸር፣ ለበልግ የምርት ወቅቶች እና ለመስኖ ልማት የሚውል 24 ሚሊዮን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ለመግዛት በእቅድ መያዙንም ጠቁመዋል።
የግብርና ሚኒስትሩ ሪፖርት ከተጠናቀቀ በኋላ በተከተለው የጥያቄ እና መልስ ጊዜ የመናገር ዕድል ያገኙ የፓርላማ አባላት የአፈር ማዳበሪያን ጉዳይ በድጋሚ አንስተዋል።
🔴 ዝርዝሩን ለማንበብ ➡️ https://ethiopiainsider.com/2025/14946/
@EthiopiaInsiderNews
የግብርና ሚኒስቴር ኃላፊዎች የሩብ፣ የመንፈቅ፣ የዘጠኝ ወር አሊያም የዓመት የስራ አፈጻጸም ሪፖርታቸውን ለማቅረብ ወደ ፓርላማ በሚመጡበት ጊዜ ሁልጊዜም ከአንድ ጉዳይ ጋር የተያያዙ በርከት ያሉ ጥያቄዎች ይቀርቡላቸዋል። ጉዳዩ አብዛኛውን የሀገሪቱን ህዝብ ብዛት የሚወክለውን አርሶ አደር በቀጥታ የሚመለከተው የአፈር ማዳበሪያ አቅርቦት እና ስርጭት ነው።
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ትላንት ሰኞ ጥር 19፤ 2017 ባካሄደው ልዩ ስብሰባ ላይ ይህ ጉዳይ ተነስቶ መወያያ ሆኗል። ለልዩ ስብሰባው በቀዳሚነት የተያዘው አጀንዳ፤ “የግብርና ሚኒስቴር የ2017 በጀት ዓመት የስድስት ወራት የእቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ማዳመጥ” የሚል ነበር።
በዚህም መሰረት የግብርና ሚኒስትሩ ዶ/ር ግርማ አመንቴ የመስሪያ ቤታቸውን የመንፈቅ ዓመት የስራ አፈጻጸም፤ ግማሽ ሰዓት ያህል ወስደው በንባብ አሰምተዋል። ሚኒስትሩ በሪፖርታቸው ካነሷቸው አንኳር ጉዳዮች መካከል የአፈር ማዳበሪያን የተመለከተው ይገኝበታል።
የኢትዮጵያ መንግስት ለዘንድሮ በጀት ዓመት ለአፈር ማዳበሪያ ግዢ የሚውል 1.3 ቢሊዮን ዶላር እና 156 ቢሊዮን ብር በጀት መያዙን ዶ/ር ግርማ በሪፖርታቸው ላይ አስታውሰዋል። በተያዘው የ2017 በጀት ዓመት፤ ለመኸር፣ ለበልግ የምርት ወቅቶች እና ለመስኖ ልማት የሚውል 24 ሚሊዮን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ለመግዛት በእቅድ መያዙንም ጠቁመዋል።
የግብርና ሚኒስትሩ ሪፖርት ከተጠናቀቀ በኋላ በተከተለው የጥያቄ እና መልስ ጊዜ የመናገር ዕድል ያገኙ የፓርላማ አባላት የአፈር ማዳበሪያን ጉዳይ በድጋሚ አንስተዋል።
🔴 ዝርዝሩን ለማንበብ ➡️ https://ethiopiainsider.com/2025/14946/
@EthiopiaInsiderNews