የኢትዮጵያ እና የሶማሊያ “ቴክኒካዊ ድርድር” ዛሬ ይጀመራል ተብሎ ይጠበቃል
ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ በቱርክ አመቻችነት የሚያካሄዱት “ቴክኒካዊ ድርድር” ዛሬ ይጀመራል ተብሎ ይጠበቃል።
በሶማሊያ
የማስታወቂያ፣ ባህል እና ቱሪዝም ሚኒስትር ዳውድ አዌይስ የተመራ የልዑካን ቡድን ዛሬ ሰኞ ወደ አንካራ አቅንቷል።
ሚኒስትሩ በኤክስ ይፋዊ ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፤ የሁለቱን ሀገራት የመጀመሪያ ዙር ቴክኒካዊ ውይይት ለማስጀመር በአንካራ የሶማሊያ ልዑካንን መቀላቀላቸውን አስታውቀዋል።
ዳውድ አዌይስ በዚሁ መልዕክታቸው፤ ውይይቱ “የአንካራ ቃል ኪዳንን ተግባራዊ ለማድረግ መንገዶች ለማፈላለግ” ያለመ እንደሆነ ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ “ልዩነቶቻቸውን እና አወዛጋቢ ጉዳዮችን ወደ ኋላ ለመተው” እና “ትብብር ለማበጀት” በአንካራ ስምምነት የተፈራረሙት ባለፈው ታህሳስ ወር መጀመሪያ ላይ ነበር።
ሁለቱ ሀገራት በቱርክ አመቻችነት በተፈራረሙትን በዚሁ ስምምነታቸው፤ “አንዳቸው ለሌላው ሉዓላዊነት፣ አንድነት፣ ነጻነት እና የግዛት አንድነት ያላቸውን ክብር እና ቁርጠኝነት” መግለጻቸው ይታወሳል።
🔴 ሙሉ ዘገባውን ለማንበብ ➡️ https://ethiopiainsider.com/2025/15123/
@EthiopiaInsiderNews
ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ በቱርክ አመቻችነት የሚያካሄዱት “ቴክኒካዊ ድርድር” ዛሬ ይጀመራል ተብሎ ይጠበቃል።
በሶማሊያ
የማስታወቂያ፣ ባህል እና ቱሪዝም ሚኒስትር ዳውድ አዌይስ የተመራ የልዑካን ቡድን ዛሬ ሰኞ ወደ አንካራ አቅንቷል።
ሚኒስትሩ በኤክስ ይፋዊ ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፤ የሁለቱን ሀገራት የመጀመሪያ ዙር ቴክኒካዊ ውይይት ለማስጀመር በአንካራ የሶማሊያ ልዑካንን መቀላቀላቸውን አስታውቀዋል።
ዳውድ አዌይስ በዚሁ መልዕክታቸው፤ ውይይቱ “የአንካራ ቃል ኪዳንን ተግባራዊ ለማድረግ መንገዶች ለማፈላለግ” ያለመ እንደሆነ ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ “ልዩነቶቻቸውን እና አወዛጋቢ ጉዳዮችን ወደ ኋላ ለመተው” እና “ትብብር ለማበጀት” በአንካራ ስምምነት የተፈራረሙት ባለፈው ታህሳስ ወር መጀመሪያ ላይ ነበር።
ሁለቱ ሀገራት በቱርክ አመቻችነት በተፈራረሙትን በዚሁ ስምምነታቸው፤ “አንዳቸው ለሌላው ሉዓላዊነት፣ አንድነት፣ ነጻነት እና የግዛት አንድነት ያላቸውን ክብር እና ቁርጠኝነት” መግለጻቸው ይታወሳል።
🔴 ሙሉ ዘገባውን ለማንበብ ➡️ https://ethiopiainsider.com/2025/15123/
@EthiopiaInsiderNews