የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን “ደካማ የሆነ አፈጻጸም አሳይቷል ብለን እናስባለን” - ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ
ቪዲዮ፦ በዛሬው ዕለት በተካሄደው የፓርላማ አስቸኳይ ስብሰባ ላይ፤ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽንን የስራ ሪፖርት ያቀረቡት የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርአያ፤ ኮሚሽኑ በአዋጅ በተሰጠው ጊዜ ውስጥ የምክክር፣ የአጀንዳ መለየት እና ለሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የሚሳተፉ ተወካዮችን የማስመረጥ ስራዎችን ማከናወኑን ተናግረዋል። እነዚህ ሂደቶች በ10 ክልሎች እና በሁለት ከተማ አስተዳደሮች ሙሉ ለሙሉ መጠናቀቃቸውንም ገልጸዋል።
እርሳቸው ይህን ቢሉም የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) የፓርላማ ተወካይ የሆኑት ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ ግን ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽኑ “ደካማ የሆነ አፈጻጸም አሳይቷል ብለን እናስባለን” ሲሉ ተደምጠዋል። እንደ ዶ/ር ደሳለኝ ሁሉ፤ ሁለት የተቃዋሚ ፓርቲ የፓርላማ ተወካዮችም በኮሚሽኑ የስራ አፈጻጸም ያላቸውን አስተያየት እና ጥያቄ ሰንዝረዋል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
🔴 ሶስቱ የፓርላማ አባላት በዛሬው ስብሰባ ላይ የተናገሩትን ለመመልከት ይህን ሊንክ ይጫኑ ➡️ https://youtu.be/xkJymS2kYOY
@EthiopiaInsiderNews
ቪዲዮ፦ በዛሬው ዕለት በተካሄደው የፓርላማ አስቸኳይ ስብሰባ ላይ፤ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽንን የስራ ሪፖርት ያቀረቡት የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርአያ፤ ኮሚሽኑ በአዋጅ በተሰጠው ጊዜ ውስጥ የምክክር፣ የአጀንዳ መለየት እና ለሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የሚሳተፉ ተወካዮችን የማስመረጥ ስራዎችን ማከናወኑን ተናግረዋል። እነዚህ ሂደቶች በ10 ክልሎች እና በሁለት ከተማ አስተዳደሮች ሙሉ ለሙሉ መጠናቀቃቸውንም ገልጸዋል።
እርሳቸው ይህን ቢሉም የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) የፓርላማ ተወካይ የሆኑት ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ ግን ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽኑ “ደካማ የሆነ አፈጻጸም አሳይቷል ብለን እናስባለን” ሲሉ ተደምጠዋል። እንደ ዶ/ር ደሳለኝ ሁሉ፤ ሁለት የተቃዋሚ ፓርቲ የፓርላማ ተወካዮችም በኮሚሽኑ የስራ አፈጻጸም ያላቸውን አስተያየት እና ጥያቄ ሰንዝረዋል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
🔴 ሶስቱ የፓርላማ አባላት በዛሬው ስብሰባ ላይ የተናገሩትን ለመመልከት ይህን ሊንክ ይጫኑ ➡️ https://youtu.be/xkJymS2kYOY
@EthiopiaInsiderNews