የኢትዮጵያ እና ሶማሊያ “ቴክኒካዊ ድርድር” በመጪው መጋቢት ወር ይቀጥላል ተባለ
የኢትዮጵያ እና የሶማሊያ ከፍተኛ ባለስልጣናት የተሳተፉበት የመጀመሪያው ዙር ቴክኒካዊ ድርድር ተጠናቀቀ። በቱርክ አንካራ ከተማ በተካሄደው ድርድር፤ የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ እና የሶማሊያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አሊ ሞሐመድ ዑመር ተገኝተዋል።
በቱርክ በኩል በድርድሩ የተገኙት፤ የኢትዮጵያ እና የሶማሊያ መሪዎች በታህሳስ ወር መጀመሪያ ፊት ለፊት ከመገናኘታቸው በፊት በአዲስ አበባ እና በሞቃዲሾ ተመላልሰው ውይይቱን ያመቻቹት የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሐካን ፊዳን ናቸው።
በዛሬው ድርድር ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ፤ የሁለቱን ሀገራት ልዑካን ቡድን በተናጠል እና በጋራ ማነጋገራቸውን መስሪያ ቤታቸው አስታውቋል።
ሐካን ፊደን በተናጠል እና በጋራ በተደረጉት ውይይቶች፤ ከጊዜ ወደ ጊዜ ልዩነት በበረታበት ዓለም ውስጥ ቀጠናዊ ትብብር ወሳኝ ጠቀሜታዎች እንዳሉት በአጽንኦት መናገራቸውን የቱርክ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት አመልክቷል።
ፊዳን በኢትዮጵያ እና በሶማሊያ መካከል የተጀመረው ድርድር “የአፍሪካን ቀንድ መጻኢ ጊዜ ታሪካዊ ዕድል ይወክላል” በማለት ፋይዳውን ገልጸዋል።
🔴 ለዝርዝሩ ➡️ https://ethiopiainsider.com/2025/15146/
@EthiopiaInsiderNews
የኢትዮጵያ እና የሶማሊያ ከፍተኛ ባለስልጣናት የተሳተፉበት የመጀመሪያው ዙር ቴክኒካዊ ድርድር ተጠናቀቀ። በቱርክ አንካራ ከተማ በተካሄደው ድርድር፤ የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ እና የሶማሊያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አሊ ሞሐመድ ዑመር ተገኝተዋል።
በቱርክ በኩል በድርድሩ የተገኙት፤ የኢትዮጵያ እና የሶማሊያ መሪዎች በታህሳስ ወር መጀመሪያ ፊት ለፊት ከመገናኘታቸው በፊት በአዲስ አበባ እና በሞቃዲሾ ተመላልሰው ውይይቱን ያመቻቹት የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሐካን ፊዳን ናቸው።
በዛሬው ድርድር ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ፤ የሁለቱን ሀገራት ልዑካን ቡድን በተናጠል እና በጋራ ማነጋገራቸውን መስሪያ ቤታቸው አስታውቋል።
ሐካን ፊደን በተናጠል እና በጋራ በተደረጉት ውይይቶች፤ ከጊዜ ወደ ጊዜ ልዩነት በበረታበት ዓለም ውስጥ ቀጠናዊ ትብብር ወሳኝ ጠቀሜታዎች እንዳሉት በአጽንኦት መናገራቸውን የቱርክ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት አመልክቷል።
ፊዳን በኢትዮጵያ እና በሶማሊያ መካከል የተጀመረው ድርድር “የአፍሪካን ቀንድ መጻኢ ጊዜ ታሪካዊ ዕድል ይወክላል” በማለት ፋይዳውን ገልጸዋል።
🔴 ለዝርዝሩ ➡️ https://ethiopiainsider.com/2025/15146/
@EthiopiaInsiderNews