ለአዲስ አበባ ኮሪደር ልማት የሚውለው ገንዘብ ምንጭ፤ የከተማይቱ “ግብር ከፋዮች” መሆናቸውን ከንቲባ አዳነች አቤቤ ተናገሩ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የኮሪደር ልማትን ጨምሮ በአንድ ጊዜ በርካታ ፕሮጀክቶችን ለመተግበር የሚያወጣው ገንዘብ ምንጭ፤ በከተማይቱ ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤ ላይ አነገጋረ። የከተማይቱ ከንቲባ አዳነች አቤቤ “የበጀታችን ምንጩ ግብር ነው። የከተማይቱ ግብር ከፋዮች ናቸው” ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል።
የከተማይቱ ምክር ቤት አባላት ካለፈው ዓመት ጀምሮ በአዲስ አበባ እየተተገበረ የሚገኘውን የኮሪደር ልማት የተመለከቱ ጥያቄዎች እና አስተያየቶችን የሰነዘሩት፤ ዛሬ ረቡዕ የካቲት 12፤ 2017 በተካሄደ የምክር ቤቱ መደበኛ ጉባኤ ላይ ነው።
አቶ ጋትዌች ዎርዲየው የተባሉ የከተማይቱ ምክር ቤት አባል “የኮሪደር ልማት በጀት ምንጩ ከየት ነው?” ሲሉ ለምክር ቤቱ ማብራሪያ እንዲሰጥ ጠይቀዋል። ይህ የእርሳቸው ጥያቄ፤ በሌላኛው የምክር ቤት አባል አቶ ፍቃዱ ታምራት በተሰጠ አስተያየት ላይም ተንጸባርቋል።
የኮሪደር ልማት ስራው “ከስፋቱ አንጻር ሲታይ፣ ምን ያህል በጀት የወሰደ እንደሆነ ሲታይ፣ ምን ያህል ለውጥ ከተማዋ ላይ እያመጣ እንደሆነ ሲታይ፣ ብቻውን በቂ ነበር” ያሉት አቶ ፍቃዱ፤ ይህንኑ አስመልክቶ ብዙ ሰዎች “በግርምት” የሚጠይቁት ጥያቄ “የከተማ አስተዳደሩ ይሄን ያህል ገንዘብ ከየት ሊያመጣ ቻለ?” የሚል እንደሆነ አመልክተዋል።
ዶ/ር ወርቅነሽ ምትኩ የተባሉ የምክር ቤት አባል፤ “አንድ ከተማ በነበረው ሁኔታ፣ ከነበረው ገቢ፣ ይሄን ሁሉ ስኬት ማሳለጥ የሚችል ከሆነ፤ የት ነበርን? ይህ ገንዘብ ገንዘቡ ፈልቆ ነበር?” ሲሉ በገረሜታ ጠይቀዋል።
🔴 ለዝርዝሩ ➡️ https://ethiopiainsider.com/2025/15161/
@EthiopiaInsiderNews
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የኮሪደር ልማትን ጨምሮ በአንድ ጊዜ በርካታ ፕሮጀክቶችን ለመተግበር የሚያወጣው ገንዘብ ምንጭ፤ በከተማይቱ ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤ ላይ አነገጋረ። የከተማይቱ ከንቲባ አዳነች አቤቤ “የበጀታችን ምንጩ ግብር ነው። የከተማይቱ ግብር ከፋዮች ናቸው” ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል።
የከተማይቱ ምክር ቤት አባላት ካለፈው ዓመት ጀምሮ በአዲስ አበባ እየተተገበረ የሚገኘውን የኮሪደር ልማት የተመለከቱ ጥያቄዎች እና አስተያየቶችን የሰነዘሩት፤ ዛሬ ረቡዕ የካቲት 12፤ 2017 በተካሄደ የምክር ቤቱ መደበኛ ጉባኤ ላይ ነው።
አቶ ጋትዌች ዎርዲየው የተባሉ የከተማይቱ ምክር ቤት አባል “የኮሪደር ልማት በጀት ምንጩ ከየት ነው?” ሲሉ ለምክር ቤቱ ማብራሪያ እንዲሰጥ ጠይቀዋል። ይህ የእርሳቸው ጥያቄ፤ በሌላኛው የምክር ቤት አባል አቶ ፍቃዱ ታምራት በተሰጠ አስተያየት ላይም ተንጸባርቋል።
የኮሪደር ልማት ስራው “ከስፋቱ አንጻር ሲታይ፣ ምን ያህል በጀት የወሰደ እንደሆነ ሲታይ፣ ምን ያህል ለውጥ ከተማዋ ላይ እያመጣ እንደሆነ ሲታይ፣ ብቻውን በቂ ነበር” ያሉት አቶ ፍቃዱ፤ ይህንኑ አስመልክቶ ብዙ ሰዎች “በግርምት” የሚጠይቁት ጥያቄ “የከተማ አስተዳደሩ ይሄን ያህል ገንዘብ ከየት ሊያመጣ ቻለ?” የሚል እንደሆነ አመልክተዋል።
ዶ/ር ወርቅነሽ ምትኩ የተባሉ የምክር ቤት አባል፤ “አንድ ከተማ በነበረው ሁኔታ፣ ከነበረው ገቢ፣ ይሄን ሁሉ ስኬት ማሳለጥ የሚችል ከሆነ፤ የት ነበርን? ይህ ገንዘብ ገንዘቡ ፈልቆ ነበር?” ሲሉ በገረሜታ ጠይቀዋል።
🔴 ለዝርዝሩ ➡️ https://ethiopiainsider.com/2025/15161/
@EthiopiaInsiderNews