በኢትዮጵያ ከሚከሰተው የኤሌክትሪክ ኃይል መቆራረጥ የ47 በመቶው መንስኤ “ዛፎች የሚፈጥሩት ንክኪ ነው” ተባለ
በኢትዮጵያ በተለያዩ አካባቢዎች ለሚከሰት የኤሌክትሪክ ኃይል መቆራረጥ 47 በመቶ የሚሆነውን ድርሻ የሚይዘው፤ ዛፎች እና ቅርንጫፎች በኤሌክትሪክ መስመሮች ላይ የሚፈጥሩት ንኪኪ መሆኑ ተገለጸ።
በመሰረተ ልማት ላይ የሚደርሱ ስርቆቶች እና ጉዳቶች የኃይል መቆራረጥ እንዲከሰት የሚያደርጉ ሌሎች ዋነኛ ምክንያቶች መሆናቸውንም ተነግሯል።
ይህ የተገለጸው፤ የኤሌክትሪክ ኃይል ማከፋፈያ መስመሮችን የማስተዳደር እና የኤሌክትሪክ ኃይልን በጅምላ ገዝቶ ለደንበኞች የመሸጥ ኃላፊነት ያለፈበት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት፤ ዛሬ ሐሙስ የካቲት 20፤ 2017 በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ነው።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የኃይል አቅርቦት እና ጥራትን ለማሻሻል በአጭር ጊዜ ለመተግበር ካቀዳቸው ተግባራት መካከል፤ በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ውስጥ የገቡ ዛፎች እና ቅርንጫፎችን መቁረጥ አንዱ እንደሆነ የተቋሙ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ጌቱ ገረመው በዛሬው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ተናግረዋል።
በኤሌክትሪክ መስመሮች ላይ አደጋ የሚፈጥሩ ዛፎች እና ቅርንጫፎችን የመቁረጥ ተግባር ከሁለት ወር በፊት እንደተጀመረ የገለጹት አቶ ጌቱ፤ የስራው አፈጻጸም በአዲስ አበባ 50 በመቶ እንዲሁም በሀገር አቀፍ ደረጃ 30 በመቶ እንደደረሰ አስረድተዋል።
🔴 ዝርዝሩን ለማንበብ ➡️ https://ethiopiainsider.com/2025/15194/
@EthiopiaInsiderNews
በኢትዮጵያ በተለያዩ አካባቢዎች ለሚከሰት የኤሌክትሪክ ኃይል መቆራረጥ 47 በመቶ የሚሆነውን ድርሻ የሚይዘው፤ ዛፎች እና ቅርንጫፎች በኤሌክትሪክ መስመሮች ላይ የሚፈጥሩት ንኪኪ መሆኑ ተገለጸ።
በመሰረተ ልማት ላይ የሚደርሱ ስርቆቶች እና ጉዳቶች የኃይል መቆራረጥ እንዲከሰት የሚያደርጉ ሌሎች ዋነኛ ምክንያቶች መሆናቸውንም ተነግሯል።
ይህ የተገለጸው፤ የኤሌክትሪክ ኃይል ማከፋፈያ መስመሮችን የማስተዳደር እና የኤሌክትሪክ ኃይልን በጅምላ ገዝቶ ለደንበኞች የመሸጥ ኃላፊነት ያለፈበት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት፤ ዛሬ ሐሙስ የካቲት 20፤ 2017 በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ነው።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የኃይል አቅርቦት እና ጥራትን ለማሻሻል በአጭር ጊዜ ለመተግበር ካቀዳቸው ተግባራት መካከል፤ በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ውስጥ የገቡ ዛፎች እና ቅርንጫፎችን መቁረጥ አንዱ እንደሆነ የተቋሙ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ጌቱ ገረመው በዛሬው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ተናግረዋል።
በኤሌክትሪክ መስመሮች ላይ አደጋ የሚፈጥሩ ዛፎች እና ቅርንጫፎችን የመቁረጥ ተግባር ከሁለት ወር በፊት እንደተጀመረ የገለጹት አቶ ጌቱ፤ የስራው አፈጻጸም በአዲስ አበባ 50 በመቶ እንዲሁም በሀገር አቀፍ ደረጃ 30 በመቶ እንደደረሰ አስረድተዋል።
🔴 ዝርዝሩን ለማንበብ ➡️ https://ethiopiainsider.com/2025/15194/
@EthiopiaInsiderNews