ወንዞችን በቆሻሻ የሚበክሉ ግለሰቦችን እና ተቋማትን እስከ አንድ ሚሊዮን ብር የሚያስቀጣ ደንብ ተግባራዊ ሊደረግ ነው
በአዲስ አበባ ከተማ ያሉ ወንዞችን፤ በባህሪያቸው “አደገኛነት” ባላቸው ደረቅም ይሁን ፈሳሽ ቆሻሻ የሚበክሉ ድርጅቶችን አንድ ሚሊዮን ብር ቅጣት የሚጥል ደንብ ተግባራዊ ሊደረግ ነው።
ከመኖሪያ ቤቶች የሽንት ቤት አሊያም ማንኛውንም ያልተጣራ ፍሳሽ ቆሻሻ ወደ ወንዝ መልቀቅ እስከ 300 ሺህ ብር እንደሚያስቀጣ ደንቡ ይደነግጋል። የወንዞችን ብክለት ለመከላከል የሚያስችለውን ይህ ደንብ የጸደቀው፤ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ ባለፈው ታህሳስ ወር ባደረገው ስብሰባ ላይ ነው።
በደንቡ ላይ የሰፈሩ ድንጋጌዎች ከታህሳስ 2፤ 2017 ጀምሮ ተፈጻሚ እንደሚሆኑ በሰነዱ ላይ ቢገልጽም፤ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በዚህ መሰረት ገና መቅጣት አለመጀመሩን የመስሪያ ቤቱ ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል።
ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ከከተማይቱ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን እና የውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ ጋር በመሆን፤ ደንቡን የተመለከተ ስልጠና እና የግንዛቤ ማስጨበጫ በትላንትናው እና በዛሬው ዕለት አካሄዷል።
ስልጠናው የተመረኮዘበት “የወንዞች ዳርቻ ልማት እና ብክለት መከላከል ደንብ”፤ በሰባት ክፍሎች እና በ21 አንቀጾች የተከፋፈለ ነው። በደንቡ መጨረሻ በአባሪነት የተካተተው ሰንጠረዥ፤ በወንዝ እና በወንዝ ዳርቻ ላይ ብክለት በሚፈጸሙ ድርጅቶች እና ግለሰቦች ላይ የሚጣሉ አስተዳደራዊ የገንዘብ ቅጣቶችን ዘርዝሯል።
🔴 ዝርዝሩን ለማንበብ ➡️ https://ethiopiainsider.com/2025/15201/
@EthiopiaInsiderNews
በአዲስ አበባ ከተማ ያሉ ወንዞችን፤ በባህሪያቸው “አደገኛነት” ባላቸው ደረቅም ይሁን ፈሳሽ ቆሻሻ የሚበክሉ ድርጅቶችን አንድ ሚሊዮን ብር ቅጣት የሚጥል ደንብ ተግባራዊ ሊደረግ ነው።
ከመኖሪያ ቤቶች የሽንት ቤት አሊያም ማንኛውንም ያልተጣራ ፍሳሽ ቆሻሻ ወደ ወንዝ መልቀቅ እስከ 300 ሺህ ብር እንደሚያስቀጣ ደንቡ ይደነግጋል። የወንዞችን ብክለት ለመከላከል የሚያስችለውን ይህ ደንብ የጸደቀው፤ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ ባለፈው ታህሳስ ወር ባደረገው ስብሰባ ላይ ነው።
በደንቡ ላይ የሰፈሩ ድንጋጌዎች ከታህሳስ 2፤ 2017 ጀምሮ ተፈጻሚ እንደሚሆኑ በሰነዱ ላይ ቢገልጽም፤ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በዚህ መሰረት ገና መቅጣት አለመጀመሩን የመስሪያ ቤቱ ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል።
ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ከከተማይቱ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን እና የውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ ጋር በመሆን፤ ደንቡን የተመለከተ ስልጠና እና የግንዛቤ ማስጨበጫ በትላንትናው እና በዛሬው ዕለት አካሄዷል።
ስልጠናው የተመረኮዘበት “የወንዞች ዳርቻ ልማት እና ብክለት መከላከል ደንብ”፤ በሰባት ክፍሎች እና በ21 አንቀጾች የተከፋፈለ ነው። በደንቡ መጨረሻ በአባሪነት የተካተተው ሰንጠረዥ፤ በወንዝ እና በወንዝ ዳርቻ ላይ ብክለት በሚፈጸሙ ድርጅቶች እና ግለሰቦች ላይ የሚጣሉ አስተዳደራዊ የገንዘብ ቅጣቶችን ዘርዝሯል።
🔴 ዝርዝሩን ለማንበብ ➡️ https://ethiopiainsider.com/2025/15201/
@EthiopiaInsiderNews