ኮንጎ ከሩዋንዳ ጋር ያላትን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት አቋረጠች❗️
በሩዋንዳ በሚደገፉት አማፂያን እና በዴሞክራቲክ ኮንጎ መንግስት ኃይሎች መካከል፤ ቁልፍ በሆነችው ጎማ ከተማ ምሥራቃዊ ክፍል ጦርነት የተቀሰቀሰ ሲሆን፣ በትንሹ 13 የሰላም አስከባሪ ሃይሎች እና የውጭ ሃገር ወታደሮች ህይወታቸው ሲያልፍ፤ በሺህዎች የሚቆጠሩ ሰላማዊ ዜጎች ተፈናቅለዋል። ዴሞክራቲክ ሪፐሊክ ኮንጎም ከሩዋንዳ ጋር ያላትን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት አቋርጣለች።
የኤም 23 አማፂ ቡድን ከሩዋንዳ ጋር በሚያዋስነው ድንበር አካባቢ ከቅርብ ሳምንታት ወዲህ ወደ ሁለት ሚሊዮን የሚጠጉ ሰዎች መኖሪያ እና የሰብዓዊና የጸጥታ ማዕከል ወደ ሆነችው ወደ ጎማ ግዛት በመገስገስ ብዙ ስፍራዎችን ተቆጣጥሯል።
በሩዋንዳ በሚደገፉት አማፂያን እና በዴሞክራቲክ ኮንጎ መንግስት ኃይሎች መካከል፤ ቁልፍ በሆነችው ጎማ ከተማ ምሥራቃዊ ክፍል ጦርነት የተቀሰቀሰ ሲሆን፣ በትንሹ 13 የሰላም አስከባሪ ሃይሎች እና የውጭ ሃገር ወታደሮች ህይወታቸው ሲያልፍ፤ በሺህዎች የሚቆጠሩ ሰላማዊ ዜጎች ተፈናቅለዋል። ዴሞክራቲክ ሪፐሊክ ኮንጎም ከሩዋንዳ ጋር ያላትን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት አቋርጣለች።
የኤም 23 አማፂ ቡድን ከሩዋንዳ ጋር በሚያዋስነው ድንበር አካባቢ ከቅርብ ሳምንታት ወዲህ ወደ ሁለት ሚሊዮን የሚጠጉ ሰዎች መኖሪያ እና የሰብዓዊና የጸጥታ ማዕከል ወደ ሆነችው ወደ ጎማ ግዛት በመገስገስ ብዙ ስፍራዎችን ተቆጣጥሯል።