ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ለቀናት ያለ ምግብ እና ውሃ ከቆዩ በኋላ በህይወት መገኘታቸው ተሰማ
ሜዲትራኒያን ባሕርን ለመሻገር የሞከሩ ኢትዮጵያዊያን አሊያም ኤርትራዊያንን ጨምሮ 32 ፍልሰተኞች በቱኒዚያ የባህር ዳርቻ ለበርካታ ቀናት ያለ እርዳታ ከቆዩ በኋላ በረድኤት ድርጅት ሕይወታቸው ታደገ።
ፍልሰተኞች ተሳፍረውበት የነበረው ጀልባ አደጋ ከደረሰበት በኋላ "ሴቶች፣ ህፃናት እና ወንዶች" ካለ ምግብ እና ውሃ ለቀናት መቆየታቸውን ሜድትሪና የተሰኘው ረድኤት ድርጅት ገልጿል። አንድ ሰው በነዳጅ ማቀነባበሪያው ውስጥ ሕይወቱ ማለፉንም አስታውቋል።
መንግሥታዊ ያልሆነው ድርጅት ከነዳጅ ማቀነባበሪያው 32ቱንም ፍልሰተኞች ማክሰኞ ከሰዓት እንደታደገ የገለፀ ሲሆን፤ ፍልሰተኞቹ ክትትል እተደረገላቸው ነው ብሏል።
ሜዲትራኒያን ባሕርን ለመሻገር የሞከሩ ኢትዮጵያዊያን አሊያም ኤርትራዊያንን ጨምሮ 32 ፍልሰተኞች በቱኒዚያ የባህር ዳርቻ ለበርካታ ቀናት ያለ እርዳታ ከቆዩ በኋላ በረድኤት ድርጅት ሕይወታቸው ታደገ።
ፍልሰተኞች ተሳፍረውበት የነበረው ጀልባ አደጋ ከደረሰበት በኋላ "ሴቶች፣ ህፃናት እና ወንዶች" ካለ ምግብ እና ውሃ ለቀናት መቆየታቸውን ሜድትሪና የተሰኘው ረድኤት ድርጅት ገልጿል። አንድ ሰው በነዳጅ ማቀነባበሪያው ውስጥ ሕይወቱ ማለፉንም አስታውቋል።
መንግሥታዊ ያልሆነው ድርጅት ከነዳጅ ማቀነባበሪያው 32ቱንም ፍልሰተኞች ማክሰኞ ከሰዓት እንደታደገ የገለፀ ሲሆን፤ ፍልሰተኞቹ ክትትል እተደረገላቸው ነው ብሏል።