አሜሪካ ከዩክሬን ጋር ስታደርግ የቆየችውን የወታደራዊ ደህንነት መረጃ ልውውጥ ማቋረጧን አስታወቀች
አሜሪካ ከዩክሬን ጋር ስታደርግ የቆየችውን የወታደራዊ ደህንነት መረጃ ልውውጥ ማቋረጧን አስታወቀች። ዋሽንግተን እና ኬቭ የሩሲያ-ዩክሬን ጦርነት ከተጀመረ ወዲህ የወታደራዊ ደህንነት መረጃዎችን ሲለዋወጡ መቆየታቸው ተነግሯል። የፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር የሁለቱ ሀገራት የደህንነት መረጃ ልውውጥ እንዲቋረጥ ውሳኔ ማሳለፉን የአሜሪካ የብሔራዊ ደህንነት አማካሪ ማይክ ዋልዝ አረጋግጠዋል።
አሜሪካ ከዩክሬን ጋር ስታደርግ የቆየችውን የወታደራዊ ደህንነት መረጃ ልውውጥ ማቋረጧን አስታወቀች። ዋሽንግተን እና ኬቭ የሩሲያ-ዩክሬን ጦርነት ከተጀመረ ወዲህ የወታደራዊ ደህንነት መረጃዎችን ሲለዋወጡ መቆየታቸው ተነግሯል። የፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር የሁለቱ ሀገራት የደህንነት መረጃ ልውውጥ እንዲቋረጥ ውሳኔ ማሳለፉን የአሜሪካ የብሔራዊ ደህንነት አማካሪ ማይክ ዋልዝ አረጋግጠዋል።