ኦነግና ኦፌኮ ያራመዱት አቋም ተቃወሞ ገጠመው
እናት፣ ኢሕአፓ፣ መኢአድ እና ዐማራ ግዮናዊ ንቅናቄ፤ ኦነግ እና ኦፌኮ ከሳምንታት በፊት በኦሮሚያ ክልል የጋራ "ሽግግር መንግሥት" እንዲመሠረት ከተለያዩ አካላት አደራ መቀበላቸውን በሚመለከት ያራመዱትን አቋም ተቃውመዋል።
አራቱ የፖለቲካ ድርጅቶች ዛሬ በጋራ ባወጡት መግለጫ "የሽግግር መንግሥት በተናጠል በክልል ደረጃ ሊመሠረት አይችልም" ብለዋል።
የሁለቱን ፓርቲዎች አቋም ክልሎችን ከክልሎች የሚያጋጭ እና ለኢትዮጵያ አደጋ የሚያስከትል ነው ያሉት አራቱ የፖለቲካ ድርጅቶች ሁኔታው "እሳት ላይ ቤንዚን እንደማርከፍከፍ የሚቆጠር ነው" ሲሉ ነቅፈዋል።
አራቱ የፖለቲካ ድርጅቶች የታሰበው "የሽግግር መንግሥት" ጥያቄ ችግሮችን የሚያባብስ እንጂ መፍትሔ የሚያመጣ እንዳልሆነም በመግለጫቸው ጠቅሰዋል።
እናት፣ ኢሕአፓ፣ መኢአድ እና ዐማራ ግዮናዊ ንቅናቄ፤ ኦነግ እና ኦፌኮ ከሳምንታት በፊት በኦሮሚያ ክልል የጋራ "ሽግግር መንግሥት" እንዲመሠረት ከተለያዩ አካላት አደራ መቀበላቸውን በሚመለከት ያራመዱትን አቋም ተቃውመዋል።
አራቱ የፖለቲካ ድርጅቶች ዛሬ በጋራ ባወጡት መግለጫ "የሽግግር መንግሥት በተናጠል በክልል ደረጃ ሊመሠረት አይችልም" ብለዋል።
የሁለቱን ፓርቲዎች አቋም ክልሎችን ከክልሎች የሚያጋጭ እና ለኢትዮጵያ አደጋ የሚያስከትል ነው ያሉት አራቱ የፖለቲካ ድርጅቶች ሁኔታው "እሳት ላይ ቤንዚን እንደማርከፍከፍ የሚቆጠር ነው" ሲሉ ነቅፈዋል።
አራቱ የፖለቲካ ድርጅቶች የታሰበው "የሽግግር መንግሥት" ጥያቄ ችግሮችን የሚያባብስ እንጂ መፍትሔ የሚያመጣ እንዳልሆነም በመግለጫቸው ጠቅሰዋል።