የክርስትና እውነቶች


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha
Toifa: Din


📖መጽሐፍ ቅዱሳዊ📖 የሆኑ መንፈሳዊ ጽሑፎችን የሚያገኙበት ቻናል ነው❗
https://t.me/+TmGQ3IbrOB4vS0rR

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Toifa
Din
Statistika
Postlar filtri




የጌታን እናት ማርያምን የሚመለከት ውዝግብ በቅርቡ በማኅበራዊ ሚዲያ ተነሥቶ እንደ ነበር ይታወሳል። የጉዳዩ ምንጭ ወዳጄ ዘላለም መንግስቱ ሲሆን፣ ይኸውም ማርያም ወላዲተ አምላክ አይደለችም የሚል ነው። ብዘገይም እንኳን አንዳች ነገር ማለት እንዳለብኝ አስቤያለሁ። በአጭሩ ለመናገር፣ ይህ ሙልጭ ያለ ስሕተት ነው። አዲስ አስተምህሮን በ21ኛው መቶ ክ/ዘ ለማምጣት ካልሆነ በቀር የክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ይህን ትምህርት አታውቀውም።

የማርያም ወላዲተ አምላክነት በጥንት ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ጥያቄ አስነሥቶ ተገቢ ማብራሪያና ውሳኔ ተሰጥቶበታል። በርግጥ ጉዳዩ የተነሣው ስለ ኢየሱስ እንጂ ስለ ማርያም ተብሎ አልነበረም። ማርያም ወላዲተ አምላክ ናት ማለት፣ ኢየሱስ አምላክ ነው ማለት ነው። ኢየሱስ አምላክ ሆኖ፣ እናቱ ወላዲተ አምላክ ካልሆነች፣ ኢየሱስ አምላክ የሆነው ከተወለደ በኋላ ነው ማለት ይሆናል። ኢየሱስ ግን አምላክ ያልነበረበት ቅጽበት አልነበረም፤ ከዘላለምም።

እግዚአብሔር ወልድ በድንግል ማርያም ማሕፀን ያደረው አምላክነቱን ሳይተው ነው። እናም ማርያም አምላክም ሰውም የሆነውን ኢየሱስን በመንፈስ ቅዱስ ፀንሳ ወልዳለች። ስለዚህ እምዬ ማርያም ወላዲተ አምላክ ናት። አምላክ በሥጋ ሲወለድ ወልዳዋለችና። ይህ እንግዲህ የኢየሱስን አምላክነት በሚመለከት የሚነሣ ጉዳይ ነው።

የኢየሱስ ሰው-ነት ሲነሣ ደግሞ፣ ሰው መሆኑን ለማስረዳት ማርያም ወላዲተ ሰው መሆኗን መናገር ይቻላል። ወላዲተ አምላክ-ሰው፣ ወላዲተ ክርስቶስ ልንላትም እንችላለን። እነዚህን ሁሉ ስንናገር ግን ወላዲተ አምላክ መሆኗን ሳንክድ መሆን አለበት።

(ዘላለም ያነሣውን ጉዳይ ከሰሞኑ እንደምመለስበት በማሰብ ወደ ሌላ አጠቃላይ ጉዳይ ልለፍ።)

             *              *               *

ለመሆኑ፣ ሰዎች በቅዱሱ መጽሐፍም በቤተ ክርስቲያን ጉባኤም ተነግሮ ያለቀለትን ነገር ለምን ይክዳሉ?

አንድም፣ ባለማወቅ ነው። አላዋቂው ለመማር የተዘጋጅ ልቡና ካለው ይህ ዕዳው ገብስ ነው። በማስተማር መፍትሔ ማግኘት ይቻላል።

አንድም፣ ትኩረትን ፍለጋ ነው። እንዲህ ዐይነቱን ትኩረት የተጠማ ችላ ከማለት በቀር ሌላ መፍትሔ ለጊዜው አልታየኝም።

አንድም፣ አንድን ጽንፍ ለመቃወም፣ ሌላ ጽንፍ መርገጥ ነው። ከኦርቶዶክስ ወገኖች የሚመጣ ቅድስት ማርያምን የሚመለከት ስሁት አስተምህሮ አለ። ከዚህም የተነሣ ወንጌላውያን ያን ስሕተት ሽሽት ሌላ ስህተት ውስጥ የሚገቡባቸው አጋጣሚዎች አሉ። ለምሳሌ፣ “የተሰቀለው የማርያም ሥጋ ነው” የሚል ትምህርት ሲገጥማቸው፣ “ኢየሱስ ከድንግል ማርያም ሥጋ አልነሣም (የሰውነትን ባሕርይ ከማርያም አልተካፈለም)” ሲሉ ኖረዋል። ስሕተትን በስሕተት ማረም ግን ከቶ የሚቻል አይደለም፤ ሁለት ስህተት አንድ እውነት አይሆንምና! ጌታ ኢየሱስ የሰውነትን ባህርይ የተካፈለው ከእናቱ ስለ መሆኑ በቅዱስ መጽሐፍም በቤተ ክርስቲያን ትውፊትም የተረጋገጠ ነው። በተጨማሪም፣ የእኔ ሥጋ የእኔ እንጂ የእናቴ እንዳልሆነ ሁሉ፣ የኢየሱስም ሥጋ የኢየሱስ እንጂ የማርያም አይደለም። ስለዚህ የተሰቀለው የማርያም ሥጋ ሊሆን አይችልም። ለነገሩማ፣ የተሰቀለው ኢየሱስ እንጂ ሥጋው አይደለም።

ስለዚህ ማርያምን የአምላክ ምንጭ፣ መገኛ፣ እርሷ ባትኖር ኖሮ አምላክ እንደማይኖር የሚናገር ጤና ቢስ አስተምህሮን ሽሽት፣ ማርያም ወላዲተ አምላከ መሆኗን መካድም ስሕተትን በስህተት ለማረም የሚደረግ የማያዋጣ ሙከራ ነው። በአንዳንድ ዐቃብያነ እምነት ዘንድ፣ የሚቃወሙትን አሳብ ለመርታት እስካገዘ ድረስ ለልከኛ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትርጓሜና ለትክክለኛ ትውፊት ግድ አለመሰኘት መስተዋል ከጀመረ ግን ከራራመ። እንዲህ ዐይነቱ አካሄድ በማኅበራዊ ሚዲያም ሆነ በመጻሕፍት ላይ፣ ከዊልያም ሌን ክሬይግ እስከ እኛዎቹ እነ እንቶኔ ድረስ እየተስተዋለ ነው።

ዕቅበተ እምነት ውስጥ ያሉ ሰዎች፣ ከልከኛ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትርጓሜ ይልቅ እንዴትም ብለው ወደረኞቻቸውን ለማሽነፍ ቅድሚያ በመስጠት ከቀጠሉ፣ ርቱዕ አስተምህሮን በሚመለከት የእነርሱን ምልከታ ወደማንቀበልበት እንዳንደርስ እሠጋለሁ።

https://www.facebook.com/PaulsPulpit/posts/652743893948488








የጆን ወዝሊ ስብከት ተርጓሚ ግሩም ፊዳ


Sermon 1
Salvation by faith


የጆን ወዝሊ ድንቅ ስብከት ትርጉም በግሩም ፊዳ










እንኳን ደስ አለን!! ፍኖተ ብርሐን

የስነ አፈታትን ( hermenuetics )ትንታኔ የያዘ መፅሐፍ እንሆ ተብለናል ።

አፕል፣ሙዝ፣አናናስ

እነሆ ተወዳጅ እጅግ ጠቃሚ መፅሐፍ እጃችን ሊገባ የቀናት እድሜ ቀርተውታል ።
በእዚህ አጋጣም ወንጌላዊ ዶር Ev Henok Getachew እንኳን ደስ አለህ!!

በአንድ የስነ አሰባበክ እና አፈታት ስልጠና ላይ የሰማሁትን ምሳሌ በማንሳት ልጀምር
አፕል 🍎 መብላት ብንፈልግ እንዴት ልንበላው እንችላለን ? በቀላሉ በንፁህ ውሃ አጠብ አጠብ አድርገን መግመጥ እንችላለን። አንዴን የቅዱሳት መፅሐፍ ክፍሎች እንዲሁ ናቸው ። በግልፅ ከተፃፈው ውጪ ውስብስብ ትርጉም የላቸውም።
ሙዝ 🍌 እንዴት ልንበላው እንችላለን ። እንደ አፕል አጠብ አጠብ ማድረግ ብቻ አይበቃም ።መላጥ ይጠበቅብናል ።ልፋታችን ብዙ ባይሆንም መላጥ ግን ግዴታ ነው። ምክንያቱም ሳይላጥ የሚበላ ከሆነ ለጤና ልክ ላይሆን ይችላልና ። ከቅዱሳት መፅሐፍትም እንዲሁ የተወሰነ ስራ የሚፈልጉ ክፍሎች አሉ ።አሊያ በቀላሉ ትርጉማቸውን ልናገኝ የምንችላቸው ክፍሎችን በስንፍናችን ምክንያት ሳናገኝ እንቀራለን ።
አናናስ 🍍 ስንመገብ ላጥ ላጥ ማድረግ ብቻ አይበቃም ማጠብ ብቻም አይበቃም።ምክንያቱም ለመብላት የማይመች ብዙ ነገር አለውና ።ስለዚህ ቢላ ወይ ሌላ ማሽን ያስፈልገን ይሆናል። አንዳንድ የመፅሐፍ ቅዱስ ክፍሎችም እንዲሁ ናቸው ።በቀላሉ ትርጉማቸውን ማግኘት ከባድ ነው ።ስለዚህ ብዙ ጥናት እና ንባብ ያስፈልጋቸዋል ።ለምን? ያልን እንደሆነ በእኛ እና በፅሁፉ መካከል ያሉ ጋፖችን እነሱን ባለመረዳት የትርጉም መዛባት ውስጥ ልንገባ እንችላለና ።

ለእዚህ ፍቱን መድሐኒቱ እንዴት ቅዱሳት መፅሐፍትን ይጠኑ ?እንዴት ይፈቱ ?የስነ አፈታት መርሐችን እንዴት ይሁን? የሚለውን ማወቅ ነው።

ለእዚህ እጅግ ጠቃሚ መፅሐፍ በወንድማችን ወንጌላዊ ዶር ሄኖክ ጌታቸው ቀርቦልናል። ይህ መፅሐፍ ከአመታት በፊት የታተመ ሲሆን አሁን ዳብሮ ሰፍቶ ብዙ ነገር ተጨምሮበት እንደገና በእጃችን ሊገባ ቀናት ቀርተውታል።

ሁሉም ምዕመን ፣የቃሉ ሰባኪዎች ፣ አስተማሪዎች ፣ የቅዱሳት መፅሐፍትን ትርጉም በጥልቀት ማወቅ ለሚፈልጉ ሁሉ ይሄ መፅሐፍ ጥቆማዬ ነው ።

በድጋሚ ሄኒ እንኳን ደስ አለህ 🙏🥰🙏

13 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.