🙏🙏🙏
#የቤተ መንግስቱን ግድግዳ ሰንጥቆ ገብቶ…
በ1ኛው መቶ ክ/ዘመን መጨረሻ አካባቢ በሮም ቤተ መንግስት የተወለደች፣ ንጉሡ አባቷ ጣዖት የሚያመልክ፣ እስከ ወጣትነቷ ድረስ ክርስቶስን ልታውቅ የምትችልበት አጋጣሚ ያልነበራት፣ ይሁንና ስለክርስቶስ ፍቅር በሰማዕትነት ያረፈች እናት ናት ቅድስት ኦርኒ፡፡ "ኦርኒ" ማለት በምሥራቃውያን ልሳን "ሰላም" ማለት ነው:: ቅድስቲቱ አርበኛ የዘመነ ሐዋርያት የቤተ ክርስቲያን ፍሬ ስትሆን ተወልዳ ያደገችውም በቀድሞው የሮም ግዛት ውስጥ ነው:: ንግሥት እናቷ ምንም ክርስቲያን ብትሆንም የሚደርስባትን መከራ በመፍራት ስለ ክርስትና ልትነግራት አልደፈረችም፡፡ ዘወትር ስለልጇ በስውር ከመጸለይ ግን አልቦዘነችምና ድንቅ ምላሽ አግኝታለች፡፡
ጣዖት የሚያመልከው አባቷ ሰው እንዳያያት ለብቻዋ ቤተ መንግስት ሠርቶ 12 ሞግዚቶችን መድቦ ፍቅረ ጣኦት እንዲያድርባት፣ ጣዖት ከፊቷ አቁሞ ለዘመናት በስውር አቆያት፡፡ የሚያስተምራት ፈላስፋ ከቀጠረላት በኋላም መልኳን እንዳያየው በር ላይ ሆኖ ነበር የሚያስተምራት፡፡ የመዳን ምክንያት የሚፈልግልን እግዚአብሔር ግን ይህን የንጉሱ አካሔድ ተጠቀመበት፡፡ በሚገርም ሁኔታ መምህሯ ጠንካራ ክርስቲያን ደግ ሰው ነበርና በምን መንገድ ሃይማኖትን ሊያስተምራት እንደሚችል ሲያስብ አንድ ቀን ቅድስት ኦርኒ ራዕይ እንዳየች ነገረችው፡፡ ራዕዬዋ የቤቷ መስኮቶች ተከፍተው በስተምሥራቅ ነጭ ርግብ የወይራ ዝንጣፊ ይዛ ገብታ ከማዕዷ ላይ አስቀምጣው ትወጣለች፡፡ እርሷን ተከትሎ ቁራ በምዕራብ ገብቶ ማዕዷ ላይ እባብ ጥሎይወጣል፡፡ በ3ኛው ደግሞ ንስር ገብቶ አክሊል አስቀምጦላት ወጣ፡፡
ቅድስቲቱም እየገረማት አረጋዊ መምህሯን "ተርጉምልኝ" አለችው፡፡ እርሱም:- ርግብ-ጥበብ መንፈስ ቅዱስ፣ ዘይት-ጥምቀት፣ ቁራ-ክፉ ንጉሥ፣ እባብ-መከራ፣ ንስር-ድል ነሺነት ልዑላዊነት፣ አክሊልም-ክብረ ሰማዕታት ነው" በማለት ክርስቲያን ሆና ይህ ሁሉ እንደሚደረግ ነግሮ ተሰናበታት፡፡ እርሷም ስትጸልይ የእግዚአብሔር መልአክ ተገልጦ ካጽናናት በኋላ አስተምሮ ያጠምቃት ዘንድ ሐዋርያው ቅዱስ ጢሞቴዎስን ልኮላታል፡፡ ሐዋርያውም የቤተ መንግስቱን ግድግዳ ሰንጥቆ ገብቶ፣ ለሰማያዊ ሙሽርነት የሚያበቃ ትምህርት አስተምሮ አጥምቋት ሔዷል፡፡ በክርስቶስ ፍቅር የተነካቸው ቅድስት ኦርኒም የአባቷን ጣዖታት ቀጥቅጣ ሰብራ እውነተኛውን አምላክ ማማለክ በመጀመሯ ከአባቷ ጋር ተጣላች፡፡ ንጉሱ አባቷ በእንስሳት ጅራት ላይ ጸጉሯን አስሮ በማስጎተት ሊገድላት እንስሶቹን ሲይዛቸው ደንብረው እጁን ገንጥለው መሬት ላይ ጥለው ገደሉት፡፡ ቅድስት ኦርኒ ግን ወደ ፈጣሪዋ ጸልያ አድርሳ አባቷን ከሞት አስነሳችው፤ እጁም ተመለሰለት፡፡
በዚህ ታላቅ ተአምር ምክንያትም በዚያች ዕለት ብቻ አባቷና 30,000 የከተማው አሕዛብ አምነው ተጠምቀዋል፡፡ ቅድስት ኦርኒ ኃይለ መንፈስ ቅዱስ ታጥቃ ክርስትናን ሰብካለች፡፡ የክርስትና ጠላት የነበረው ንጉሡ ዳኬዎስ፣ ልጁና ሌሎች 2 ነገሥታት ክርስትናን እንደትተው ለጣኦትም እንድትሰግድ በእሳት በማቃጠል፣ ለአራዊት በመስጠት፣ በግርፋትና በጦር ፈትነዋታል፡፡ እርሷ ግን ሁሉን በክርስቶስ ኃይል ድል ነስታለች፡፡ ድንቅ ተአምራት ያደረገችው ቅድስት እናት በመጨረሻም ጥር 30 በሰማዕትነት አርፋለች፡፡ በዘመነ ስብከቷ አስተምራ ካሳመነቻቸው ባሻገር 130,000 የሚያህሉ ሰዎች ለሰማዕትነት እንዲበቁም ምክንያት ሆናለች፡፡ ገዳማውያን አባቶችና እናቶቻችንን በመርዳት የበረከታቸው ተሳታፊ እንሁን፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
🙏🙏🙏
🌴🌴🌴
https://www.facebook.com/share/p/18Dc1yaZPy/?mibextid=wwXIfr
#የቤተ መንግስቱን ግድግዳ ሰንጥቆ ገብቶ…
በ1ኛው መቶ ክ/ዘመን መጨረሻ አካባቢ በሮም ቤተ መንግስት የተወለደች፣ ንጉሡ አባቷ ጣዖት የሚያመልክ፣ እስከ ወጣትነቷ ድረስ ክርስቶስን ልታውቅ የምትችልበት አጋጣሚ ያልነበራት፣ ይሁንና ስለክርስቶስ ፍቅር በሰማዕትነት ያረፈች እናት ናት ቅድስት ኦርኒ፡፡ "ኦርኒ" ማለት በምሥራቃውያን ልሳን "ሰላም" ማለት ነው:: ቅድስቲቱ አርበኛ የዘመነ ሐዋርያት የቤተ ክርስቲያን ፍሬ ስትሆን ተወልዳ ያደገችውም በቀድሞው የሮም ግዛት ውስጥ ነው:: ንግሥት እናቷ ምንም ክርስቲያን ብትሆንም የሚደርስባትን መከራ በመፍራት ስለ ክርስትና ልትነግራት አልደፈረችም፡፡ ዘወትር ስለልጇ በስውር ከመጸለይ ግን አልቦዘነችምና ድንቅ ምላሽ አግኝታለች፡፡
ጣዖት የሚያመልከው አባቷ ሰው እንዳያያት ለብቻዋ ቤተ መንግስት ሠርቶ 12 ሞግዚቶችን መድቦ ፍቅረ ጣኦት እንዲያድርባት፣ ጣዖት ከፊቷ አቁሞ ለዘመናት በስውር አቆያት፡፡ የሚያስተምራት ፈላስፋ ከቀጠረላት በኋላም መልኳን እንዳያየው በር ላይ ሆኖ ነበር የሚያስተምራት፡፡ የመዳን ምክንያት የሚፈልግልን እግዚአብሔር ግን ይህን የንጉሱ አካሔድ ተጠቀመበት፡፡ በሚገርም ሁኔታ መምህሯ ጠንካራ ክርስቲያን ደግ ሰው ነበርና በምን መንገድ ሃይማኖትን ሊያስተምራት እንደሚችል ሲያስብ አንድ ቀን ቅድስት ኦርኒ ራዕይ እንዳየች ነገረችው፡፡ ራዕዬዋ የቤቷ መስኮቶች ተከፍተው በስተምሥራቅ ነጭ ርግብ የወይራ ዝንጣፊ ይዛ ገብታ ከማዕዷ ላይ አስቀምጣው ትወጣለች፡፡ እርሷን ተከትሎ ቁራ በምዕራብ ገብቶ ማዕዷ ላይ እባብ ጥሎይወጣል፡፡ በ3ኛው ደግሞ ንስር ገብቶ አክሊል አስቀምጦላት ወጣ፡፡
ቅድስቲቱም እየገረማት አረጋዊ መምህሯን "ተርጉምልኝ" አለችው፡፡ እርሱም:- ርግብ-ጥበብ መንፈስ ቅዱስ፣ ዘይት-ጥምቀት፣ ቁራ-ክፉ ንጉሥ፣ እባብ-መከራ፣ ንስር-ድል ነሺነት ልዑላዊነት፣ አክሊልም-ክብረ ሰማዕታት ነው" በማለት ክርስቲያን ሆና ይህ ሁሉ እንደሚደረግ ነግሮ ተሰናበታት፡፡ እርሷም ስትጸልይ የእግዚአብሔር መልአክ ተገልጦ ካጽናናት በኋላ አስተምሮ ያጠምቃት ዘንድ ሐዋርያው ቅዱስ ጢሞቴዎስን ልኮላታል፡፡ ሐዋርያውም የቤተ መንግስቱን ግድግዳ ሰንጥቆ ገብቶ፣ ለሰማያዊ ሙሽርነት የሚያበቃ ትምህርት አስተምሮ አጥምቋት ሔዷል፡፡ በክርስቶስ ፍቅር የተነካቸው ቅድስት ኦርኒም የአባቷን ጣዖታት ቀጥቅጣ ሰብራ እውነተኛውን አምላክ ማማለክ በመጀመሯ ከአባቷ ጋር ተጣላች፡፡ ንጉሱ አባቷ በእንስሳት ጅራት ላይ ጸጉሯን አስሮ በማስጎተት ሊገድላት እንስሶቹን ሲይዛቸው ደንብረው እጁን ገንጥለው መሬት ላይ ጥለው ገደሉት፡፡ ቅድስት ኦርኒ ግን ወደ ፈጣሪዋ ጸልያ አድርሳ አባቷን ከሞት አስነሳችው፤ እጁም ተመለሰለት፡፡
በዚህ ታላቅ ተአምር ምክንያትም በዚያች ዕለት ብቻ አባቷና 30,000 የከተማው አሕዛብ አምነው ተጠምቀዋል፡፡ ቅድስት ኦርኒ ኃይለ መንፈስ ቅዱስ ታጥቃ ክርስትናን ሰብካለች፡፡ የክርስትና ጠላት የነበረው ንጉሡ ዳኬዎስ፣ ልጁና ሌሎች 2 ነገሥታት ክርስትናን እንደትተው ለጣኦትም እንድትሰግድ በእሳት በማቃጠል፣ ለአራዊት በመስጠት፣ በግርፋትና በጦር ፈትነዋታል፡፡ እርሷ ግን ሁሉን በክርስቶስ ኃይል ድል ነስታለች፡፡ ድንቅ ተአምራት ያደረገችው ቅድስት እናት በመጨረሻም ጥር 30 በሰማዕትነት አርፋለች፡፡ በዘመነ ስብከቷ አስተምራ ካሳመነቻቸው ባሻገር 130,000 የሚያህሉ ሰዎች ለሰማዕትነት እንዲበቁም ምክንያት ሆናለች፡፡ ገዳማውያን አባቶችና እናቶቻችንን በመርዳት የበረከታቸው ተሳታፊ እንሁን፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
🙏🙏🙏
🌴🌴🌴
https://www.facebook.com/share/p/18Dc1yaZPy/?mibextid=wwXIfr