ለቅዳሴ ያለንን ቦታ እንፈትሽ
እስቲ ቅዳሴ የምንቀርበትን ምክንያቶች እንፈትሻቸው ክርስቶስ በአካል ከሚገኝበት ቦታ ምን በልጦብን ነው የምንቀረው? ኳስ መጫወት ፣ ስፖርት መሥራት ፣ እንቅልፍ? እነዚህ ነገሮች በራሳቸው ጥሩ ቢኾኑም የጌታን ቦታ እየወሰዱ ከኾነ ግን ዝሙት ናቸው። ቅዱስ አውግስጢኖስ "አንድን ነገር የሙሽራውን የክርስቶስን ቦታ እስኪወስድ ድረስ የምንወድ ከኾነ በሙሽራችን ላይ የሚፈጸም ዝሙት ነው" ይለናል። ለአንድ ክርስቲያን በጌታ ቀን በዕለተ እሑድ ቅዳሴ ቀርቶ ሌላ ቦታ መዋል የሙሽራውን ድግስ አልፈልግም በማለት በሙሽራው ላይ የሚፈጸም አመጽ ነው! አሁን በምድራዊው የክርስቶስ ሠርግ ላይ ካልተገኘን እንዴት በሰማያዊው ሠርግ ላይ የመሳተፍ እድል አለን ብለን እናስባለን? ለቅዳሴ ፣ ለክርስቶስ ያለንን ቦታ እንፈትሽ።
መንፈሳዊ ሕይወት ላይ ጥሩ ነን ብለን እራሳችንን የምናስብ ሰዎችም ቢኾን ለቅዳሴው ያለንን ቦታ መልሰን እንፈትሽ፤ ስንት ጊዜ ነው ማኅሌት ተሳተፍን ብለን ቅዳሴው እየተጀመረ ረግጠን የወጣነው? ስንት ጊዜ ነው በጌታ ቀን ቅዳሴውን ትተን መንፈሳዊ ጉዞ ብለን የሔድነው? በቤተክርስቲያን ውስጥ የትኛውም አገልግሎት ሊቀር ይችላል ቅዳሴ ግን በፍጹም አይቀርም ቅዳሴ ለቤተክርስቲያን ሕይወቷ ነውና!
የታረደው በግ ደም እንዳይፋረደን በበጉ ሠርግ ላይ እንገኝ የሕይወትንም መድኃኒት እንቀበል!
እስቲ ቅዳሴ የምንቀርበትን ምክንያቶች እንፈትሻቸው ክርስቶስ በአካል ከሚገኝበት ቦታ ምን በልጦብን ነው የምንቀረው? ኳስ መጫወት ፣ ስፖርት መሥራት ፣ እንቅልፍ? እነዚህ ነገሮች በራሳቸው ጥሩ ቢኾኑም የጌታን ቦታ እየወሰዱ ከኾነ ግን ዝሙት ናቸው። ቅዱስ አውግስጢኖስ "አንድን ነገር የሙሽራውን የክርስቶስን ቦታ እስኪወስድ ድረስ የምንወድ ከኾነ በሙሽራችን ላይ የሚፈጸም ዝሙት ነው" ይለናል። ለአንድ ክርስቲያን በጌታ ቀን በዕለተ እሑድ ቅዳሴ ቀርቶ ሌላ ቦታ መዋል የሙሽራውን ድግስ አልፈልግም በማለት በሙሽራው ላይ የሚፈጸም አመጽ ነው! አሁን በምድራዊው የክርስቶስ ሠርግ ላይ ካልተገኘን እንዴት በሰማያዊው ሠርግ ላይ የመሳተፍ እድል አለን ብለን እናስባለን? ለቅዳሴ ፣ ለክርስቶስ ያለንን ቦታ እንፈትሽ።
መንፈሳዊ ሕይወት ላይ ጥሩ ነን ብለን እራሳችንን የምናስብ ሰዎችም ቢኾን ለቅዳሴው ያለንን ቦታ መልሰን እንፈትሽ፤ ስንት ጊዜ ነው ማኅሌት ተሳተፍን ብለን ቅዳሴው እየተጀመረ ረግጠን የወጣነው? ስንት ጊዜ ነው በጌታ ቀን ቅዳሴውን ትተን መንፈሳዊ ጉዞ ብለን የሔድነው? በቤተክርስቲያን ውስጥ የትኛውም አገልግሎት ሊቀር ይችላል ቅዳሴ ግን በፍጹም አይቀርም ቅዳሴ ለቤተክርስቲያን ሕይወቷ ነውና!
የታረደው በግ ደም እንዳይፋረደን በበጉ ሠርግ ላይ እንገኝ የሕይወትንም መድኃኒት እንቀበል!