ሁሉንም አታስደንቁም!
ዓለምን ብትገዙ፣ ብዙ ድንቅ ነገርን ብታደርጉ፣ የስኬት ማማ ላይ ብትቀመጡ፣ በብዙ መንገድ ራሳችሁን ብትቀይሩ ምንም የማይደነቁባችሁና የማይኮሩባችሁ ሰዎች ይኖራሉ። ምናልባትም እነዚህ ሰዎች የሚደነቁት ምንም ውጤት ሳይኖር ጠንቅራችሁ ስትሰሩ ይሆናል፣ ይበልጥ የሚገረሙት ተስፋ ትቆርጣላችሁ ብለው በሚያስቡበት ወቅት ጥረታችሁን በመቀጠላችሁ ይሆናል። የለውጥ ሂደታችሁን በሚገባ ይመለከታሉ፣ አካሔዳችሁን ይከታተላሉ፣ ጥረታችሁን እግር በእግር ያስተውላሉ ነገር ግን እንዴት እንደምትሰሩ፣ በምን መንገድ ወደፊት እንደምትጓዙ አያውቁም። ትወድቃላችሁ ብለው ሲጠብቁ እናንተ ፍጥነታችሁን ጨምራችኋል፣ ይሳሳታሉ ብለው ሲጠብቁ እናንተ ይበልጥ ተምራችሁና ተሻሽላችሁ ወደፊት እየተጓዛችሁ ነው። እናንተ ላይ እንከን በመፈለግ ተጠምደዋል ነገር ግን ይሔን ያህል ትልቅ እንከን አያገኙም። በዚህ ሰዓት በጣም ይደነቃሉ፣ የእነርሱ ምቀኝነትና ክፉ ሀሳብ እንደማያስቆማችሁ ሲረዱ ይበልጥ ይገረማሉ። ከጉዟችሁ ሊያስተጓጉሏችሁ ቢሞክሩም ግን አልቻሉም፤ ጭብጨባቸውን በመንፈግ ስሜታችሁን መጉዳት ቢፈልጉም አይችሉም።
አዎ! ሁሉንም አታስደንቁም! ሁሉም ሰው በእናንተ ለውጥና እድገት አይገረምም፣ ሁሉም ሰውም ለጥረታችሁ እውቅና ለመስጠት አይመጣም። "እኔ ህይወቴ እንዲቀየር፣ ስኬታማና ደስተኛ እንድሆን ሰዎች ሊያምኑብኝ ይገባል፣ እነርሱም የግድ ሊደግፉኝ ይገባል።" ብላችሁ የምታስቡ ከሆነ አትሳሳቱ። ምንም ለማድረግ ከሰው አመኔታ ይልቅ የሚያስፈልጋችሁ የራሳችሁ በራስመተማመን ነው፤ ከሰው ድጋፍና ጭብጨባ በላይ የራሳችሁ ተነሳሽነትና ወኔ ነው። ስኬትና ጥንካሬ ለሰዎች እንደምትችሉ ማሳየት ሳይሆን ለራሳችሁ እንደምትችሉና አቅሙ እንዳላችሁ በተግባር ማስመስከር ነው። አንዳንዴ ብዙ ታዛቢና ደጋፊ ያላችሁ ቢመስላችሁም መጀመሪያ ግን የሚታዘባችሁ የገዛ ማንነታችሁ ነው። ራሱን ያላኮራ በምንም መንገድ ሰዎችን ሊያኮራ አይችልም፣ ራሱን ያላስደነቀ ሰው እንዴትም ሰዎችን ሊያስደንቅ አይችልም። "ከአሁን ከአሁን ሰዎችን አስደንቃለሁ፣ ከአሁን ከአሁን ሰዎችን አስደስታለሁ" ብላችሁ የምታስቡ ከሆነ አትሸወዱ። መጀመሪያ ራሳችሁን አስደስቱ፣ በቅድሚያ በራሳችሁ አቅም ተማመኑ።
አዎ! ጀግናዬ..! ከማንም ምንም ያለመጠበቅን ጥበብ ተማር፤ ከፈጣሪ እገዛ ውጪ የማንም ድጋፍ እንደማያስፈልግህ እመን። ውስጥህ ያለው ፅኑ ፍላጎት ትልቁ ብርታትህ ነው፣ ሰዎች የሚጥሉብህ እያንዳንዱ ትቺት ትልቅ ሃይልህ ነው። አንተ ራስህ ውስጥ የማታየውን ሰው ሰዎች በፍፁም አንተ ውስጥ ሊመለከቱት አይችሉም። ስላንተ የሚሉህን ሁሉ አትመን፣ ስለአቅምህ የሚነግሩህን በሙሉ አትቀበል። ራስህን ባወቅከው ልክ ራስህን ወደፊት ትገፋለህ፣ በራስህ በተማመንክ መጠን ጥረትህን ትጨምራለህ። በፍፁም ራስህን ዝቅ አድርገህ አትመልከት፣ በፍፁም አቅምህን አታሳንስ። ብዙ ፈታኝ ሁነቶች ይመጣሉ ይሔዳሉ፣ ብዙ አስቸጋሪ ጊዜያት ይመጣሉ ይሔዳሉ አንተ ግን በፈጣሪ ቸርነት እስካሁን አለህ። ሰው ከሚደነቅብህ በላይ በራስህ የምትደነቅበት ጊዜ ያስፈልግሃል፣ ሰው ከሚኮራብህ በላይ በራስህ የምትኮራበት ሰዓት ያስፈልግሃል። ሰውን ለማስደመም አትጣር ይልቅ ራስህን አስደምም፣ ሰው ፊት በግርማሞገስ ለመመላለስ አትድከም ይልቅ የራስህን ግርማሞገስ ራስህ አጣጥም።
ግሩም ድንቅ ቀን ይሁንልን! 🏞🌞🌅
(Epha A.)
ምክረ-አዕምሮ ለተሻለ ነገ!
በYouTube አማራጭ ይቀላቀሉን!
🔺🔻 SUBSCRIBE NOW
https://www.youtube.com/channel/UCIZv4h3iDx2C7CGbv9WIkVg?sub_confirmation=1
ምክረ-አዕምሮ/ @mikre_aimro 😊 💪
ዓለምን ብትገዙ፣ ብዙ ድንቅ ነገርን ብታደርጉ፣ የስኬት ማማ ላይ ብትቀመጡ፣ በብዙ መንገድ ራሳችሁን ብትቀይሩ ምንም የማይደነቁባችሁና የማይኮሩባችሁ ሰዎች ይኖራሉ። ምናልባትም እነዚህ ሰዎች የሚደነቁት ምንም ውጤት ሳይኖር ጠንቅራችሁ ስትሰሩ ይሆናል፣ ይበልጥ የሚገረሙት ተስፋ ትቆርጣላችሁ ብለው በሚያስቡበት ወቅት ጥረታችሁን በመቀጠላችሁ ይሆናል። የለውጥ ሂደታችሁን በሚገባ ይመለከታሉ፣ አካሔዳችሁን ይከታተላሉ፣ ጥረታችሁን እግር በእግር ያስተውላሉ ነገር ግን እንዴት እንደምትሰሩ፣ በምን መንገድ ወደፊት እንደምትጓዙ አያውቁም። ትወድቃላችሁ ብለው ሲጠብቁ እናንተ ፍጥነታችሁን ጨምራችኋል፣ ይሳሳታሉ ብለው ሲጠብቁ እናንተ ይበልጥ ተምራችሁና ተሻሽላችሁ ወደፊት እየተጓዛችሁ ነው። እናንተ ላይ እንከን በመፈለግ ተጠምደዋል ነገር ግን ይሔን ያህል ትልቅ እንከን አያገኙም። በዚህ ሰዓት በጣም ይደነቃሉ፣ የእነርሱ ምቀኝነትና ክፉ ሀሳብ እንደማያስቆማችሁ ሲረዱ ይበልጥ ይገረማሉ። ከጉዟችሁ ሊያስተጓጉሏችሁ ቢሞክሩም ግን አልቻሉም፤ ጭብጨባቸውን በመንፈግ ስሜታችሁን መጉዳት ቢፈልጉም አይችሉም።
አዎ! ሁሉንም አታስደንቁም! ሁሉም ሰው በእናንተ ለውጥና እድገት አይገረምም፣ ሁሉም ሰውም ለጥረታችሁ እውቅና ለመስጠት አይመጣም። "እኔ ህይወቴ እንዲቀየር፣ ስኬታማና ደስተኛ እንድሆን ሰዎች ሊያምኑብኝ ይገባል፣ እነርሱም የግድ ሊደግፉኝ ይገባል።" ብላችሁ የምታስቡ ከሆነ አትሳሳቱ። ምንም ለማድረግ ከሰው አመኔታ ይልቅ የሚያስፈልጋችሁ የራሳችሁ በራስመተማመን ነው፤ ከሰው ድጋፍና ጭብጨባ በላይ የራሳችሁ ተነሳሽነትና ወኔ ነው። ስኬትና ጥንካሬ ለሰዎች እንደምትችሉ ማሳየት ሳይሆን ለራሳችሁ እንደምትችሉና አቅሙ እንዳላችሁ በተግባር ማስመስከር ነው። አንዳንዴ ብዙ ታዛቢና ደጋፊ ያላችሁ ቢመስላችሁም መጀመሪያ ግን የሚታዘባችሁ የገዛ ማንነታችሁ ነው። ራሱን ያላኮራ በምንም መንገድ ሰዎችን ሊያኮራ አይችልም፣ ራሱን ያላስደነቀ ሰው እንዴትም ሰዎችን ሊያስደንቅ አይችልም። "ከአሁን ከአሁን ሰዎችን አስደንቃለሁ፣ ከአሁን ከአሁን ሰዎችን አስደስታለሁ" ብላችሁ የምታስቡ ከሆነ አትሸወዱ። መጀመሪያ ራሳችሁን አስደስቱ፣ በቅድሚያ በራሳችሁ አቅም ተማመኑ።
አዎ! ጀግናዬ..! ከማንም ምንም ያለመጠበቅን ጥበብ ተማር፤ ከፈጣሪ እገዛ ውጪ የማንም ድጋፍ እንደማያስፈልግህ እመን። ውስጥህ ያለው ፅኑ ፍላጎት ትልቁ ብርታትህ ነው፣ ሰዎች የሚጥሉብህ እያንዳንዱ ትቺት ትልቅ ሃይልህ ነው። አንተ ራስህ ውስጥ የማታየውን ሰው ሰዎች በፍፁም አንተ ውስጥ ሊመለከቱት አይችሉም። ስላንተ የሚሉህን ሁሉ አትመን፣ ስለአቅምህ የሚነግሩህን በሙሉ አትቀበል። ራስህን ባወቅከው ልክ ራስህን ወደፊት ትገፋለህ፣ በራስህ በተማመንክ መጠን ጥረትህን ትጨምራለህ። በፍፁም ራስህን ዝቅ አድርገህ አትመልከት፣ በፍፁም አቅምህን አታሳንስ። ብዙ ፈታኝ ሁነቶች ይመጣሉ ይሔዳሉ፣ ብዙ አስቸጋሪ ጊዜያት ይመጣሉ ይሔዳሉ አንተ ግን በፈጣሪ ቸርነት እስካሁን አለህ። ሰው ከሚደነቅብህ በላይ በራስህ የምትደነቅበት ጊዜ ያስፈልግሃል፣ ሰው ከሚኮራብህ በላይ በራስህ የምትኮራበት ሰዓት ያስፈልግሃል። ሰውን ለማስደመም አትጣር ይልቅ ራስህን አስደምም፣ ሰው ፊት በግርማሞገስ ለመመላለስ አትድከም ይልቅ የራስህን ግርማሞገስ ራስህ አጣጥም።
ግሩም ድንቅ ቀን ይሁንልን! 🏞🌞🌅
(Epha A.)
ምክረ-አዕምሮ ለተሻለ ነገ!
በYouTube አማራጭ ይቀላቀሉን!
🔺🔻 SUBSCRIBE NOW
https://www.youtube.com/channel/UCIZv4h3iDx2C7CGbv9WIkVg?sub_confirmation=1
ምክረ-አዕምሮ/ @mikre_aimro 😊 💪