ፍቅርን ብለሽ...!
ፍቅርን ብለሽ ብታቀረቅሪ፣ አንገትሽን ብትደፊ፣ ብትታዘዢ፣ ዝቅ ብትይ፣ እራስሽን ብትሰዊ፣ እራስሽን ብትሰጪ ምንም ክፋት የለውም። ክፋቱ ፍቅርን ብለሽ ባቀረቀርሽበት ስትረገጪ ነው፤ ፍቅርን ብለሽ እራስሽን በሰጠሽበት ስትሰቃዪ ነው፤ ፍቅርን ብለሽ ብትታዘዢ እንደባሪያ ስትቆጠሪ ነው። ሁሌም ያንቺ ፍቅር በመልካም ሃሳቦች፣ በቅን ተግባሮችና በበጎ ሁነቶች የተደገፈ ሊሆን ይችላል፣ የተቀባዩ ግን በበደልና በክፋት ከታገዘ፣ በጭካኔ ከተሞላ፣ ርህራሄ ከራቀው፣ ፍቅርን ካልታደለ ያንቺ ፍቅርን መምረጥ፣ በፍቅር መመላለስ፣ ፍቅርን ማለት አደጋ ላይ መውደቁ አይቀርም። ፍቅር እንዲገባው የሚፈልግ ሰው ይገባዋል፤ ካልፈለገ ግን ሊገባው ቀርቶ ምንም ለመረዳትና ለማስታወስ አይፈልግም።
አዎ! ጀግኒት..! ፍቅርን ብለሽ ፍቅርን አትግፊ፤ ያተረፍሽ መስሎሽ አታጉድይ፣ ያገኘሽ መስሎሽ አትጪ፤ ባንቺ ውስጥ ባለው ስሜት ብቻ እየተመራሽ አንቺን ብሎ ከመጣው አትሽሺ። በፍቃድሽ ሰዶ ማሳደድ ውስጥ አትግቢ። ለእውነተኛ ስሜትሽ፣ ለጥልቅ ፍቅርሽ ዋጋ ብትከፍይም፣ ብትሰቃይም፣ ብትወጪም ብትወርጂም ይህ ሁሉ መሱዓትነት ለፍቅርሽ ዋስተና፣ ላንቺም ደህንነት ጠበቃ ሊሆንሽ እንደማይችል አስታውሺ። ስትወጂው የማይወድሽን፣ ጊዜ ስትሰጪው ጊዜ የማይሰጥሽን፣ ስትከተይው የሚሸሽሽን፣ ስትደግፊው የሚጎዳሽን፣ ስታክሚው የሚያሳምምሽን እያሳደድሽ ተንከባካቢሽን፣ ውድ አፍቃሪሽን፣ ጠባቂሽን እንዳታጪ፣ በምላሹም ከረፈደ ወደማሳደድ እንዳትገቢ ተጠንቀቂ።
አዎ! ጀግናዬ..! የሚያለቅስልህ፣ የሚያስብልህ፣ የሚራራልህ እያለ ለሚስቅብህ፣ ለሚያፌዝብህ፣ ለሚቀልድብህ አታልቅስ። ላንተውን ጊዜን የሚያመቻች እያለ በትፍ ጊዜ ከሚያስታውስህ ጋር አትታገል። ፍቅርህን ከረገጠው ባላይ በፍቅር የሚያነግስህ አለ፤ መውደድህን ካኮሰሰው በላይ በፍቃዱ የሚንከባከብህ አለ። ለፍቅርህ ብለህ ብቻህን ዋጋ ብትከፍል፣ ብትሰበር፣ ብትጋጣ፣ ብትላላጥ፣ ብትገፋ፣ ብትረሳ እራስህን ታጣለህ እንጂ ፍቅርህን አታተርፍም፤ ማንነትህን ታሳንሳለህ እንጂ ለክብር አትበቃም፤ በስቃይ ትሞላለህ እንጂ ሰላምን አታገኝም። ዋጋ መክፈልህ ድጋፍ ይፈልጋል፤ መሱዓትነትህ አጋዥ መሶዓትነት ይጠበቅበታል። ብቻህን ጥረህ፣ ግረህ የእራስህን ቤት ልትገነባ ትችላለህ ነገር ግን ብቻህን ለፍተህና ደክመህ እኩልነት የሰፈነበት፣ በነፃነት የተሞላ፣ በፍቅር የታነፀ የጋራ ቤት መገንባት እንደማትችል አስታውስ። ቢያንስ የጋራ ጥረትና ልፋት ምሰሶውን ማቆሙ የግድ ነው።
ፍቅርን ብለሽ ብታቀረቅሪ፣ አንገትሽን ብትደፊ፣ ብትታዘዢ፣ ዝቅ ብትይ፣ እራስሽን ብትሰዊ፣ እራስሽን ብትሰጪ ምንም ክፋት የለውም። ክፋቱ ፍቅርን ብለሽ ባቀረቀርሽበት ስትረገጪ ነው፤ ፍቅርን ብለሽ እራስሽን በሰጠሽበት ስትሰቃዪ ነው፤ ፍቅርን ብለሽ ብትታዘዢ እንደባሪያ ስትቆጠሪ ነው። ሁሌም ያንቺ ፍቅር በመልካም ሃሳቦች፣ በቅን ተግባሮችና በበጎ ሁነቶች የተደገፈ ሊሆን ይችላል፣ የተቀባዩ ግን በበደልና በክፋት ከታገዘ፣ በጭካኔ ከተሞላ፣ ርህራሄ ከራቀው፣ ፍቅርን ካልታደለ ያንቺ ፍቅርን መምረጥ፣ በፍቅር መመላለስ፣ ፍቅርን ማለት አደጋ ላይ መውደቁ አይቀርም። ፍቅር እንዲገባው የሚፈልግ ሰው ይገባዋል፤ ካልፈለገ ግን ሊገባው ቀርቶ ምንም ለመረዳትና ለማስታወስ አይፈልግም።
አዎ! ጀግኒት..! ፍቅርን ብለሽ ፍቅርን አትግፊ፤ ያተረፍሽ መስሎሽ አታጉድይ፣ ያገኘሽ መስሎሽ አትጪ፤ ባንቺ ውስጥ ባለው ስሜት ብቻ እየተመራሽ አንቺን ብሎ ከመጣው አትሽሺ። በፍቃድሽ ሰዶ ማሳደድ ውስጥ አትግቢ። ለእውነተኛ ስሜትሽ፣ ለጥልቅ ፍቅርሽ ዋጋ ብትከፍይም፣ ብትሰቃይም፣ ብትወጪም ብትወርጂም ይህ ሁሉ መሱዓትነት ለፍቅርሽ ዋስተና፣ ላንቺም ደህንነት ጠበቃ ሊሆንሽ እንደማይችል አስታውሺ። ስትወጂው የማይወድሽን፣ ጊዜ ስትሰጪው ጊዜ የማይሰጥሽን፣ ስትከተይው የሚሸሽሽን፣ ስትደግፊው የሚጎዳሽን፣ ስታክሚው የሚያሳምምሽን እያሳደድሽ ተንከባካቢሽን፣ ውድ አፍቃሪሽን፣ ጠባቂሽን እንዳታጪ፣ በምላሹም ከረፈደ ወደማሳደድ እንዳትገቢ ተጠንቀቂ።
አዎ! ጀግናዬ..! የሚያለቅስልህ፣ የሚያስብልህ፣ የሚራራልህ እያለ ለሚስቅብህ፣ ለሚያፌዝብህ፣ ለሚቀልድብህ አታልቅስ። ላንተውን ጊዜን የሚያመቻች እያለ በትፍ ጊዜ ከሚያስታውስህ ጋር አትታገል። ፍቅርህን ከረገጠው ባላይ በፍቅር የሚያነግስህ አለ፤ መውደድህን ካኮሰሰው በላይ በፍቃዱ የሚንከባከብህ አለ። ለፍቅርህ ብለህ ብቻህን ዋጋ ብትከፍል፣ ብትሰበር፣ ብትጋጣ፣ ብትላላጥ፣ ብትገፋ፣ ብትረሳ እራስህን ታጣለህ እንጂ ፍቅርህን አታተርፍም፤ ማንነትህን ታሳንሳለህ እንጂ ለክብር አትበቃም፤ በስቃይ ትሞላለህ እንጂ ሰላምን አታገኝም። ዋጋ መክፈልህ ድጋፍ ይፈልጋል፤ መሱዓትነትህ አጋዥ መሶዓትነት ይጠበቅበታል። ብቻህን ጥረህ፣ ግረህ የእራስህን ቤት ልትገነባ ትችላለህ ነገር ግን ብቻህን ለፍተህና ደክመህ እኩልነት የሰፈነበት፣ በነፃነት የተሞላ፣ በፍቅር የታነፀ የጋራ ቤት መገንባት እንደማትችል አስታውስ። ቢያንስ የጋራ ጥረትና ልፋት ምሰሶውን ማቆሙ የግድ ነው።