ከምንም አትጣበቅ!
ለብቻ መሆን፣ እራስን በብዙ ዘርፍ መቻል፣ ለግል አቋም ታማኝና ቆራጥ መሆን፣ ከማንም ምንም ብታጣ እንኳን ከተፅዕኖ ነፃ መሆን መቻል ቀላል አይደለም። ቢሆን ኖሮ ብዙዎች ባደረጉትና ከሰዎች ሲለያዩ እራሳቸውን ባላጡ ነበር። ከአንድ ሰው ወይም ከቁስ ጋር ባለህ ግንኙነት ዘወትር ፈላጊው አንተ፣ ሙሉ ትኩረትህ እርሱ ላይ፣ ደስታና ሰላምህንም ከእርሱ እያገኘህ ከሆነ የአደጋህ ቀይ መብራት በትልቁ እንደበራ አስተውል። የዛፍ ቅርንጫፎች የዛፉ ስር ሲቆረጥ አብረው ይወድቃሉ፣ አንተም እንዲሁ የተደገፍከው፣ የተጣበከው፣ ከልብህ የተማመንክበት ነገር ካጋደለ ያንተም ህይወት ከማጋደልና ከመውደቅ አያመልጥም። እንደ ቀልድ የጀመርከው የትኛውም ግንኙነት ገዢህና መሪህ እንዲሆን አትፍቀድ። ምንም ዘላለማዊ ነገር የለም። ያለን ነገር ሁሉ ጅማሬና ፍፃሜ አለው።
አዎ! ጀግናዬ..! ከፈጣሪህ፣ ከአምላክህ በቀር ከአንዳች ምድራዊ ነገር ለመነጠል እስከሚያስቸግርህ ድረስ አትዋሃደው፤ ከምንም አትጣበቅ፤ ለማንም እራስህን፣ ክብርህን፣ ማንነትህንና ህልውናህን አሳልፈህ አትስጥ። ላንተም ሆነ ለአምላክህ ካንተ በላይ ዋጋ ያለው ነገር የለም። የሚመጡ ሁሉ የጊዜ ጉዳይ እንጂ የሆነ ጊዜ ጥለውህ ይሔዳሉ፤ የማይሔዱም ቢሆን ሊገዙህና እንደፈለጉ ሊነዱህ ስልጣን የላቸውም። የብዙዎች ስብራት፣ የብዙዎች ህመም፣ የብዙዎች ቁስል ዋናው ምክንያት ከልክ ያለፈ መዋሃድ፣ ገደብ የሌለው መጣበቅ ወይም Over Obsession, Over Attachment ነው። ፍቅርና Attachment, ግንኙነትና ጥገኝነት የተለያዩ ጉዳዮች ናቸው። ነፃነትን የሚነሳ ፍቅር ፍቅር ሳይሆን ጥገኝነት ነው፤ "ያለእርሱ መኖር አልችልም፤ ያለእርሷ ህይወት ለእኔ ባዶ ነው" የሚያስብል ግንኙነት ጤነኛ ግንኙነት አይደለም።
አዎ! ምንም አይነት ግንኙነት ውስጥ ብትሆን ትልቁና ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ አንተ ከእራስህ ጋር ያለህ ግንኙነትና አብራህ ያለችው ወዳጅህ ከእራሷ ጋር ያላት ግንኙነት ነው። ግንኙነት ውስጥ ያሉ ሁለት ሰዎች ከእራሳቸው ጋር ሰላም ከሆኑ፣ ምንም አይነት የጥገኝነት ባህሪና ሙጭጭ የማለት ፀባይ ከሌለባቸው ግንኙነት ሰላማዊ፣ የተረጋጋና አስደሳች የመሆን እንድሉ እጅግ በጣም ሰፊ ነው። ሰውን ተደግፈህ ሰው ቢጥልህ ካለሰውየው ድጋፍ ለመነሳት ልትቸገር ትችላለህ፤ ፈጣሪህንና እራስህን ተደግፈህ ብትወድቅ ግን በፈጣሪህ ድጋፍ ባንተ ብርታት ድጋሜ ትነሳለህ። እራስን ማክበር እራስን ከልብ የመውደድ አይነተኛ ማሳያ ነው። መገፋትህ እንዳያሳምምህ፣ በመገለልህ እንዳትሰበር፣ ሁሉም ቦታ በመገኘት ዋጋህን እንዳታጣ፣ ጥገኛ በመሆን ስሜትህ እንዳይጎዳ ከምንም በላይ ለእራስህ ቦታ ስጥ፣ ከማንም በተሻለ ከእግዚአብሔር አምላክህና ከእራስህ ጋር የጠበቀ ግንኙነት ይኑርህ። መጪው ቀድሞ ያልነበረ ስላለመሔዱም እርግጠኛ የማትሆንበት ነውና እራስህን በመውደድህ፣ ለእራስህም ቅድሚያ ባለመስጠትህ ምንም ሃፍረት አይሰማህ።
ለብቻ መሆን፣ እራስን በብዙ ዘርፍ መቻል፣ ለግል አቋም ታማኝና ቆራጥ መሆን፣ ከማንም ምንም ብታጣ እንኳን ከተፅዕኖ ነፃ መሆን መቻል ቀላል አይደለም። ቢሆን ኖሮ ብዙዎች ባደረጉትና ከሰዎች ሲለያዩ እራሳቸውን ባላጡ ነበር። ከአንድ ሰው ወይም ከቁስ ጋር ባለህ ግንኙነት ዘወትር ፈላጊው አንተ፣ ሙሉ ትኩረትህ እርሱ ላይ፣ ደስታና ሰላምህንም ከእርሱ እያገኘህ ከሆነ የአደጋህ ቀይ መብራት በትልቁ እንደበራ አስተውል። የዛፍ ቅርንጫፎች የዛፉ ስር ሲቆረጥ አብረው ይወድቃሉ፣ አንተም እንዲሁ የተደገፍከው፣ የተጣበከው፣ ከልብህ የተማመንክበት ነገር ካጋደለ ያንተም ህይወት ከማጋደልና ከመውደቅ አያመልጥም። እንደ ቀልድ የጀመርከው የትኛውም ግንኙነት ገዢህና መሪህ እንዲሆን አትፍቀድ። ምንም ዘላለማዊ ነገር የለም። ያለን ነገር ሁሉ ጅማሬና ፍፃሜ አለው።
አዎ! ጀግናዬ..! ከፈጣሪህ፣ ከአምላክህ በቀር ከአንዳች ምድራዊ ነገር ለመነጠል እስከሚያስቸግርህ ድረስ አትዋሃደው፤ ከምንም አትጣበቅ፤ ለማንም እራስህን፣ ክብርህን፣ ማንነትህንና ህልውናህን አሳልፈህ አትስጥ። ላንተም ሆነ ለአምላክህ ካንተ በላይ ዋጋ ያለው ነገር የለም። የሚመጡ ሁሉ የጊዜ ጉዳይ እንጂ የሆነ ጊዜ ጥለውህ ይሔዳሉ፤ የማይሔዱም ቢሆን ሊገዙህና እንደፈለጉ ሊነዱህ ስልጣን የላቸውም። የብዙዎች ስብራት፣ የብዙዎች ህመም፣ የብዙዎች ቁስል ዋናው ምክንያት ከልክ ያለፈ መዋሃድ፣ ገደብ የሌለው መጣበቅ ወይም Over Obsession, Over Attachment ነው። ፍቅርና Attachment, ግንኙነትና ጥገኝነት የተለያዩ ጉዳዮች ናቸው። ነፃነትን የሚነሳ ፍቅር ፍቅር ሳይሆን ጥገኝነት ነው፤ "ያለእርሱ መኖር አልችልም፤ ያለእርሷ ህይወት ለእኔ ባዶ ነው" የሚያስብል ግንኙነት ጤነኛ ግንኙነት አይደለም።
አዎ! ምንም አይነት ግንኙነት ውስጥ ብትሆን ትልቁና ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ አንተ ከእራስህ ጋር ያለህ ግንኙነትና አብራህ ያለችው ወዳጅህ ከእራሷ ጋር ያላት ግንኙነት ነው። ግንኙነት ውስጥ ያሉ ሁለት ሰዎች ከእራሳቸው ጋር ሰላም ከሆኑ፣ ምንም አይነት የጥገኝነት ባህሪና ሙጭጭ የማለት ፀባይ ከሌለባቸው ግንኙነት ሰላማዊ፣ የተረጋጋና አስደሳች የመሆን እንድሉ እጅግ በጣም ሰፊ ነው። ሰውን ተደግፈህ ሰው ቢጥልህ ካለሰውየው ድጋፍ ለመነሳት ልትቸገር ትችላለህ፤ ፈጣሪህንና እራስህን ተደግፈህ ብትወድቅ ግን በፈጣሪህ ድጋፍ ባንተ ብርታት ድጋሜ ትነሳለህ። እራስን ማክበር እራስን ከልብ የመውደድ አይነተኛ ማሳያ ነው። መገፋትህ እንዳያሳምምህ፣ በመገለልህ እንዳትሰበር፣ ሁሉም ቦታ በመገኘት ዋጋህን እንዳታጣ፣ ጥገኛ በመሆን ስሜትህ እንዳይጎዳ ከምንም በላይ ለእራስህ ቦታ ስጥ፣ ከማንም በተሻለ ከእግዚአብሔር አምላክህና ከእራስህ ጋር የጠበቀ ግንኙነት ይኑርህ። መጪው ቀድሞ ያልነበረ ስላለመሔዱም እርግጠኛ የማትሆንበት ነውና እራስህን በመውደድህ፣ ለእራስህም ቅድሚያ ባለመስጠትህ ምንም ሃፍረት አይሰማህ።